TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ድርድር

መንግሥት " ኦነግ ሸኔ " እያለ የሚጠራው የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት አዛዥ መሮ ዲሪባ ፥ የታጠቂ ቡድኑን ከፌደራል መንግሥቱ ጋር የሚያደራድር ሦስተኛ አካል መኖሩን ለቢቢሲ በሰጡት ቃል አረጋግጠዋል።

ጃል መሮ አደራዳሪዎቹ እነማን እንደሆኑ በስም ከጥቀስ ተቆጥበዋል።

መሮ ዲሪባ ታጣቂ ቡድኑን ወክለው ከመንግሥት ጋር የሚደራደሩ የልዑክ ቡድን አባላት ወደ #ታንዛኒያ ጉዞ እያደረጉ ስለመሆኑ አሳውቀዋል።

መሮ ዲሪባ ይህ ንግግር በታንዛኒያዋ ራስ ገዝ ግዛት በሆነችው #ዛንዚባር ደሴት ላይ እንደሚከናወን ገልጸው፤ " የጥይት ድምጽ ሳይሰማ የኦሮሞ ሕዝብ ጥያቄ መልስ የሚያገኝ ከሆነ በራችን ሁሌም ክፍት ነው " ሲሉ ተናግረዋል።

መሮ ፥ በቅርቡ ኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት እና መንግሥት ሦስተኛ ወገን ባለበት በኬንያ ለመነጋገር ቀጠሮ ይዘው የታጣቂ ቡድኑ ተወካዮች በቦታው ቢገኙም የመንግሥት ተወካዮች ግን ሳይገኙ ቀርተዋል ብለዋል።

" በሌሎች አገራት ግብዣ በኬንያ ለመገናኘት ቀጠሮ ነበር። ነገር ግን መንግሥት ሳይገኝ ቀረ "  ያሉት መሮ " በአሁኑ ድርድር ስኬት ላይ ጥርጣሬዎች ቢኖረንም የንግግር ሂደቱ ሰላም ሊያመጣ ይችላል የሚል ተስፋ አለኝ " ሲሉ ተናግረዋል።

" ንግግር መጀመሩ ጥሩ ነው። መነጋገር እና መፍታት ያለብን ብዙ ነገሮች ስላሉ ጉዳዩ በአንድ ጊዜ የሚጠናቀቅ አይሆንም " ሲሉ አክለዋል።

ከዚሁ ድርድር ጋር በተያያዘ ቢቢሲ የኢትዮጵያ መንግሥት ከታጣቂ ቡድኑ ጋር በሚደረገው ንግግር ፦
- የስዊድን፣
- የኖርዌይ፣
- የኬንያ፣
- የአውሮፓ ኅብረት እና የአሜሪካ ዲፕሎማቶች እንደሚገኙ ሁለት ስማቸው እንዲገለፅ ያልፈለጉ ምንጮች እንደገለፁለት ዘግቧል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ድርድር ጠ/ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ስለ #ድርድር ምንድነው ያሉት ? " ከኦነግ ሸኔ ጋር የሚደረገው ድርድር ከነገ ወዲያ በታንዛኒያ ይጀመራል። ይህንን ድርድር የኢትዮጵያ መንግሥት እና ህዝብ አብዝቶ ይፈልገዋል። በዚህ ድርድር የሚሳተፉ ወገኖች ሁሉ የዛሬዋን ቀን እያሰቡ ፣ ከግጭት፣  ከጦርነት እንደማናተርፍ አውቀው ህግ እና ስርዓት ተከትለን ይቅር ተባብለን ሀገራችንን በጋራ ማነፅ እና መገንባት…
#ታንዛኒያ

የኢትዮጵያ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ዛሬ #ታንዛኒያ ገብተዋል።

አቶ ደመቀ በ4 የአፍሪካ ሀገራት ጉብኝት ያደርጋሉ የተባለ ሲሆን የመጀመሪያውን ጉብኝታቸውን በታንዛኒያ ጀምረዋል።

ከታንዛኒያ በመቀጠል በኮሞሮስ ፣ ቡሩንዲ እና ዩጋንዳ ጉብምት ያደርጋሉ ተብሏል።

አቶ ደመቀ ዛሬ ታንዛኒያ ከገቡ በኃላ #በዛንዚባር የሚገኘውን የአፄ ኃይለሥላሴ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤትን ጎብኝተዋል።

አቶ ደመቀ መኮንን ወደ ታንዛኒያ ለጉብኝት ያመሩት ትላንት የኢፌዴሪ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ " ኦነግ ሸኔ " ሲሉ ከተጠሩት የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት ጋር መንግሥት ነገ በታንዛኒያ ድርድር እንደሚጀምር ካሳወቁ በኃላ ነው።

አቶ ደመቀ የታንዛኒያ ጉዟቸው በ4 የአፍሪካ ሀገራት ለሚያደርጉት ጉብኝት የመጀመሪያ ሀገር ከመሆኑ በዘለለ ይደረጋል ከተባለው ድርድር ጋር ይገናኝ እንደሆነ ወይም በዚህ ድርድር ላይ ይገኙ/አይገኙ የታወቀም ሆነ ይፋ የተደረገ መረጃ #የለም

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update የኢትዮጵያ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ እና የኬንያው ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ የጋራ መግለጫ ምን ይላል ? የጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ የኬንያ ያስራ ጉብኝትን እና ከፕሬዜዳንት ዊሊያም ሩቶ ጋር ያደረጉትን ምክክር ተከትሎ የኬንያ " ስቴት ሀውስ " የጋራ ነው ያለውን መግለጫ ዛሬ ምሽት አውጥቷል። በዚህም መግለጫ ፤ ፕሬዚዳንት ሩቶ እና ጠ/ሚ ዶ/ር ዐብይ ከአፍሪቃ ቀንድ ደህንነት…
#ኢትዮጵያ #ኬንያ #ታንዛኒያ

በኬንያ ናይሮቢ ለ2 ቀን የስራ ጉብኝት ያደረጉት የኢትዮጵያ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ዛሬ ደግሞ ወደ ታንዛኒያ አቅንተዋል።

በታንዛኒያ የሶስት ቀን የስራ ጉብኝት ያደርጋሉ ተብሏል።

በሌላ በኩል ደግሞ ፤ የኢትዮጵያ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ በኬንያ ይፋዊ የሥራ ጉብኝት ማድረጋቸው ተነግሯል።

ኢታማዦር ሹሙ ፤ ከኬንያው አቻቸው ጄኔራል ፍራንሲስ ኦሞንዲ ኦጎላ ጋር የሁለቱን ሀገራት ትስስር ይበልጥ ማጠናከር በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ መምከራቸው ተገልጿል።

በወታደራዊ መሪዎቹ መካከል በተካሄደ ውይይት የቀጣናውን ደህንነት ማስጠበቅ፣ የመከላከያ ትብብር እና የጋራ ስልጠና ልምምዶችን ማሳደግ የሚሉት ተነስተዋል ተብሏል።

@tikvahethiopia
በምስራቅ አፍሪካዊቷ ሀገር #ታንዛኒያ ለሳምንታት በዘለቀ ከባድ ዝናብ ምክንያት በተከሰተ የጎርፍ አደጋ እና የመሬት መንሸራተት 155 ሰዎች ሲሞቱ ፤ 236 ሰዎች ደግሞ የተለያየ መጠን ያለው ጉዳት እንደደረሰባቸው የሀገሪቱ ጠ/ሚ ቃሲም ማጅዋሊ ተናግረዋል።

በዚህ ሳምንት በጎረቤት #ኬንያ በደረሰው የጎርፍ አደጋ በትንሹ 35 ሰዎች መሞታቸው ተነግሯል። 40,000 ሰዎች  ደግሞ ከቤታቸው እንዲፈናቀሉ ሆነዋል።

@tikvahethiopia