TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#AmanuelMentalHospital

ወደ አማኑኤል ሆስፒታል የሚገቡ የአዕምሮ ህሙማን ቁጥር እየጨመረ ነው።

ሆስፒታሉ አዳዲስ ታካሚዎች እየጨመሩ መጥተዋል ብሏል።

አማኑኤል አዕምሮ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ምን አለ ?

- ከሚመጡ ታካሚዎች ከሴቶች በበለጠ ወንዶች ትልቁን ቦታ ይይዛሉ።

- ከሆስፒታሉ ደህና ሆነው ወጥተው ከወጡም በኋላ ያለው ሁኔታ የተስተካከለ ስለማይሆንላቸው ተመልሶ የማገርሸት እና ተመልሶ የመምጣት ነገር እየጨመረ ይገኛል።

- አንድ ክፍተት እየፈጠረ ያለው የተጠኑ ጥናቶች ባለመኖራቸው መንግስትም ትኩረት እየሰጠው ባለመሆኑ ነው።

- ወደ ሆስፒታል የሚመጡ አብዛኞቹ ታካሚዎች ፦
° #ድባቴ
° #ባይፖላር
° #ከባድ_የአእምሮ_ህመም
° #በአደንዛዥ_እፅ_ሱስ ሳቢያ የሚመጣ የአዕምሮ ህመም የተጠቁ ናቸው።

- በሆስፒታሉ ከሚታከሙ ታካሚዎቸ ውስጥ በብዛት ከ20-40 አመት የእድሜ ክልል ውስጥ የሚገኙት ቁጥራቸው ከፍ ይላል።

- የሆስፒታሉ ግንባታ በጣም የቆየና ደረጃውን የጠበቀ ባለመሆኑ በተደጋጋሚ የአልጋ እጥረቶች እየገጠሙ ነው።

- ለሚፈጠሩት ክፍተቶች እንደማስተንፈሻ እንዲሆን በጤና ሚኒስቴር አማካኝነት በሆስፒታሉ ግቢ ሌላ ህንፃ ለመገንባት መሰረተ ድንጋይ ተጥሏል። በአንድ አመት ግዜ ውስጥ ያልቃል ተብሎ እቅድ ተይዟል።

- የአእምሮ ህመም ታክሞ መዳን የሚችል በመሆኑ ህብረተሰቡ በቂ ግንዛቤ ሊኖረው ይገባል።

የዚህ መረጃ ባለቤት ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 ሬድዮ ጣቢያ ነው።

@tikvahethiopia