TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#AddisAbaba በአዲስ አበባ በህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪዎች ላይ የአገልግሎት መስጫ የዋጋ ታሪፍ ማሻሻያ ጥናት መደረጉ ታውቋል። በጥር ወር የነዳጅ ችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ላይ ጭማሪ መደረጉ ይታወቃል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትራንስፖርት ቢሮ ፤ በጥር ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ላይ የተደረገውን የዋጋ ማስተካከያ መነሻ በማድረግ በህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪዎች ላይ…
#Update

በአዲስ አበባ የትራንስፖርት ታሪፍ ላይ ማሻሻያ ተደረገ።

በጥር ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ላይ የተደረገውን የዋጋ ማስተካከያ ተከትሎ የትራንስፖርት ታሪፍ ላይ ማሻሻያ ማድረጉን የአዲስ አበባ ከተማ ትራንስፖርት ቢሮ አስታውቋል፡፡

አዲሱ የታሪፍ ማሻሻያ #ከነገ_ጀምሮ ተግባራዊ እንደሚደረግ ተገልጿል፡፡

በዚህም መሰረት ፦ ለሚኒባስ የታክስ ተሸከርካሪዎች ፦

- የጉዞ ርቀት በኪሎ ሜትር እስከ 2 ነጥብ 5 ርቀት በነባር የክፍያ ታሪፍ 3 ብር ከ50 ሣንቲም የነበረው በተስተካከለው ታሪፍ 4 ብር፣

- ከ2 ነጥብ 6 እስከ 5ኪሎ ሜትር ርቀት 6 ብር ከ50 ሣንቲም የነበረው ታሪፍ በአዲሱ የታሪፍ ማሻሻያ 7 ብር ፤

- ከ5 ነጥብ 1 እስከ 7 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር ርቀት 10 ብር የነበረው ታሪፍ በተመሳሳይ 10 ብር ሆኖ እንዲቀጥል ተወስኗል፡፡

ምንጭ፦ ኤፍ ቢ ሲ

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update በአዲስ አበባ የትራንስፖርት ታሪፍ ላይ ማሻሻያ ተደረገ። በጥር ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ላይ የተደረገውን የዋጋ ማስተካከያ ተከትሎ የትራንስፖርት ታሪፍ ላይ ማሻሻያ ማድረጉን የአዲስ አበባ ከተማ ትራንስፖርት ቢሮ አስታውቋል፡፡ አዲሱ የታሪፍ ማሻሻያ #ከነገ_ጀምሮ ተግባራዊ እንደሚደረግ ተገልጿል፡፡ በዚህም መሰረት ፦ ለሚኒባስ የታክስ ተሸከርካሪዎች ፦ - የጉዞ ርቀት…
#AddisAbaba

በጥር ወር የተደረገውን የነዳጅ የችርቻሮ ዋጋ ጭማሪን ተከትሎት በአዲስ አበባ ትራንስፖርት ታሪፍ ላይ የታሪፍ ማሻሻያ ዛሬ ተደርጓል።

ማሻሻያው ከነገ ጀምሮ ተግባራዊ የሚደረገ ሲሆን የታሪፍ ጭማሬ የተደረገው የህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት በሚሰጡ ፦
- የሚኒባስ፣
- የሚድ ባስ ማለትም ሀይገርና ቅጥቅጥ፣
- የከተማ አውቶብስ አገልግሎት ድርጅት - የአዲስ አበባ ቀላል ባቡር አገልግሎት ድርጅት ናቸው።

ሙሉ ዝርዝሩን ከላይ ይመልከቱ።

ምንጭ ፦ የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ

@tikvahethiopia
#ከተራ #ጥምቀት

መንግስት የዘንድሮ ዓመት የከተራ እና የጥምቀት በዓል በመላው ሀገሪቱ #በሰላም ተከብሮ መጠናቀቁን አሳውቋል።

የበዓላቱን በሰላም መጠናቀቅ አስመልክቶ ዛሬ ማምሻውን በኮሚኒኬሽን አገልግሎት በኩል መግለጫ ያወጣው መንግሥት ፤ የከተራ እንዲሁም የጥምቀት በዓላት በድምቀት እና በሰላም እንዲጠናቀቁ ላደረጉ አካላት በሙሉ ምስጋና አቅርቧል።

@tikvahethiopia
ከ / ወደ ትግራይ  የየብስ ትራንስፖርት መቼ ይጀምራል ?

ከትግራይ ክልል ወደ ተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች #በቅርቡ የየብስ ትራንስፖርት እንደሚጀምር ከሰሞኑን ተገልጿል።

ከአየር ትራንስፖርት በተጨማሪ የየብስ ትራንስፖርት በቅርብ ቀን ለማስጀመር ከፌዴራል መንግስት ጋር በመነጋገር ኮሚቴ ተቋቁሞ እየተሰራ መሆኑን የክልል የኮንድትራክሽንና መንገድ ትራንስፖርት ቢሮ አሳውቋል።

ከሰላም ስምምነቱ በኃላ በህጋዊ መንገድ የህዝብ የየብስ ትራንስፖርት እንዳልተጀመረ የገለፀው ቢሮው ሸቀጦች፣ ሰብዓዊ እርዳታ እየገባ ስለመሆኑ አመልክቷል።

ወደ ትግራይ ክልል ለሁለት ዓመት ትራንስፖርት ተዘግቶ ስለቆየ አሁን ላይ ያለው የአየር ትራንስፖርት በገንዘብ ውድም ስለሆነ ብቻውን የህዝቡን ችግር አይፈታም ያለው ቢሮው የኢኮኖሚ ውስንነት ያለበት፣ ህዝቡም በብዛት መንቀሳቀስ እንዲችል የመንገድ ትራንስፖርት ማስጀመር አስፈላጊ ስለሆነ በኛ በኩል አስፈላጊ ዝግጅት እያደረግን ነው ብሏል ለክልሉ ቴሌቪዥን በሰጠው ቃል።

በቅርብ ለሚጀመረው ለየብስ ትራንስፖርት ሀገር አቋራጭ ተሽከርካሪዎች በማህበራቸው በኩል አስፈላጊ ዝግጅት እያደረጉ መሆኑ ተገልጿል።

ከ/ወደ ትግራይ የየብስ ትራንስፖርት በቅርብ የጀመራል ይባል እንጂ ቁርጥ ያለው ትክክለኛ ቀን አልታወቀም።

የአየር ትራንስፖርት ውድ በመሆኑና ወረፋውም እጅግ ከፍተኛ ስለሆነ በትግራይ ክልል ነዋሪ የሆኑ እጅግ በርካታ ዜጎች ለተለያዩ የማህበራዊ ጉዳዮቻቸው፣ ለስራ እንቅስቃሴ የየብስ ትራንስፖርት እስኪጀመር እየተጠባበቁ ይገኛሉ።

@tikvahethiopia
Forwarded from TIKVAH-ETHIOPIA
ባንካችን አቢሲንያ ከሳፋሪኮም ጋር በአጋርነት መሥራት ጀመረ፡፡

የባንካችን ደንበኞች የሳፋሪኮም አየር ሰዓት በአቢሲንያ ሞባይል ባንኪንግ ካሉበት ሆነው ወይም አቅራቢያዎ በሚገኙት የባንካችን ቅርንጫፎች መሙላት ይችላሉ፡፡

#BankofAbyssinia #Abyssinia #Banking #BankingService #MobileBanking #Digital #DigitalEthiopia #DigitalPayment #Ethiopia #የሁሉም_ምርጫ
#Triple_E_Hotel

በመዲናችን አ/አ ቦሌ ክ/ከተማ ወረዳ 03፣ 22 በተለምዶ ዳውን ታውን ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በ500 ካ.ሜ ቦታ ላይ ባለቤትነቱ የአቶ  መስፍን ውብሸት በሆነው ኤሉዛይ ሆቴል እና ቱሪዝም ካምፓኒ የተገነባው ትሪፕል-ኢ ሆቴል እና ስፓ ዛሬ በይፋ ይመረቃል።

ከአራት መቶ ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ እንደወጣበት የተነገረለት ይኸው ሆቴል በ4 ዓመት ግንባታው ተጠናቆ የሙከራ ስራውን የጀመረው በሐምሌ ወር ነበር።

ትሪፕል-ኢ ሆቴል በውስጡ ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ 48 የመኝታ ክፍሎች፣ አዳራሽ፣ ባር፣ ሬስቶራንት፣ ካፍቴሪያ፣ ሩፍ ቶፕ ኦፕን ባር እና ፒዜሪያ፣ ሳውና ፣ስቲም ባዝ፣ ሞሮኮ፣ ማሳጅ፣ ጂምናዚየም፣ የሴቶችና የወንዶች ጸጉር ቤትን አሟልቶ የያዘ ነው፡፡ 

ሆቴሉ ስራ ከጀመረ ጀምሮ እስካሁን ድረስ 70 ለሚሆኑ ሰራተኞች ቋሚ የስራ ዕድል የፈጠረ ሲሆን በቀጣይ ሆቴሉ በሙሉ አቅሙ ወደ ስራ ሲገባ ከ100 በላይ ለሚሆኑ ሰራተኞች ቋሚ የስራ ዕድል የሚፈጥር ይሆናል፡፡ ካምፓኒው በቀጣይ በአዲስአበባ ሌሎች ባለኮከብ ሆቴሎችን ለመገንባት በዝግጅት ላይ ይገኛል ተብሏል።

ሆቴሉን በምስል ለመጎብኘት 👉 https://telegra.ph/Triple-e-Hotel--Spa-01-20
#UK

የዩናይትድ ኪንግደም (UK) ጠቅላይ ሚኒስትር ሪሺ ሱናክ እየተጓዘ ባለ መኪና ውስጥ ሳሉ የደህንነት (መቀመጫ) ቀበቶ ባለማሰራቸው ተቀጡ።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጉዞ ላይ ባለ መኪና ውስጥ ሆነው ማኅበራዊ ሚዲያ ላይ የሚለጠፍ ቪድዮ እየቀረጹ ሳለ የደህንነት (መቀመጫ) ቀበቷቸውን ባለማሰራቸው መቀጣታቸውን ፖሊስ ገልጿል።

የጠቅላይ ሚኒስትሩ ቢሮ  " ስህተት መሆኑን እናምናለን ይቅርታም እንጠይቃለን " ብሎ ቅጣቱን እንደሚከፍል አክሏል።

ዩናይትድ ኪንግደም ውስጥ የመቀመጫ ቀበቶ ያላደረጉ ሰዎች 100 ፓውንድ ይቀጣሉ።

ጉዳዩ ፍርድ ቤት ከደረሰ ቅጣቱ 500 ፓውንድ ሊደርስ ይችላል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለቅጣት የተዳረጉት ስለ መንግሥታቸው ወጭ የሚገልጽ ቪድዮ መኪና ውስጥ ቀርጸው በኢንስታግራም ገጻቸው ባጋሩበት ወቅት ነው።

ምንጭ፦ ቢቢሲ

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ፎቶ ፦ " የአፍሪካ ሃገራት ቻምፒዮና/ቻን " እየተባለ በሚጠራው የአፍሪካ ሀገራት ውድድር ላይ ተሳታፊ የሆነው የሀገራችን ብሔራዊ ቡድን ለውድድሩ ዝግጅት ዛሬ ሞሮኮ ካዛብላንካ በሰላም መድረሱን የቲክቫህ ስፖርት ቤተሰብ አባላት አሳውቀዋል። ቡድኑ ወደ ሞሮኮ ከመሄዱ በፊት በሀገር ውስጥ ልምምድ ሲያደርግ ቆይቷል። በሞሮከ የብሔራዊ ቡድኑ ዝግጅት ለሚቀጥሉት ስምንት ቀናት የሚያደርግ ሲሆን የፊታችን ቅዳሜ…
#Update

የአፍሪካ ሃገራት ቻምፒዮና / CHAN AFRICA እየተባለ በሚጠራው የአፍሪካ ሀገራት ውድድር ላይ ተሳታፊ የነበረው የሀገራችን ብሔራዊ ቡድን ከምድቡ ማለፍ ሳይችል ቀርቷል።

ብሄራዊ ቡድኑ #ከሞዛምቢክ#አልጄሪያ እና #ሊቢያ ጋር በአንድ ምድብ ነበር የተደለደለው። ከሞዛምቢክ 0 ለ 0 ሲለያይ በአልጄሪያ 1 ለ 0 ተሸንፎ ነበር።

በምድብ የመጨረሻው ጨዋታ #ከሊብያ ጋር የገጠመው ብሔራዊ ቡድናችን 3 ለ 1 በሆነ ውጤት ተሸንፎ ከወዲሁ ከውድድሩ ተሰናብቷል።

ቡድኑ በውድድሩ ላይ በአጠቃላይ 4 ጎሎች ሲቆጠሩበት ማስቆጠር የቻለው አንድ ጎል ብቻ ነው።

በተመሳሳይ ምድብ ውስጥ የነበሩት አልጄሪያ እና ሞዛምቢክ ከምድቡ ማለፋቸውን አረጋግጠዋል።

የዘንድሮው የአፍሪካ ሃገራት ቻምፒዮና እየተካሄደ የሚገኘው በአልጄሪያ ነው።

ተጨማሪ : https://publielectoral.lat/+VvwzStMNcNHmhK0x    

@tikvahethiopia
Forwarded from TIKVAH-ETHIOPIA
ባንካችን አቢሲንያ ከሳፋሪኮም ጋር በአጋርነት መሥራት ጀመረ፡፡

የባንካችን ደንበኞች የሳፋሪኮም አየር ሰዓት በአቢሲንያ ሞባይል ባንኪንግ ካሉበት ሆነው ወይም አቅራቢያዎ በሚገኙት የባንካችን ቅርንጫፎች መሙላት ይችላሉ፡፡

#BankofAbyssinia #Abyssinia #Banking #BankingService #MobileBanking #Digital #DigitalEthiopia #DigitalPayment #Ethiopia #የሁሉም_ምርጫ
TIKVAH-ETHIOPIA
#Triple_E_Hotel በመዲናችን አ/አ ቦሌ ክ/ከተማ ወረዳ 03፣ 22 በተለምዶ ዳውን ታውን ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በ500 ካ.ሜ ቦታ ላይ ባለቤትነቱ የአቶ  መስፍን ውብሸት በሆነው ኤሉዛይ ሆቴል እና ቱሪዝም ካምፓኒ የተገነባው ትሪፕል-ኢ ሆቴል እና ስፓ ዛሬ በይፋ ይመረቃል። ከአራት መቶ ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ እንደወጣበት የተነገረለት ይኸው ሆቴል በ4 ዓመት ግንባታው ተጠናቆ የሙከራ ስራውን…
#Triple_E_Hotel

በመዲናችን ቦሌ ክ/ከተማ ወረዳ 03፣ 22 በተለምዶ ዳውን ታውን ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በ500 ካ.ሜ ቦታ ላይ ያረፈው ትሪፕል-ኢ ሆቴል እና ስፓ በትላንትናው ዕለት ተመርቋል።

ከአራት መቶ ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ እንደወጣበት የተነገረለት ይኸው ሆቴል በ4 ዓመት ግንባታው ተጠናቆ የሙከራ ስራውን የጀመረው በሐምሌ ወር ነበር።

ሆቴሉን በምስል ለመጎብኘት 👉 https://telegra.ph/Triple-e-Hotel--Spa-01-20
#ETHIOPIA #USA

የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ከአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊነከን ጋር በስልክ መወያየታቸውን የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መ/ቤት አሳውቋል።

ውይይታቸው ትኩረቱን ያደረገው የሰላም ስምምነቱን አፈፃፀም በተመለከተ እንደነበር ተመላክቷል።

የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መ/ቤት ይፋ ባደረገው መረጃ፤ የኤርትራ ወታደሮች ከሰሜን ኢትዮጵያ እየወጡ መሆኑን በማመልከት በዚህም ጉዳይ ብሊንከን ከጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ መነጋገራቸውን ገልጿል።

ብሊንከን ፤ የታየውን መሻሻል (የኤርትራ ሰራዊት መውጣት መጀመር) በደስታ መቀበላቸው፤ ይህም በሰሜን ኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላም ለማስፈን ቁልፍ መሆኑን የገለፁ ሲሆን የዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብቶች ተቆጣጣሪዎች ወደየአካባቢዎቹ እንዲደርሱ አሳስበዋል።

ብሊንከን ፤ ሀገራቸው አሜሪካ በአፍሪካ ህብረት መሪነት እየተካሄደ ላለው የሰላም ሂደት ድጋፏን አጠናክራ እንደምትቀጥል ለዶ/ር ዐቢይ አህመድ አረጋግጠዋል።

በተጨማሪ፤ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ እና ብሊንከን በኦሮሚያ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች ያለውን አለመረጋጋት እንዲያበቃ በማድረግ አስፈላጊነት ላይም መመካከራቸው ተገልጿል።

ይህንን የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት መረጃ በተመለከተ ከኢትዮጵያ መንግሥት ኮሚኒኬሽን /ከጠ/ሚ ፅ/ቤት/ ከራሳቸው ከጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ በኩል ምንም የተባለ ነገር የለም።

የኤርትራ ወታደሮችን ከሰሜን ኢትዮጵያ በተለይ ከትግራይ ክልል መውጣትን በተመለከተ ከሰሞኑን ዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን ነዋሪዎችን ዋቢ አድርገው ዘገባ እያቀረቡ ይገኛሉ ነገር ግን  ወታደሮቹ እየወጡ ስለመሆኑ ከአፍሪካ ህብረት/ ከኢትዮጵያ መንግሥት/ከትግራይ ክልል አመራሮች በኩል እስካሁን ምንም ይፋዊ መግለጫ አልተሰጠም።

@tikvahethiopia