TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
ከውሸት ዜናዎች ተጠንቀቁ። በቅርቡ ከዚህ ዓለም በሞት የተለየው አርቲስት ታሪኩ ብርሃኑ (ባባ) በህይወት በነበረበት ሰዓት የዓይን ብሌኑን ለመለገስ ቃል በገባው መሰረት የኢትዮጵያ ዓይን ባንክ የአርቲስቱን ቃል ተፈፃሚ ማድረጉ አይዘነጋም። ነገር ግን ከአርቲስት ታሪኩ ጋር በተያያዘ በዩትዩብ እና በሌሎች ሶሻል ሚዲያዎች ሀሰተኛ ዜናዎች እና መልዕክቶች እየተሰራጩ መሆኑን የኢትዮጵያ ዓይን ባንክ አሳውቋል።…
#እንድታውቁት

ስለ ዓይን ብሌን ንቅለ ተከላ ፦

(የኢትዮጵያ ዓይን ባንክ)

- የዓይን ባንኩ ንቅለ ተከላ የተደረገላቸው ሰዎች የማን እንደተሰራላቸው አያሳውቅም፤

- ባንኩ አስፈላጊውን ፍተሸ በማድረግ ለንቅለ ተከላ ማዕከላት ያሰራጫል፤

- የዓይን ባንኩ የዓይን ብሌን ንቅለ ተከላ ህክምና ከሚሰሩ ተቋማት ጋር ይሰራል፤

- የዓይን ብሌን ንቅለ ተከላ ህክምና የሚሰጠው የዓይን ብሌን ንቅለ ተከላ የሚሰራበቸው ማዕከላት ውስጥ ብቻ ነው እነዚህም ፦
👉 ዳግማዊ ምኒልክ ኮምፕርሄንሲቭ ሪፈራል ሆሰፒታል
👉 ቅ.ጳውሎስ ሚሊኔም ኮሌጅ
👉 ጎንደር ስፔሻላይዝድ ማስተማሪያ ሆስፒታል
👉 ጅማ ስፔሻይዝድ ማስተማሪያ ሆስፒታል
👉 ሐዋሳ ስፔሻላይዝድ ማስተማሪያ ሆስፒታል ናቸው።

በተጨማሪም አዲስ አበባ ውስጥ በሚገኙ የግል የዓይን ህክምና ጣቢያወች መካከል ፦
👉 ብሩህ ቪዢን ልዩ የዓይን ክሊኒክ
👉 ዋጋ ቪዥን ልዩ የዓይን ክሊኒክ
👉 አልአሚን የዓይን ህክምና ማዕከል
👉 ላቪስታ ስፔሻሊስት የዓይን ክልኒክ ናቸው።

የኢትዮጵያ ዓይን ባንክን በምን ላግኛቸው ?

አድራሻ ፦ ዳግማዊ ምኒልክ ሆስፒታል ቅጥር ግቢ ውስጥ

ስልክ ፦
0111223838
0930006367
0930006368
Email eyebank2015@gmail.com

#የኢትዮጵያ_ዓይን_ባንክ

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ETHIOPIA #PEACE

በኢትዮጵያ መንግስት እና በህወሓት መካከል የተደረሰው የሰላም ስምምነት ትግበራ " ተስፋ ሰጪ ነው " ሲሉ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ገለፁ።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህን የገለፁት የናይሮቢ ሁለተኛውን ውይይት ተከትሎ የሰላም ሂደቱ በተገመገመበት ወቅት ነው።

ዛሬ የናይሮቢውን ውይይት ተከትሎ የሰላም ሂደቱ የተገመገመ ሲሆን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ግምገማውን ተከትሎ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው  " የሰላም ስምምነቱ የትግበራ ሂደት ተስፋ ሰጪ ነው። " ብለዋል።

" አሁንም ለሰላም ባለን ቁርጠኝነት ጸንተናል " ሲሉ ገልፀዋል።

@tikvahethiopia
" ... አንድ ተማሪ ከነልጇ ህይወታቸው አልፏል " - የቤኒሻንጉል  ጉሙዝ ትምህርት ቢሮ

የ2ኛ ዙር የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ተፈታኝ ተማሪዎች ወደሚፈተኑበት ተቋም እየገቡ እንደሆነ ይታወቃል።

ዛሬ ከወደ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል አሳዛኝ ዜና ተሰምቷል።

በ2ኛ ዙር ለሚሰጠው የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ለመፈተን ከሚዢጋ ወረዳ ወደ አሶሳ ሲመጡ በነበሩ ተማሪዎች ላይ የትራፊክ አደጋ ደርሶ ነበር።

ከክልሉ ትምህርት ቢሮ በተገኘ መረጀ በደረሰው የተሸከርካሪ አደጋ ፤ አንድ ተማሪ ከልጇ ጋር ሕይወታቸው አልፏል።

በአምስት ተማሪዎች ላይ የአካል ጉዳት ደርሷል፡፡

ምንጭ፦ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ትምህርት ቢሮ የማህበራዊ ትስስር ገፅ

@tikvahethiopia
#Tigray #Mekelle

ዛሬ በአፈ ጉባኤ ታገሠ ጫፎ የሚመራ የፌደራል መንግሥት ከፍተኛ የልኡካን ቡድን የትግራይ መዲና መቐለ አቅንቷል።

የልኡካን ቡድኑ ወደ መቐለ ያቀናው የሰላም ስምምነቱን የትግበራ ሂደት ለመቃኘትና በስምምነቱ የተካተቱ ዋና ዋና ጉዳዮች በታቀደው መሠረት እንዲፈጸሙ ለማድረግ ነው ተብሏል።

የልኡካን ቡድኑ ከሁለት ዓመት በኋላ ወደ መቐለ የተጓዘ የመጀመሪያው የፌዴራል መንግሥት ከፍተኛ ልኡክ ሲሆን ስምምነቱ በመልካም ሁኔታ ላይ  እንደሚገኝ ማሳያ መሆኑ ታምኖበታል።

በልዑካን ቡድኑ #የብሔራዊ_ምክክር_ኮሚሽን አባላትም ተካትተዋል።

ምንጭ፦ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Tigray #Mekelle ዛሬ በአፈ ጉባኤ ታገሠ ጫፎ የሚመራ የፌደራል መንግሥት ከፍተኛ የልኡካን ቡድን የትግራይ መዲና መቐለ አቅንቷል። የልኡካን ቡድኑ ወደ መቐለ ያቀናው የሰላም ስምምነቱን የትግበራ ሂደት ለመቃኘትና በስምምነቱ የተካተቱ ዋና ዋና ጉዳዮች በታቀደው መሠረት እንዲፈጸሙ ለማድረግ ነው ተብሏል። የልኡካን ቡድኑ ከሁለት ዓመት በኋላ ወደ መቐለ የተጓዘ የመጀመሪያው የፌዴራል መንግሥት ከፍተኛ…
ፎቶ ፦ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ የተመራው የፌደራል መንግስት ልኡካን ቡድን የትግራይ ክልል መዲና መቐለ ገብቷል።

ቡድኑ መቐለ ሲደረስ የሃይማኖት አባቶች ፣ እነ አቶ ጌታቸው ረዳ ፣ ዶ/ር ሀጎስ ጎደፋይን ጨምሮ ክልሉን እያስተዳደሩ የሚገኙ ከፍተኛ አመራሮች አቀባበል አድርገዋል።

#Peace #Ethiopia

Photo Credit : Demtsi Weyane / ድምፂ ወያነ

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Tigray #Mekelle

ተጨማሪ ፎቶዎች፦ ዛሬ በመቐለ ከተማ ለፌዴራል መንግስት ልዑካን ቡድን የተደረገለት አቀባበል።

Photo Credit : Tigrai Television & Demtsi Weyane

@tikvahethiopia