TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
ከውሸት ዜናዎች ተጠንቀቁ። በቅርቡ ከዚህ ዓለም በሞት የተለየው አርቲስት ታሪኩ ብርሃኑ (ባባ) በህይወት በነበረበት ሰዓት የዓይን ብሌኑን ለመለገስ ቃል በገባው መሰረት የኢትዮጵያ ዓይን ባንክ የአርቲስቱን ቃል ተፈፃሚ ማድረጉ አይዘነጋም። ነገር ግን ከአርቲስት ታሪኩ ጋር በተያያዘ በዩትዩብ እና በሌሎች ሶሻል ሚዲያዎች ሀሰተኛ ዜናዎች እና መልዕክቶች እየተሰራጩ መሆኑን የኢትዮጵያ ዓይን ባንክ አሳውቋል።…
#እንድታውቁት

ስለ ዓይን ብሌን ንቅለ ተከላ ፦

(የኢትዮጵያ ዓይን ባንክ)

- የዓይን ባንኩ ንቅለ ተከላ የተደረገላቸው ሰዎች የማን እንደተሰራላቸው አያሳውቅም፤

- ባንኩ አስፈላጊውን ፍተሸ በማድረግ ለንቅለ ተከላ ማዕከላት ያሰራጫል፤

- የዓይን ባንኩ የዓይን ብሌን ንቅለ ተከላ ህክምና ከሚሰሩ ተቋማት ጋር ይሰራል፤

- የዓይን ብሌን ንቅለ ተከላ ህክምና የሚሰጠው የዓይን ብሌን ንቅለ ተከላ የሚሰራበቸው ማዕከላት ውስጥ ብቻ ነው እነዚህም ፦
👉 ዳግማዊ ምኒልክ ኮምፕርሄንሲቭ ሪፈራል ሆሰፒታል
👉 ቅ.ጳውሎስ ሚሊኔም ኮሌጅ
👉 ጎንደር ስፔሻላይዝድ ማስተማሪያ ሆስፒታል
👉 ጅማ ስፔሻይዝድ ማስተማሪያ ሆስፒታል
👉 ሐዋሳ ስፔሻላይዝድ ማስተማሪያ ሆስፒታል ናቸው።

በተጨማሪም አዲስ አበባ ውስጥ በሚገኙ የግል የዓይን ህክምና ጣቢያወች መካከል ፦
👉 ብሩህ ቪዢን ልዩ የዓይን ክሊኒክ
👉 ዋጋ ቪዥን ልዩ የዓይን ክሊኒክ
👉 አልአሚን የዓይን ህክምና ማዕከል
👉 ላቪስታ ስፔሻሊስት የዓይን ክልኒክ ናቸው።

የኢትዮጵያ ዓይን ባንክን በምን ላግኛቸው ?

አድራሻ ፦ ዳግማዊ ምኒልክ ሆስፒታል ቅጥር ግቢ ውስጥ

ስልክ ፦
0111223838
0930006367
0930006368
Email eyebank2015@gmail.com

#የኢትዮጵያ_ዓይን_ባንክ

@tikvahethiopia