TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update ኢህአዴግ⬇️

የኢህአዴግ ምክር ቤት ከዛሬ ጀምሮ #መደበኛ ስብሰባውን እንደሚያካሂድ የኢህአዴግ ምክር ቤት ጽህፈት ቤት አስታወቀ።

ፅህፈት ቤቱ ለfbc እንዳስታወቀው፥ ምክር ቤቱ ባለፈው ሳምንት በኢህአዴግ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ የተገመገሙና ለምክር ቤቱ እንዲቀርቡ የተወሰኑ አጀንዳዎች ላይ ይወያያል።

ምክር ቤቱ ድርጅቱ ከመስከረም አጋማሽ በኃላ በሚካሄደው 11ኛው ድርጅታዊ ጉባኤ የሚቀርብ ሪፖርት ላይም ይወያያል ተብሎ ይጠበቃል፡፡

በተጨማሪም በወቅታዊ ድርጅታዊና ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ይመክራል ተብሎ እንደሚጠበቅ ጽህፈት ቤቱ አመልክቷል፡፡

©fbc
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update⬆️የኢህአዴግ ምክር ቤት #መደበኛ ስብሰባውን ማካሄድ ጀምሯል። ምክር ቤቱ ባለፈው ሳምንት በኢህአዴግ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ የተገመገሙና ለምክር ቤቱ እንዲቀርቡ የተወሰኑ አጀንዳዎች ላይ ይወያያል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ፌደራል ፖሊስ⬇️

በአዲስ አበባ #ለዛሬ የተጠራ ምንም ዓይነት #ሰልፍ አለመኖሩን የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ገለፀ።

ኮሚሽኑ ለfbc እንደገለፀው፥ ህብረተሰቡ በመዲናዋ ምንም ዓይነት የተጠራ ሰልፍ አለመኖሩን አውቆ #መደበኛ የእለት ተእለት እንቅስቃሴውን እንዲያከናውን አሳስቧል።

መቀመጫቸውን አዲስ አበባ ያደረጉ አንዳንድ ዓለም አቀፍ ተቋማት ለረቡዕ በአዲስ አበባ የተጠራ ሰልፍ አለ በሚል ያወጡት መረጃ ሙሉ በሙሉ #የተሳሳተም ነው ብሏል።

©fbc
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ነቀምት‼️

በነቀምቴ ከተማ አስተዳደር ተቋርጦ የቆየው  የህዝብ አገልግሎት ሰጪ ተቋማትና የትራንስፖርት እንቅስቃሴ  #መደበኛ ስራ  መጀመሩን የከተማው አስተዳደር አስታወቀ፡፡

የከተማው የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን  ጉዳዮች ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ፈይሣ ብርሃኑ እንዳሉት ተቋማቱ አገልግሎት ያቆሙት በቤኒሻንጉል ጉሙዝና ምስራቅ ወለጋ አዋሳኝ ወረዳዎች በተፈጠረ ግጭት ለተፈናቀሉ ወገኖች ዘላቂ #መፍትሔ እንዲሰጥ ለመጠየቅ ነው።

በዚህም ከጥቅምት 26/2011 ዓ.ም. ጀምሮ ለሶስት ቀናት ስራቸውን አቋርጠው ቆይተዋል፡፡

እነዚህ በከተማዋ የሚገኙ  የተለያዩ የንግድ ድርጅቶች፣ የትራንስፖርት ፣ የትምህርትና ሌሎች አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ዛሬ ወደ መደበኛ ሥራቸው መመለሳቸውን ኃላፊው አስታውቀዋል፡፡

የከተማዋ  ፖሊስ መምሪያ አዛዥ ምክትል ኮማንደር ግርማ አብዲሣ በበኩላቸው በአሁኑ ጊዜ በከተማው አስተማማኝ ሠላም ሰፍኖ ሁሉም ነገር  ወደ ነበረበት መመለሱን ገልጸዋል፡፡

ከነዋሪዎቹ  መካከል ወይዘሮ የሺ ሐረግ ፋንታሁን በሰጡት አስተያየት የአገልግሎት ሰጪ ተቋማት ስራ ማቆማቸው በተለይ በቀን ሠራተኛውና  በሌሎችም በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ በሚገኙ ነዋሪዎች ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ ማሳደሩንና የመንግሥት ስራም መበደሉን ጠቁመዋል፡፡፡

በመንገድ መዘጋጋት ምክንያት አምቡላንሶች ወላድ እናቶችንና ድንገተኛ ህሙማንን ወደ ጤና ተቋማት ለማድረስ ችግር ሆኖባቸው መቆየቱን የተናገሩት ደግሞ የከተማዋ ቀበሌ ሰባት ነዋሪ ወይዘሮ ድንቅነሽ ምትኩ  ናቸው ፡፡

ሌላው የከተማዋ ቀበሌ ሶስት ነዋሪ አቶ ጌታሁን ወዳጆ እንዳሉት ማንም እንደፈለገው መንገድ የሚዘጋና  የአገልግሎት መስጫ ተቋማትን የሚያቋርጥ ከሆነ በነዋሪው ላይ የሚፈጥረው አሉታዊ ተጽዕኖ ከፍተኛ ነው፡፡

መንግሥት የሕግ የበላይነትን ማስከበርና  የሕዝቡ ቅሬታ መስማት እንዳለበት አመልክተዋል፡፡

ምንጭ፦ ENA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
መደበኛ ሎተሪ!!

1611 ኛው #መደበኛ_ሎተሪ ሐሙስ ታህሳስ 4 /2011 ዓ.ም በብሔራዊ ሎተሪ ዕድል አዳራሽ ከምሽቱ 12፡00 ሰዓት ላይ በህዝብ ፊት ወጥቷል፡፡
በዚህም መሰረት የወጡት የአሸናፊ ዕጣ ቁጥሮች እንደሚከተሉት ሆነዋል፡፡

1ኛ. 600,000 ብር የሚያስገኘው የ1ኛ ዕጣ ቁጥር 110749

2ኛ. 300,000 ብር የሚያስገኘው የ2ኛ ዕጣ ቁጥር 078905

3ኛ. 150,000 ብር የሚያስገኘው የ3ኛ ዕጣ ቁጥር 129287

4ኛ. 60,000 ብር የሚያስገኘው የ4ኛ ዕጣ ቁጥር 104306

5ኛ. 30,000 ብር የሚያስገኘው የ5ኛ ዕጣ ቁጥር 228690

6ኛ. 6ኛ ዕጣ 3 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 1,200 የሚያስገኙት ዕጣ ቁጥሮች 099058፣ 013909 እና 073560

7ኛ. 7ኛ ዕጣ 3 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 600 የሚያስገኙት ዕጣ ቁጥሮች 160897፣ 105369 እና 073270

8ኛ. 8ኛ ዕጣ 34 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር150 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር 2014

9ኛ . 9ኛ ዕጣ 34 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 120 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር 2940

10ኛ. 10ኛ ዕጣ 34 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 90 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር 8933

11ኛ. 11ኛ ዕጣ 340 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 60 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር 569

12ኛ. 12ኛ ዕጣ 340 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 45 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር 445

13ኛ. 13ኛ ዕጣ 3400 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 30 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር 43

14. 14ኛ 34,000 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 15 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር (የማስተዛዘኛ ዕጣ) ደግሞ ቁጥር 1 በመሆን ወጥቷል፡፡

አስተዳደሩ በወጡት ዕጣ ቁጥሮች ዕድለኛ ለሆኑ እንኳን ደስ ያላችሁ ብሏል። ዜናውን ጓደኞቻችሁ በማጋራት (share በማድረግ) ለሌሎች እንዲደርስ ታደርጉ ዘንድ በትህትና እ ንጠይቃለን!

የብሔራዊ ሎተሪ አስተዳደር
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የስደተኞች ጉዳይ...‼️

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጥር 9፣ 2011 ዓ. ም. ማለዳ ባደረገው አስራ ዘጠነኛ #መደበኛ ስብሰባ፤ #የስደተኞች_ጉዳይ ረቂቅ አዋጅን በአብላጫ ድምፅ አፅድቋል።

አዋጁ በተለያየ ምክንያት ወደ ኢትዮጵያ ለሚመጡ ስደተኞች ልዩ ልዩ መብቶችን በማጎናፀፍ፤ ኢትዮጵያ ለምታስተናግዳቸው ስደተኞች የምታደርገውን እንክባካቤ ያስቀጥላል ተብሏል። አዋጁ በሦስት ተቃውሞና በአንድ ተዓቅቦ ፀድቋል።

በአዋጁ መሠረት ዕውቅና ያገኙ ስደተኞች ከመንቀሳቀስ መብት በተጨማሪ ትምህርትና ሥራ የማግኘት መብት ይኖራቸዋል።

ኢትዮጵያ በመቶ ሺህዎች የሚቆጠሩ ስደተኞች የሚገኙባት ስትሆን፤ ይህም በርካታ ስደተኞችን ከተቀበሉ የአፍሪካ አገራት ከቀዳሚዎቹ ተርታ ያስመደባታል።

"በኢትዮጵያዊያን ሥራ ፈላጊዎች ላይ ተጨማሪ ፈተና ይደቅናል። ስደተኞችን የሚያስተናዱ የክልል መንግሥታት አልተማከሩበትም" የሚሉ ነቀፌታዎችን አዋጁ ላይ የሰነዘሩ የሕዝብ እንደራሴዎች ነበሩ።

አዋጁን የተመለከተ ማብራሪያ ሲሰጡ የነበሩት የሕግ፣ የፍትሕ እና ዲሞክራሲ ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ፎዚያ አሚን፤ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሁሉም ኢትዮጵያዊያን ወኪል በመሆኑ፤ በጉዳዩ ላይ መወያየቱ የሕዝቦችን ድምፅ እንዳስተናገደ እንደሚቆጠር ተናግረዋል። በተጨማሪም በረቂቅ አዋጁ ላይ ሕዝባዊ ምክክሮች መደረጋቸውን አስረድተዋል።

በአዋጁ መሠረት፤ ስደተኞች ለውጭ አገር ዜጎች የተፈቀዱ የሥራ መስኮች ላይ የመሰማራት ዕድል የሚኖራቸው ሲሆን፤ ይህም የኢትዮጵያዊያንን ዕድል የሚነጥቅ ሳይሆን ክፍተትን የሚሞላ ይሆናል ተብሏል።

ከማርቀቅ እስከ ማስፀደቅ ከሁለት ዓመታት በላይ ጊዜ ወስዷል የተባለው አዋጅ፤ በዓለም አቀፍ ትብብር በሚቀረፁ ላይ ሰባ መቶ የሚሆነውን ድርሻ ኢትዮጵያዊያን እንዲይዙት ተደርጎ፤ የቀረውን ብቃት ባላቸው ስደተኞች እንዲያዝ የሚያስችል ይሆናል።

ለስደተኞች ክፍት ይሆናሉ ተብለው ከሚጠበቁት እና ኢትዮጵያ ከዓለም አቀፍ አጋሮቿ ጋር በጋራ ከምትከውናቸው ፕሮጀክቶች መካከል የኢንዱስትሪ ፓርኮች እና የመስኖ ልማቶች ይገኙበታል።

ምንጭ፦ BBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#Italy

በሮም የኢፌዴሪ ሚሲዮን በኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ምክንያት ከ03/07/2012 ዓ/ም ጀምሮ በሳምንት ሁለት (2) ቀን ብቻ ተወስኖ የቆየው የቆንስላ አገልግሎት ከ10/09/2012 ዓ/ም ጀምሮ #መደበኛ ስራውን የሚጀምር መሆኑን ገልጿል። የሚደረጉ እንቅስቃሴዎች ከአስፈላጊ ጥንቃቄ ጋር እንዲሆንም #ማሳስቢያ ተሰጥቷል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ለኣክሱም ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ፦

ለኣክሱም ዪኒቨርስቲ ኤክስቴንሽን /ኢ- መደበኛ/ እንዲሁም መደበኛ የሁለተኛ ድግሪ (ማስተርስ) ተማሪዎች ት/ት የሚጀሙሩበት ቀን ጥሪ አቀረበ።

- ለነባር ወይም ስንየር የኤክስተንሽን(ኢ-መደበኛ) ድግሪ ተማሪዎች ከመጋቢት 11/2013ዓ/ም ጀምሮ እንዲገቡ ጥሪ ያቀረበ ሲሆን፤

- ከመጋቢት 15 -16/2013ዓ/ም ባለው ጊዜ ለሁሉም #መደበኛ# የሁለተኛ ዲግሪ(ማስተርስ) ተማሪዎች የአንደኛ ሴሚስተር ኖርማል ምዝገባ ይካሄዳል።

- ለሁሉም የኤክስተንሽን (ኢ-መደበኛ) ማስተርስ ተማሪዎች ከመጋቢት 18-19/2013ዓ/ም ባለው ጊዜ የአንደኛ ሴሚስተር ኖርማል ምዝገባ ያደርጋሉ።

(ጌታቸው ካሕሱ /የአክሱም ዩኒቨርስቲ አዲስ አበባ ጉዳይ ማስፈፀሚያ ጽ/ቤት ሃላፊ)

@tikvahethiopia
#MoE

ትምህርት ሚኒስቴር ፤ በትግራይ ክልል በሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች ይማሩ የነበሩና በሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች ተመድበው ለተመረቁ ተማሪዎች #መደበኛ_ዲግሪ ለመስጠት እንደሚቸገር አሳውቋል፡፡

በትግራይ ክልል በሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች ይማሩ የነበሩና በሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች ተመድበው ትምህርታቸውን ያጠናቀቁ ከአራት ሺህ በላይ ተማሪዎች መደበኛ ዲግሪ ማግኘት ባለመቻላቸው ሥራ ለመቀጠር መቸገራቸውን ይገልጻሉ።

በተማሪዎቹ ቅሬታ ዙሪያ በሪፖርተር ጋዜጣ የተጠየቁት የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) " የተማሪዎቹ ሙሉ መረጃ ሳይገኝ መደበኛ ዲግሪ ለመስጠት እንደሚቸገሩ " ገልጸዋል።

" ሰላምና መረጋጋት በሰሜን ኢትዮጵያ በአስተማማኝ ሁኔታ ሲሰፍን ከመጡባቸው ዩኒቨርሲቲዎች ትምህርት ያቆሙበት መረጃ ተሟልቶ ሲቀርብ ዲግሪው ይሰጣቸዋል " ሲሉ አክለዋል፡፡

እስከዚያው ግን በተሰጣቸው ጊዚያዊ ሰርተፊኬት ሥራ መፈለግ እንደሚችሉ ነው ሚኒስትሩ የተናገሩት።

በትግራይ ክልል ከሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች ተፈናቅለው በሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች ትምህርታቸውን ያጠናቀቁት ተማሪዎች ግን " ትምህርት ሚኒስቴር በአንድ ሴሚስተር የውጤት መግለጫ ወረቀት/Grade Report አሰናብቶናል " ሲሉ ቅሬታቸውን አሰምተዋል፡፡

ይህ ወረቀት በሥራ ዓለም ተወዳዳሪ ሆኖ ለመቀጠር እንደማያስችላቸው በመጥቀስ ሚኒስቴሩ ዘላቂ መፍትሄ እንዲፈልግላቸው ጠይቀዋል፡፡

@tikvahuniversity @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
ከቲክቫህ ቤተሰብ አባላት ፦

(የፀጥታ ጉዳዮች)

ከቀናት ለፊት በኦሮሚያ ክልል የሚገኙ ቤተሰቦቻችን በተለይ በወለጋ አካባቢዎች በፀጥታ ችግር ከፍተኛ ችግር እያጋጠማቸው መሆኑን ፣ በተለያዩ ቦታዎች ላይ ባሉ ችግሮች ንፁሃንን ሰለባ እየሆኑ እንደሚገኙ ፣ ሚማሩበት ዩኒቨርሲቲ የጠራቸው ተማሪዎች መንገድ በመዘጋቱ በእግር ለመጓዝ እንደተገደዱ መግለፃቸው አይዘነጋም።

በእርግጥ በኦሮሚያ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች ላይ ያለው የፀጥታ ችግር ዘላቂ እና አስተማማኝ መፍትሄ ሳያገኝ የበርካታ ንፁሃንን ህይወት እየቀጠፈ እንሆ አመታት አልፈዋል ፤ አሁንም ቀጥሏል ፤ በፀጥታ ችግሩ ሳቢያ ኢኮኖሚው ተጎድቷል፣ ገበሬዎች ማረስ እንዳችሉ ሆነዋል በርካቶች የሰው እጅ ጠባቂ ሊሆኑ ተገደዋል።

ከሰሞኑን ደግሞ የፀጥታ ችግሩ እስከ ትልቋ የነቀምቴ ከተማ ደርሶ ነበር።

ባለፈው እሁድ ዕለት በከተማይቱ መንግስት 'ሸኔ' ሲል በሽብርተኝነት የፈረጀው እራሱን የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት እያለ የሚጠራው ታጣቂ ቡድን ወደ ከተማይቱ ዘልቆ በመግባት ከመንግስት የፀጥታ ኃይል ጋር #የተኩስ ልልውጥ አድርጎ ነበር።

በዕለቱ የደረሱ ጉዳቶች ስለመኖራቸው (ትክክለኛውን ለመግለፅ ቢያስቸግርም) ፣  ነገር ግን ሁኔታውን የፀጥታ ኃይሉ መቆጣጠር እንደቻለ ከቤተሰቦቻችን ተገልጾልናል።

ይህን ያህል በትልቅ ከተማ ውስጥ የተኩስ ልውውጥ እስኪደረግ የፀጥታና ደህንነት ኃይሉ ምን ይሰራ ነበር የሚለው " ትልቁ ጥያቄያቸው " እንደሆነ ቤተሰቦቻችን ነግረውናል።

የነቀምቴ ከተማ አስተዳደር ለማህበረሰቡ እና ለመላ ለአገልግሎት ሰጪዎች ባሰራጨው አጭር መልዕክት ፤ በቅርቡ ነቀምቴ ከተማ ውስጥ በሸኔ ቡድን የፀጥታ ችግር ተፈጥሮ እንደነበር ገልጾ ችግሩ በፀጥታ ኃይሉ ቅንጅት ፣ በከተማው ህዝብ ተሳትፎ እንዲረጋጋ መድረጉን አመልክቷል።

ነቀምቴ ከተማ አሁን ላይ ሰላም በመሆኗ መንግስታዊ እና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ፣ የአገልግሎት ሰጪዎች (የትራንስፖርት ፣ ባንክ ...የመሳሰሉ) ወደ ስራ ተመልሰው አገልግሎት እንዲሰጡ የከተማው አስተዳደር አሳስቧል።

                                 --------

በአ/አ - ሀዋሳ ፈጣን መንገድ ላይ " መቂ " አካባቢ ምንድነው የሆነው ?

ከትናንትና በስቲያ ምሽት 2 ሰአት አከባቢ ከአ/አ ወደ ሃዋሳ በሚወስደው ፈጣን መንገድ ላይ መቂ አከባቢ ሲጓዙ በነበሩ ተሳፋሪዎች ላይ በታጣቂዎች ተኩስ ተከፍቶ የሰዎች ህይወት ስለማለፉ አንድ የቤተሰባችን አባል ገልጿል።

ይህንን ክስተት የገለፀው የሻሸመኔ፤ ቲክቫህ ቤተሰብ አባል ታጣቂዎች በከፈቱት ተኩስ " ወንድም እና እህት መሞታቸውን አረጋግጫለሁ " ብሏል።

በወቅቱ ከተሳፋሪዎቹ አንዷ የእሱ #እህት እንደነበረች በመግለፅ በጥቃቱ ሳቢያ የቆሰሉ ሰዎች እንደነበሩ አመልክቷል።

ሟቾቹ የሻሸመኔ ከተማ 04 ቀበሌ ውሃ ልማት አካባቢ ነዋሪዎች እንደሆኑ ጠቁሟል።

የኸው ቤተሰባችን በዚያው ሰአት ከአዲስ አበባ እቃ ጭነው ሲመጡ የነበሩ ተሽከርካሪዎች መቃጠላቸውን እንደሰማ ገልጿል።

እስካሁን በዚህ ጉዳይ ከመንግስት በኩል የተባለ ነገር የለም።
 
                                 --------

በአሶሳ ምንድነው ያለው ?

" አሶሳ ፍፁም ሰላም ነች "

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ዋና ከተማ አሶሳ ከተማ ከሀሙስ ከሰአት ጀምሮ ኔትዎርክ፣ ሲስተም ፣ መብራት ጠፍቶ ነበር።

ትላንት ከሰዓት ኔትወርክ / ሲስተም የተመለሰ ሲሆን ይህ መልዕክት እስከተላከበት ሰዓት መብራት የለም።

አንድ የአሶሳ የቤተሰባችን አባል በላከው መልዕክት ፤ " ስለጉዳዩ ከመንግስት በኩል የተነገረ ምክንያት የለም " ያለ ሲሆን " አሶሳ ከተማ ግን ባለፉት 6 ቀናት ከባንኮች መዘጋት በስተቀር  እጅግ ሰላማዊና መደበኛ የስራ እንቅስቃሴዎች አንዳሉ ናቸው። " ብሏል።

በኔትወርክ መጥፋት ምክንያት የተጨነቁ ቤተሰቦችም ሁሉም ነገር ሰላም ስለሆነ ጭንቀት እንዳይገባቸው መልዕክት አስተላልፏል።

ከሰሞኑን በኦሮሚያ ክልል " ምዕራብ ወለጋ " አካባቢ ካለው የፀጥታ ችግር ጋር በተያያዘ በአሶሳ ኔትዎርክ መቋረጡ ያሳሰባቸው በርካቶች ሲሆኑ አሶሳ ከተማና አካባቢው ላይ ኔትዎርክ ከመቋረጥ በዘለለ / አሁን ላይ ኔትዎርክ ተመልሷል / ሁሉም ነገር #ሰላም ነው።

በሌላ በኩል፦ በአሶሳ ዞን #ባንባሲ ወረዳ ከወቅታዊ የፀጥታ ሁኔታ ጋር በተያያዘ (ወረዳው የስጋት ቀጠና በመሆኑ ምክንያት) ከቀናት በፊት የታወጀው የሰዓት እላፊ ተግባራዊ እየሆነ ነው።

ለማስታወስ ያህል ፦

- እግረኞች ከምሽቱ 1፡00 ሰዓት ጀምሮ እስከ ንጋቱ 12፡00 ሰዓት ምንም እንቅስቃሴ ማድረግ አይችሉም።

- ሞተር ሳይክሎችና 3 እግር ተሽከርካሪዎች ከምሽቱ 1:00 - ንጋቱ 12:00 ሰዓት ምንም እንቅስቃሴ ማድረግ አይችሉም።

- ማንኛውም የአገልግሎት ሰጪ ተቋማት ሻይ ቡና፣ ምግብ ፣ ሪስቶራንት፣ መጠጥ ቤቶች እና ወ.ዘ.ተ ከምሽቱ 1:00 ሰዓት ጀምሮ እስከ ንጋቱ 12:00 ሰዓት ድረስ ምንም ዓይነት እንቅስቃሴ ማድረግ አይችሉም።

በተጨማሪ ፦ ማንኛውም የጸጥታ አካል ከተመደበው #መደበኛ_ሠራዊት_ውጪ የተጣለውን የሰዓት እላፊ ገደብ አልፎ ሲንቀሳቀስ ከተገኘ በቁጥጥር ስር ይውላል።

@tikvahethiopia
" በነዚህ ወጣቶች ያለጊዜ ሕልፈት የተሰማኝን ሐዘን ገልፃለሁ "  - ወ/ሮ መዓዛ አሸናፊ

ከትላንት በስቲያ ታህሳስ 10 /2015 በመዲናችን አዲስ አበባ አንድ የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት ዳኛ አብራው የምትኖረውን እጮኛውን በአሰቃቂ ሁኔታ ከገደለ በኃላ እራሱን ከ13ኛ ፎቶ ወርውሮ (መገናኛ አምቼ ፊት ለፊት ባለዉ የፌደራል ዳኞች መኖሪያ ጊቢ) ህይወቱን ማጥፋቱ በርካቶችን አሳዝኗል የመዲናይቱም መነጋገሪያ ሆኗል።

ዳኛው ትንሳኤ በላነህ የሚባል ሲሆን በዕለቱ እራሱን ከ13 ፎቅ ላይ ወርውሮ ከማጥፋቱ በፊት አብራዉ የምትኖረዉን እጮኛውን ህይወት አጥፍቷል።

ህይወቱ ከማለፉ ከሰዓታት በፊትም በ " ፌስቡክ ገፁ " ላይ ፅፎታል የተባለ አንድ መልዕክትም በማህበራዊ ሚዲያ እየተዘዋወረ የብዙሃን መነጋገሪያ ሆኗል።

ይህን ጉዳይ በተመለከተ የጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕ/ት ወ/ሮ መአዛ አሸናፊ ፤ ክስተቱ በጣም አሳዛኝ መሆኑን ገልፀዋል።

" ባልተጠበቀ ሁኔታ እጮኛቸውን በመግደል ራሳቸውን ያጠፉት የፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት ዳኛ ተንሳይ በላይነህ ሞት በጣም አሳዛኝ ነው " ያሉት ወ/ሮ መዓዛ አሸናፊ ፤ " ዳኛው #መደበኛ_ያልሆነ ጠባይ ያሳዩ እንደነበረ ይህ ሁኔታ ከተከሰተ በኃላ ተጠቁሟል " ሲሉ ገልፀዋል።

" የዘርፉ ባለሙያዎች እንደሚሉት መደበኛ ሥራ መሥራት የሚችሉ ሰዎች ሥራቸውን እያከናወኑ አንዳንድ ጊዜ የአእምሮ ጤንነት ችግር ሊኖርባቸው ይችላል ፤ " ያሉት የጠቅላይ ፍ/ቤት ፕሬዜዳንቷ " እንዲህ አይነት ሁኔታዎች ሲታዩ እገዛ ሊያደርግ ለሚችል ክፍል ማሳወቅ አስፈላጊ ነው " ብለዋል።

በወጣቶቹ ያለጊዜ ሕልፈት ሐዘን እንደተሰማቸው የገለፁት ወ/ሮ መዓዛ ለቤተሰቦቻቸውና ለወዳጅ ዘመዶቻቸው መጽናናትን ተመኝተዋል።

@tikvahethiopia