TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
" ... ትግራይ ክልልም የክልሉን ግዛት እና ህዝቡን ለመጠበቅ በቂ የፖሊስ ኃይል፣ በቂ ልዩ ኃይል ፣ በቂ ሚሊሻ ይኖረዋል " - አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን

የጠቅላይ ሚኒስትሩ የብሄራዊ ደህንነት አማካሪ አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ቅዳሜ ለዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ የሰላም ስምምነት በተመለከተ ማብራሪያ በሰጡበት ወቅት " ህወሓት "ን ትጥቅ ስለማስፈታት እና በትግራይ ክልል ውስጥ ምርጫ ተከናውኖ የክልል መንግስት የሚመሰርተው አካል ክልሉን ለመጠበቅ መሳሪያ የመታጠቅ መብቱን በመጠቀም ረገድ ላይ ግርታ ሊኖር እንደማይገባ አስረድተዋል።

አምባሳዳር ሬድዋን በትግራይ በምርጫ ስልጣን የሚይዘው አካል ልክ እንደ ሌሎቹ ክልሎች በቂ የፀጥታ ኃይል እንደሚያደራጅ አረጋግጠዋል። 

መንግስት ህወሓት በሽብርተኝነት የተፈረጀበትን ድንጋጌ መልሶ እንዲመለከተው ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንደሚያቀርብም አምባሳደር ሬድዋን ጠቁመዋል። 

አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ከትጥቅ ማስፈታት ጋር በተያያዘ የተናገሩት ፦

" ህወሓትን ትጥቅ ማስፈታት ብለን ስንናገር እና የትግራይ ክልል የፀጥታ ኃይል ያደራጃል ስንል ወዳጆቻችን ግርታ ሊገባቸው ይችላል።

ክልሎች የራሳቸው #የተመጠነ የፀጥታ ኃይል አላቸው ትግራይ ክልልም የክልሉን ግዛት እና ህዝቡን ለመጠበቅ በቂ የፖሊስ ኃይል፣ በቂ ልዩ ኃይል ፣ በቂ ሚሊሻ ይኖረዋል ከዚህ ጋር ነው መታየት ያለበት።  አሁንም ደግሜ የምለው ግን ይህ የሚሆነው ለትግራይ ክልላዊ መንግስት እንጂ ለአንድ የፖለቲካ ፓርቲ አይደለም። "

Credit : Journalist Solomon Muchie / ዶቼ ቨለ

@tikvahethiopia