TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update የብሄር ብሄረሰቦች ቀን⬇️

የዘንድሮ የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች በዓል #የተራራቁና #የተኳረፉ ሕዝቦችን በማስታረቅና በማቀራረብ #ይከበራል ተባለ፡፡

የበዓሉን አከባበር አስመልክቶ የፌዴሬሽን ምክር ቤትና የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በጋራ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡

የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ኬሪያ ኢብራሂም በዓሉ እስካሁን ሲከበርበት የቆየው መንገድ የተለያዩ #ክፍተቶች እንዳሉበት በጥናት #ተረጋግጧል ብለዋል፡፡

በሕዝቦች መካከል የቆየውን አብሮ የመኖር፣ የመቻቻልና የመከባበር እሴቶች ከማስጠበቅ አንፃር ክፍተቶች ነበሩ ብለዋል፡፡

አሁን ኢትዮጵያ ላይ እየታየ ያለው ሁኔታም ለዚህ ማሳያ ነው ያሉት አፈ ጉባኤዋ የብሔር ማንነትንና ኢትዮጵያዊነትን በማጣመር የዘንድሮውን በዓል ለማክበር ዝግጅት መደረጉን ተናግረዋል፡፡

ሰው በብሔሩ ብቻ የሚፈናቀልበት፣ የሚጠቃበትና የሚገደልበት ጊዜ ላይ ደርሰናል ያሉት አፈ ጉባኤዋ በኢትዮጵያ ሕዝቦች መካከል መጠራጠርና አለመተማመን ተፈጥሯል፣ በህብረተሰቡ ውስጥም በርካታ ቁስል አለ ብለዋል፡፡

የዘንድሮ በዓል የተራራቁ የሚቀራረቡበትና ለመፃኢ የጋራ ተስፋቸው የሚተባበሩበት መንገድ የሚታሰብበት ሆኖ እንደሚከበር ተናግረዋል፡፡

በተለይም የጎላ ግጭት ባለባቸው አካባቢዎች በጥናት ላይ የተመሰረተ የሰላምና የማረጋጋት ስራ ይሰራል ብለዋል፡፡

ባህላዊ፣ ሃይማኖታዊና ሳይንሳዊ የግጭት አፈታት ዘዴዎችን በመጠቀም ዘላቂነት ያለው ሰላም ለመፍጠር ከወዲሁ ስራዎችን ጀምረናል ማለታቸው ተሰምቷል፡፡

ለ13ኛ ጊዜ የሚከበረው የዘንድሮ የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በአዲስ አበባ አስተናጋጅነት ይካሄዳል፡፡

በበዓሉ ዝግጅት ወጣቶችና የኪነ ጥበብ ሰዎች እንደሚሳተፉ የተናገሩት ምክትል ከንቲባ ታከለ ኡማ የከተማ አስተዳደሩ እለቱን የኢትዮጵያውያን ቀን አድርጎ ያከብራል ብለዋል፡፡

ለበዓሉ አከባበር የሚወጣው ወጪም ለወጣቶች የስራ እድል ፈጠራ የሚውል ሲሆን ድግስ የማይበዛበት ዝግጅት ይደረጋል ብለዋል፡፡

የዘንድሮ የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች በዓል በብዝሃነት የደመቀ ኢትዮጵያዊነት በሚል መሪ ቃል ይከበራል፡፡

ምንጭ፦ ሸገር 102.1
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#DrLiaTadesse

በሀገራችን ባለፉት 7 ቀናት ብቻ 848 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ እንደተያዙ እንዲሁም 16 ሰዎች ከኮሮና ቫይረስ ጋር በተገናኘ ህይወታቸው ማለፉን ዶክተር ሊያ ታደሰ አሳውቀዋል።

ነገር ግን በሕብረተሰቡ ዘንድ አሁንም በሽታውን ለመከላከል የሚረዱ የመከላከያ ዘዴዎች ከመተግበር አኳያ እጅግ ብዙ #ክፍተቶች እየተስተዋሉ መሆኑን ገልፀዋል።

ዶክተር ሊያ ሁሉም የሕብረተሰብ አካል፣ ክልሎች ፣ የከተማ አስተደሮችና የሚመለከታቸው ሴክተር መስሪያ ቤቶችና ሌሎች አካላት የበሽታው ስርጭት ተስፋፋቶ ከአቅም በላይ ከመድረሱ እና ለከፋ ችግር ከመዳረጋችን በፊት የጉዳዩን አሳሳቢነት በመረዳት ከምንጊዜውም በላይ ሕብረተሰቡን ባማከል እና ባሳተፈ መልኩ አስፈላጊውን የመከላከል ስራ እንዲተገብሩ #በአፅንኦት አሳስበዋል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update የ2014 የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና የማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች የሁለተኛ ቀን የፈተና መርሀ ግብር እየተካሄደ ይገኛል። ይኸው የፈተና መርሀ ግብር ዛሬ ከሰዓት በኃላም ይቀጥላል። እንደ ትምህርት ሚኒስቴር የፈተና መርሀግብር የማህበራዊ ሳይንስ ፈተና ነገ ጥቅምት 2 / 2015 የሚጠናቀቅ ሲሆን ተማሪዎች ከጥቅምት 3 እስከ ጥቅምት 4 ወደየአካባቢያቸው ይመለሳሉ። በሌላ በኩል ፤ ትላንት…
#Update

የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና የማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች #የመጨረሻ ቀን የፈተና መርሀ ግብር በመካሄድ ላይ ይገኛል።

ዛሬ ፈተናቸውን የሚያጠናቅቁት ተማሪዎች ከነገ ጀምሮ ወደየመጡበት አካባቢ የሚደረጉ ይሆናል።

የ2014 ዓ/ም የ12ኛ ክፍል ፈተና በዩኒቨርሲቲዎች እንዲሰጥ ከመደረጉ በላይ አንዳንድ ተቋማት ኩረጃን ለመከላከል ከመጀመሪያው ቀን አንስቶ የደህንነት ካሜራዎችን ሲጠቀሙ እንደነበር ለማውቅ ተችሏል።

የደህንነት ካሜራዎችን ተማሪዎች በግቢ ውስጥ ያላቸውን እንቅስቃሴ እና በፈተና ክፍል ያለው የፈተና ስርዓት ለመከታተል ነው ጥቅም ላይ እያዋሉ ያሉት።

ዘንድሮ ከታዩ በጎ በጎ ጅምሮች በተጨማሪ እንደ መጀመሪያ ጊዜም ስለሆነ #ክፍተቶች የነበሩ ሲሆን እነዚህን በቀጣይ የምናነሳቸው ይሆናል።

ትምህርት ሚኒስቴርም ፈተና እንዳለቀ አጠቃላይ የነበሩ አፈፃፀሞችን ላይ መግለጫ እንደሚሰጥ ተነግሮናል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ ግን ፤ ተፈታኝ ተማሪዎች ፈተናቸውን እንዳይፈተኑ እና ጥለው እንዲወጡ የሚያበረታቱ የተለያዩ አክቲቪስት ነን የሚሉ አካላት ፣ የማህበራዊ ትስስር ገፆች መኖራቸውን ተመልክተናል።

የተማሪዎችን ህይወትን የፖለቲካ ቁማር መጫወቻ ለማድረግ የሞከሩም ብዙ ናቸው ፤ ድርጊቱ በነገ የሀገር ተረካቢ ልጆች ላይ ትልቅ ተፅእኖ ስላለው ቢታታረም መልካም ነው።

ገና ፈተናቸውን ያልወሰዱና ወደ መፈተኛ ተቋማት የሚገቡ በርካታ ተማሪዎች በመኖራቸው ያሉ ክፍተቶች እንዲታረሙ ለማደረግ መረባረብ እንጂ ማህበራዊ ሚዲያን በመጠቀም ተማሪዎችን መረበሽ ፍፁም ተገቢ አይደለም።

ፎቶ ፦ አርሲ ዩኒቨርሲቲ እና ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ

@tikvahethiopia