TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update አምባሳደር ማይክ ሐመር ኬንያ ይገኛሉ። የኬንያ ፕሬዜዳንት ዶ/ር ዊሊያም ሩቶ ከአሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ አምባሳደር ማይክ ሐመር ጋር ተነጋግረዋል። ፕሬዜዳንት ሩቶ ከአሜሪካው አምባሳደር ሐመር ጋር ያደረጉትን ንግግር ተከትሎ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ፤ " ሰላምና መረጋጋት ለአገሮች ልማትና ብልፅግና የግድ አስፈላጊ ነው " ያሉ ሲሆን ኬንያ ፤ አሜሪካ በአፍሪካ ቀንድ በተለይም…
#Update

አምባሳደር ማይክ ሐመር ኢትዮጵያ ይገኛሉ።

የአሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛው አምባሳደር ማይክ ሐመር በአሁን ሰዓት ኢትዮጵያ የሚገኙ ሲሆን ከምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ጋር #ዛሬ ውይይት አካሂደዋል።

አቶ ደመቀ መኮን በውይይቱ ወቅት ፤ የኢትዮጵያ መንግስት በሰሜን ኢትዮጵያ የተፈጠረው ግጭት በሰላም እንዲፈታ ቁርጠኛ መሆኑን መግለፃቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያሳያል።

አምባሳደር ማይክ ሐመር በበኩላቸው፤ አሜሪካ በአፍሪካ ህብረት አደራዳሪነት ለሚካሄደው የሰላም ድርድር ድጋፏን አጠናክራ እንደምትቀጥል ገልፀዋል።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር " በውይይቱ ረጅም ዘመን ያስቆጠረውን የኢትዮጵያ እና አሜሪካ የሁለትዮሽ ግንኙነት ይበልጥ አጠናክሮ ለመቀጠል ተስማምተዋል " ሲል አሳውቋል።

አምባሳደር ማይክ ሐመር ከቀናት በፊት #ኬንያ እንደነበሩና ከኬንያው ፕሬዜዳንት ዶ/ር ዊሊያም ሩቶ ጋር መምከራቸው ይታወሳል።

አሜሪካ አምባሳደር ሐመርን ፤ በሰሜን ኢትዮጵያ ያለው ግጭት በአፋጣኝ እንዲቆም እና በአፍሪካ ህብረት የሚመራ የሰላም ድርድር እንዲጀመር ለመደገፍ ወደ ኬንያ ፣ #ደቡብ_አፍሪካ ፣ ኢትዮጵያ እንደላከች ማሳወቋ የሚዘነጋ አይደለም።

Photo Credit : Ministry of Foreign Affairs of Ethiopia

@tikvahethiopia
#ዋጋ

የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን ያለአገልግሎት የተከማቹ ቁርጥራጭ ብረታ ብረቶች፣ በስክራፕ መልክ የሚወገዱ ተሽከርካሪዎችና ማሽነሪዎችን መሸጫ የዋጋ ዝርዝር ይፋ ሆኗል።

1ኛ. ስቲል - የአንድ ኪሎ ማስረከቢያ ዋጋ (በብር)  64.00

2. ካስት አይረን  - የአንድ ኪሎ ማስረከቢያ ዋጋ (በብር) 51.75

3. አልሙኒየም - የአንድ ኪሎ ማስረከቢያ ዋጋ (ብር) 120.00

4. ስክራፕ ያደረገ ተሽከርካሪ / ማሽነሪ - የአንድ ኪሎ ማስረከቢያ ዋጋ (በብር) 51.25

5. ያገለገለ የተሽከርካሪ / ማሽነሪ መለዋወጫ - የአንድ ኪሎ ማስረከቢያ ዋጋ  (በብር) 51.25

በዚህ መሰረት መሰሪያ ቤቶች ቁርጥራጭ ብረታ ብረቶችን የማዕድን ሚኒስቴር ለሚመድብላቸው የብረታ ብረት አቅላጭ ኢንዱስትሪ/ለአምራች ኢንዱስትሪ #ብቻ በቀጥታ እንዲሸጡ ከሽያጭም የሚገኘውን ገንዘብ ወደ መንግስት ማዕከላዊ ግ/ቤት የባንክ አካውንት ገቢ እንዲያደርጉ ማሳሰቢያ ተሰጥቷል።

(ለተጨማሪ መረጃ ከላይ የተያያዙትን ደብዳቤዎች ይመልከቱ)

Credit : M. (Tikvah Family)

@tikvahethiopia
#AddisAbaba

ዶ/ር ቀነዓ ያደታ የአዲስ አበባ ከተማ የመሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ ሃላፊ ፤ ወ/ሮ ሊዲያ ግርማ  ደግሞ የሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ ሃላፊ ሆነው ተሾሙ።

ዛሬ 3ኛው የአ/አበባ ምክር ቤት 2ኛ አመት የስራ ዘመን 1ኛ መደበኛ ጉባኤው እያካሄደ ይገኛል።

በዚህም ጉባኤ በከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ አቅራቢነት ምክር ቤቱ የተለያዩ ኃላፊዎችን ሹመት አፅድቋል።

1. ዶ/ር ቀነዓ ያደታ - የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ ሃላፊ

2. አቶ ምትኩ አስማረ - የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትራንስፖርት ቢሮ ኃላፊ

3. ወ/ሮ ሊዲያ ግርማ - የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ ሃላፊ

4. ወ/ሮ ሃቢባ ሲራጅ - የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ቴክኖሎጂ ቢሮ ሃላፊ

5. ዶ/ር ጀማሉ ጀምበር - የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የህዝብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ኮሚሽን ኮሚሽነር

6. አቶ ጀማል ረዲ - የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር ሆነው ተሹመዋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#AddisAbaba ዶ/ር ቀነዓ ያደታ የአዲስ አበባ ከተማ የመሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ ሃላፊ ፤ ወ/ሮ ሊዲያ ግርማ  ደግሞ የሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ ሃላፊ ሆነው ተሾሙ። ዛሬ 3ኛው የአ/አበባ ምክር ቤት 2ኛ አመት የስራ ዘመን 1ኛ መደበኛ ጉባኤው እያካሄደ ይገኛል። በዚህም ጉባኤ በከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ አቅራቢነት ምክር ቤቱ የተለያዩ ኃላፊዎችን ሹመት አፅድቋል። 1. ዶ/ር ቀነዓ…
#AddisAbaba

የወ/ሮ ሀቢባ ዑመር ያለመከሰስ መብት ተነሳ።

የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት ፍትህ ሚኒስቴር ባቀረበው ጥያቄ የለሚ ኩራ ክ/ከተማ የመሬት አስተዳደር ፅ/ቤት ሃላፊ የነበሩትንና የከተማው ምክር ቤት አባል የሆኑትን የወ/ሮ ሀቢባ ዑመርን ያለመከሰስ መብት አንስቷል።

ግለሰቧ በክፍለ ከተማው በአርሶ አደር እና አርሶ አደር ልጅ ሰበብ በተፈፀመ " የመሬት ምዝበራ " ተጠርጥረው መሆኑን የከተማው አስተዳደር አሳውቋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#AddisAbaba

• ከወራት በፊት "በቅርብ ቀናት በድጋሚ ይወጣል። " ሲባል የነበረውን የጋራ መኖሪያ ቤቶችን ዕጣ ለማውጣት ሂደቶች እየተጠናቀቁ ነው ተብሏል።

• ትክክለኛው የዕጣ መውጫው ቀን እስካሁን አይታወቅም።


የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የተሰረዘውን የ40/60 እና 20/80 የጋራ መኖሪያ ቤቶችን ዕጣ ለማውጣት ሂደቶች እየተጠናቀቁ ሲል አሳውቋል።

የአዲስ አበባ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ፤ ዛሬ ለከተማው ም/ቤት በሰጡት ማብራሪያ " ከዚህ በፊት በ40/60 እና 20/80 የቤት ልማት ፕሮግራም ዕጣ በማውጣት ሂደት ያጋጠመንን ችግር የሚቀርፍ የዕጣ አወጣጥ ስርስዓት በመከተል ለባለ ዕድለኞች ዕጣ ለማውጣት ሂደቱ በመጠናቀቅ ላይ ይገኛል። " ሲሉ ተናግረዋል።

ከዚህ ቀደም የ40/60ና 20/80 የጋራ መኖሪያ ቤቶች ዕጣ አወጣጥ ከፍተኛ ውዝግብ ፈጥሮ እንደነበር እና ከዚሁ ጋር በተያያዘ የዕጣ አወጣት ሂደቱ ፍትሃዊ እንዳይሆን እና እንዲጭበረበር አድርገዋል የተባሉ ኃላፊዎች እንዲሁም ሰራተኞች በህግ ቁጥጥር ስር እንዲሆኑ መደረጉ አይዘነጋም።

ከጋራ መኖሪያ ቤቶች ጋር በተያያዘ በተለይም ደግሞ ፤ የ2005 የ20/80 የባለ 3 መኝታ የጋራ መኖሪያ ቤት ቆጣቢዎች ለ9 ዓመታት ቆጥበው ስለምን በዕጣው ሊካተቱ እንዳልቻለ በግልፅ ማብራሪያ ሲጠይቁ፤ የቀጣዩ የጋራ መኖሪያ ቤት ዕጣ ከመውጣቱ በፊትም መፍትሄ እንዲፈለግላቸው መጠየቃቸው ይታወቃል።

ሌላው ከዚህ የጋራ መኖሪያ ቤት ዕጣ ጋር በተያያዘ ፤ ዕጣው በወጣበት ዕለት የስም ዝርዝራቸውን በቀጥታ በቴሌቪዥን መስኮት የተመለከቱና በመድረክ ላይም ስማቸው ሲጠራ የነበሩ ነዋሪዎች ተሰባስበው የእነሱ ጉዳይ በልዩ መልክ እንዲታይላቸው ለሚመለከታቸው አካላት ጥያቄ አቅርበዋል።

" ህጋዊ በሆነ መንገድ ከእለት ጉርሳችን ላይ ቆጥበን በትእግሥት ስንጠብቅ የነበርን ምንም አይነት ህገ ወጥ የሆነ ተግባር ውስጥ የሌለን እድለኞች እድላችን ተቀምተን በአጭር ቃል ተሠርዙዋል መባላችን እጅግ ያማል " ያሉት እኚህ ነዋሪዎች የአ/አ ከተማ አስተዳደር ንፁሃንን ከወንጀለኞች በመለየት ጉዳያቸውን በልዩ ሁኔታ እንዲያይላቸው ነው የጠየቁት።

በርካታ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች የሚጠብቁት የ40/60 እና 20/80 የጋራ መኖሪያ ቤቶች ዕጣ የሚወጣበት ቁርጥ ያለ ቀን ባይታወቅም የከተማው አስተዳደር ዕጣውን ለማውጣት ሂደቶች እየተጠናቀቁ መሆኑን አሳውቋል።

@tikvahethiopia
#ETHIOPIA

በኤሌክትሪክ ሞተር ከሚሰሩት #በስተቀር የተገጣጠሙ የቤት አውቶሞቢሎች፣ የባለ ሶስት እግር ተሽከርካሪዎች እና የተገጣጠሙ ሞተር ሳይክሎችን ጨምሮ " ቅድሚያ የማይሰጣቸው " ተብለው የተለዩ 38 ዓይነት ምርቶች ወደ ሀገር ውስጥ እንዳይገቡ እግድ ተጥሏል።

እግዱ መጣሉን ያሳወቀው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ነው።

ይኸው እግድ የተላለፈው የህገወጥ የምንዛሬ ገበያውን ይበልጥ ለማውረድ በማሰብ መሆኑ ተገልጿል።

የእግዱ መተግበር በአማካኝ ግማሽ ያህል የውጭ ምንዛሬን ሊያስቀር ይችላል ተብሏል።

#ከሰኞ ጀምሮ ተግባራዊ መሆን የሚጀምረው እገዳ የሚቆየው ላልተወሰነ ጊዜ  ሲሆን እገዳ የተጣለባቸውን ምርቶች ለማስገባት የውጭ ምንዛሬ መጠየቅ እንደማይቻል የብሄራዊ ባንክ አሳውቋል።

ወደ አገር እንዳይገቡ አገዳ የተጣለባቸው ምርቶች ዝርዝር ከላይ ተያይዟል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ETHIOPIA በኤሌክትሪክ ሞተር ከሚሰሩት #በስተቀር የተገጣጠሙ የቤት አውቶሞቢሎች፣ የባለ ሶስት እግር ተሽከርካሪዎች እና የተገጣጠሙ ሞተር ሳይክሎችን ጨምሮ " ቅድሚያ የማይሰጣቸው " ተብለው የተለዩ 38 ዓይነት ምርቶች ወደ ሀገር ውስጥ እንዳይገቡ እግድ ተጥሏል። እግዱ መጣሉን ያሳወቀው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ነው። ይኸው እግድ የተላለፈው የህገወጥ የምንዛሬ ገበያውን ይበልጥ ለማውረድ በማሰብ…
ከውጭ እንዳይገቡ እገዳ የተጣለባቸው ምርቶች ዝርዝር ፦

- ከረሜላዎች፣ ማስቲካዎችና ሌሎች ጣፋጭ ዝግጅቶች

- ቸኮሌት

- ብስኩቶች እና ዋፈሮች

- የፍራፍሬ ጭማቂዎች እና የታሸጉ ፍራፍሬዎች

- ከፍራፍሬ የተዘጋጁ ጃሞች፣ የድንች ጥብሶች ፣

- የታሸጉ ውሃዎች ለስላሳ መጠጦችና አልኮል የሌላቸው መጠጦች

- ውሰኪ፣ ወይን ቢራና ለሎች አልኮል መጠጦች በሙሉ

- ሲጋራ

- ሽቶዎችና ቶይሌት ዋተርስ

- የውበት ወይም የመኳኳያ ዝግጅቶች ፣

- ሳሙናዎች

- ርችቶች

- ቦርሳና ዋሌቶች

- ሳይክሎች

- በታሪፍ ቁጥር 9401 እስከ 9403 የሚመደቡ የቤትና የቢሮ ዕቃዎች

- የገበታ ጨው

- የተለያዩ መጫወቻ እቃዎች

- የእጅ፣ የጠረጴዛና የግድግዳ ሰአቶች

- ዣንጥላዎች

- ምንጣፎች

- የአሳማ ስጋዎች

- የዶሮ ስጋዎች

- ቱናዎች፣ ሰርዲኖችና ሌሎች የአሳ ምርቶች

- ከህፃናት አልሚ ምግቦችና ወተቶች #በስተቀር የተለያዩ የታሸጉ ምግቦች

- ከሴራሚክስና ፖርስሊን የተዘጋጁ የቤት እቃዎች

- ጋዝ ላይተር

- የተለያዩ የጸጉር ጌጣጌጦች

- ልብስ ማሳያ አሻንጉሊቶች

- ከብርጭቆ የተዘጋጁ የመጠጥ መጠጫ እቃዎች፣ የስጋራ መተርኮሻዎች፣የአበባ መያዣና ተመሳሳይ እቃዎች

- የተታተመ ስዕላዊ መግለጫ ያላቸው ካርዶች፣

- የቀን መቁጠሪያ ካሌንደሮች፣

- ስዕሎች የግድግዳ ሥዕሎች ጨምሮ

- ባርኔጣዎችና ኮፍያዎች

- አርቲፊሻል አበባዎች

- የሰውና አርቴፊሻል ጸጉሮች ፣

- አርቴፊሻል ጌጣጌጦች

- የተገጣጠሙ የቤት አውቶሞቢል ና ባለሶስት እግር ተሸከርካሪዎች /በኤሌክትሪክ ሞተር የሚሰሩትን ሳይጨምር/

- የተገጣጠሙ ሞተር ሳይክሎች /በኤሌክትሪክ ሞተር የሚሰሩትን ሳይጨምር/

@tikvahethiopia
" የባንክ ሂሳባቸው ታግዷል "

13 የ " ቤቲንግ " ሥራ ድርጅቶች እንዲሁም 109 አንቀሳቃሾቻቸው ከህብረተሰቡ የሚሰበስቡትን ከፍተኛ የሆነ ገንዘብ በመጠቀም በጥቁር ገበያ የውጭ ሀገር ምንዛሬ ግዢ ላይ እየተሳተፉ መሆኑን በተደረገ ክትትል በመረጋገጡ የባንክ ሂሳባቸው እንዲታገድ ተደረገ።

ጉዳያቸውም በህግ እንደሚታይ ተገልጿል።

" ቤቲንግ " በሚል ስያሜ የሚታወቁትና የውርርድ ስራዎችን ላይ የተሰማሩት እነዚህ አካላት #የታክስ_ማጭበርበርን ጨምሮ በህገ-ወጥ የጥቁር ገበያ የውጭ ምንዛሬ ግዢ ወንጀል ድርጊት ላይ ተሳታፊ መሆናቸው #ተረጋግጧል ሲል የፋይናንስ ደኅንነት አገልግሎት አስታውቋል።

አገልግሎቱ የ13ቱን የቤቲንግ ስራ ድርጅቶች እና የ109 አንቀሳቃሾቻቸውን ስም ዝርዝር በይፋ አልገለፀም።

በእነዚህና በሌሎችም ዘርፎች በሚንቀሳቀሱ እና መሰል የወንጀል ተግባር ላይ በሚሳተፉ አካላት ላይ ቀጣይነት ያለው ክትትልና ህጋዊ የሆነ እርምጃ ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን ያስታወቀው የፋይናንስ ደህንነት አገልግሎት ታሳታፊ እየሆኑ ያሉ አካላት ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ አስጠንቅቋል።

@tikvahethiopia @tikvahethmagazine
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update ለመጀመሪያ ጊዜ በፌዴራል ተቋማት / ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ እየተሰጠ የሚገኘው የ2014 ዓ/ም 12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና የመጀመሪያው ዙር / የማህበራዊ ሳይንስ ፈተና ተጠናቋል። ከጥቅምት 5/2015 ዓ/ም ጀምሮ የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች መግባት ይጀምራሉ። ውድ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት ፤ የተማሪዎች ጉዳይ የሀገር ጉዳይ ስለሆነ ባለፉት ዓመታት የ12ኛ ክፍል ፈተናዎችን ጉዳይ በንቃት…
#Update

ዛሬ እና ነገ የ12ኛ ክፍል የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ወደ መፈተኛ ማእከላት / ዩኒቨርሲቲዎች ይገባሉ።

ይህ ፈተና ለመጀመሪያ ጊዜ በዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ ጥብቅ በሆነ ህግ መሰጠት ከመጀመሩ ጋር በተያያዘ ፈተናቸውን ጨርሰው የወጡት " የማህበራዊ ሳይንስ " ተማሪዎች በዩኒቨርሲቲ ቆይታቸው የተመለከቱትን እና በቀጣዩ " የተፈጥሮ ሳይንስ " ፈተና ወቅት ሊስተካከለ ይገባል ያሏቸውን ጉዳዮች በዝርዝር አቅርበዋል።

ፈታኝ መምህራንም ሀሳባቸውን አጋርተዋል።

#ከማህበራዊ_ሳይንስ_ተፈታኞች

- በባለፈው ፈተና ወቅት በአንዳንድ ተቋማት ውስጥ በምግብ አቅርቦት ጉዳይ ክፈትቶች የነበሩ ሲሆን ተማሪዎች በጊዜ ምግብ እንዲያገኙ እንዲሁም በግቢ ውስጥ ያሉት የአገልግሎት ሰጪዎች በተመጣጣኝ ዋጋ ሊያቀርቡ ይገባል። " የውሃ " አቅርቦትም ችግሮች የነበሩባቸው ተቋማት ነበሩ የሚገቡት ተማሪዎች ዩኒቨርሲቲ የመጀመሪያቸው እንደመሆኑን ለአምስት ቀን እንኳን ተማሪ ለማስተናገድ የሚሆን ውሃ ማቅረብ ይገባል። 

- አንዳንድ ተቋማት ውስጥ ስርዓት የጎደላቸው ተፈታኝ ተማሪዎች በሌሎች ተማሪዎች ላይ ጫና ለማሳደር ሲሞክሩ ታይቷል ፤ በየዶርሙ እየዞሩ ምግብ አምጡ፣ ብር አምጡ ሲሉ የነበሩም ተማሪዎች የነበሩ ሲሆን በቀጣዩ የፈተና ወቅት እንዲህ አይነት ባህሪ ያላቸው ተፈታኞች ካጋጠሙ የሚመለከተው አካል ለሌሎች አስተማሪ የሆነ እርምጃ መውሰድ ያስፈልገዋል።

- በባለፈው ፈተና ወቅት በአንዳንድ ተቋማት ውስጥ ሌሎች ተማሪዎችን የሚረብሹ፣ የሚጮሁ ፣ በየዶርሙ እየሄዱ ተማሪ በተኛበት ሲያንኳኩ የነበሩ ተማሪዎች ነበሩ ፤ በተጨማሪ የግል ትምህርት ቤት ተማሪዎች " ፈተና ደርሷቸዋል " በሚል የተሳሳተ መረጃ ተማሪዎች ላይ ጫና ለማሳደር እና ለማስፈራራት የሞከሩ ነበሩና በዚህኛው ፈተና ሁሉም ተማሪ በቂ ገለፃ እና ከመሰል ድርጊቶች እንዲቆጠቡ ማስገንዘብ ይገባል።

- ተፈታኝ ተማሪዎች ፤ ስለታም ነገሮች እና የተከለከሉ የሚጬሱ ነገሮችን ለምሳሌ እንደ ሲጋራ እንዳያስገቡ ፍተሻ ላይ የሚመደቡ የፀጥታ ኃይሎች ያለመሰልቸት ፍተሻ ማድረግ ይገባቸዋል። በግቢ ውስጥ ተማሪዎች ሲረብሹ ቢገኙ ደግሞ አጥፊዎችን ለይቶ ማስወጣት ይገባል እንጂ ሁሉም ተማሪዎች ላይ በጅምላ እምርጃ መውሰድ አይገባም።

- አንዳንድ ስነ ስርዓት የሌላቸው ተፈታኝ ተማሪዎች " ሴት ተማሪዎችን ለመተንኮስ " የሞከሩም ታይተዋልና የፀጥታ ኃይሎች ተማሪዎች ሳይጨነቁ እና ምንም ሳይፈሩ ፈተናቸውን እንዲወስዱ ማድረግ አለባቸው ፤ የላላ ቁጥጥር በተማሪዎች ውጤት ላይ የሚያደርሰው ተፅእኖ ከባድ ነው።

- ከተማሪዎች ማደሪያ/ዶርም ጋር በተያያዘ ትክክለኛና ወጥ የሆነ አሰራር መዘርጋት ይኖርበታል። በአንዳንድ ተቋማት ተማሪዎች በተመደቡበት ሳይሆን እንደፈለጉ እየገቡ፣ ሌሎችን ተፈታኝ ተማሪዎች እየረበሹ የመኝታ ክፍል ለመያዝ ሲጥሩ ነበር። አንዳንድ ተማሪዎች " ተመድበንበታል " ብለው የሄዱበት ማደሪያ / ዶርም በሌሎች ተይዞ እንዳገኙ ገልፀዋል፤ በማደሪያ ክፍል ችግር የተንገላቱ ብዙ ናቸው። በቀጣይ ፈተና ወቅት ይህ ከማደሪያ ክፍል ጋር የተያያዘ ችግር መስተካከል ይኖርበታል።

- ምሽት ላይ የተማሪዎችን ደህንነት የማስጠበቅ ስራ መጠናከር አለበት፣ የሚረብሹ፣ የሚጮሁ ተማሪዎችን መቆጣጠር ይገባል። ከዚህ ባለፈ ከፍተሻ መሰላቸት ጋር በተያያዘ ሊሆን ይችላል ያልተፈቀዱ ነገሮች አልፈው ሲገቡ ታይተዋል ፤ ስልክም ደብቀው ይዘው የገቡም ነበሩና ጥብቅ የሆነ ፍተሻ እና ቁጥጥር ያስፈልጋል።

ማጠቃለያ ፦ የ2014 ተፈታኞቹ እንደመጀመሪያ ጊዜ የዩኒቨርሲቲ ቆያታቸውና በእንደህ አይነት መንገድ ለፈተና መቀመጣቸው አዲስ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ በርከታ እክሎች የነበሩ ቢሆን በቀጣይ ላለው ፈተና እንዲስተካከል ጠቁመዋል።

#ከፈታኝ_መምህራን

- አንዳንድ ፈታኞች " ኩረጃን በሚያበረታታ " ድርጊት ሲፈፅሙ ነበር ፤ ይህ የትውልድ ጉዳይ ለመሆኑን ያለመሰላቸት የፈተናውን ሂደት መከታተል አለባቸው።

- ተማሪዎች ስልክ ይዘው ግቢ እንዳይገቡ የተደረገው ከውጭ በመደዋወል በሀሰተኛ ወሬ እንዳይረበሹ በማሰብ ነበር ነገር ግን አንድ የቲክቫህ ቤተሰብ አባል ፈታኝ በፈተነበት ተቋም ፀጥታ ለማስከበር የተሰማሩ አካላት ለተማሪዎች ስልክ ሲሰጡ ተመልክቷል። የፀጥታ ኃይሎች ግቢ ውስጥ ሬድዮ ብቻ ቢጠቀሙ እና ሞባይል ባይፈቀድ መልካም መሆኑን ጠቁሟል።

- አንድ የቤተሰባችን አባል የሆነ ፈተና ፈታኝ ተማሪዎች ለቀው ከወጡበት በአንዱ ተቋም እያስፈተነ የነበረ ሲሆን በፈተና ስርዓቱ ያጋጠሙ ችግሮችን በዝርዝር ገልጾልናል፡ ሱፐርቫይዘሮች እና የጣቢያ ኃላፊዎች ስራቸውን በቁርጠኝነት ሊሰሩ እንደሚገባ እና በፈተና ክፍል ለሚስተዋሉ ችግሮች ፈጣን መፍትሄ ሊሰጡ ይገባል ብሏል።

- በፈተና ወቅት ለተፈታኞ የተሰጠው " የፈተና ሰዓት " በአግባቡ መቆጣጠር የሚገባ ሲሆን ቢቻል ቢቻል ፈተናው " ሙሉ በሙሉ " እስኪያልቅ የፈተናውን ወረቀት ይዘው እንዳይወጡ መከታተል ቢቻል ጥሩ ነው።

- "በቂ ዝግጅት"  ያላደረጉ ተማሪዎች የኩረጃ መንገዱ ሁሉ ስለተዘጋባቸው የፈተናው ስርዓት እንዲረበሽ እና ፈተናው እንዲሰረዝ ለማድረግ ሲጥሩ ነበር። እነዚህ ተማሪዎች ዓለማቸውን ለማስፈፀም ሌላ አካባቢ " ፈተና ተሰረቋል " የሚል እና ሌሎችንም ያልተረጋገጡ ወሬዎችን ነው የሚያስወሩት።

በተጨማሪ ፦

• በአንዳንድ ተቋማት ውስጥ ተማሪዎች ፈታኞችን በግልፅ " እንድንኮራረጅ ካላስደረጋችሁን " ሲሉ ነበር ፤

• ፈታኝ የሚያክብሩ እንዳሉ ሁሉ ፈታኞችንና የፈተናውን ህግ የማያከብሩ ነበሩ፣

• አንዳንድ ተማሪዎች ለፈተና መምጣታቸውን በማወቅ መዘጋጀት ሲገባቸው በግቢ ውስጥ ጥንድ ጥንድ ሆነው ሲዟዟሩ/ሲዝናኑ ነበር ፣

• አንዳንድ ተማሪዎች " ፈተናውን አናልፍም " በሚል የጥያቄ ወረቀቱን ሳይከፍቱት የመልስ ወረቀቱን ዝም ብለው ሲሞሉ ነበር ፣

• ተማሪዎች " በጭንቀት " ብቻ ለህመም ስለሚጋለጡ ትምህርት ሚኒስቴር / ዩኒቨርሲቲዎች በተማሪዎች ስነልቦና ላይ ከፍተኛ ስራ ሊሰሩ ይገባል። ተማሪዎቹ ለፈተና ሊገቡ ሲሉ ፈተናውን በራሳቸው አቅም መስራት እንደሚችሉ ተስፋ ሊሰጣቸው ይገባል።

ማጠቃለያ ፦ ክፍተቶች በቶሎ ቢታረሙና መስተካከል የሚገባቸው ጉዳዮች በፍጥነት ቢስተከከሉ ቀጣዩን ፈተና ካለፈው በመማር ስኬታማ ማድረግ ይቻላል።

#ለተፈጥሮ_ሳይንስ_ተማሪዎች

ማህበራዊ ሚዲያ ላይ በሚናፈስ ምንም ያልተረጋገጠ እና ሀሰተኛ ወሬዎች ሳትረባሹ ቀደም ብለው ወደ ግቢ ገብተው ብሔራዊ ፈተናውን ከወሰዱት " የማህበራዊ ሳይንስ " ተፈታኝ ጓደኞቻችሁ ግቢውን ለመላመድ ይረዳቹ ዘንድ በቂ መረጃ በመጠየቅ ፣ የፈተና ህጎችን ሁሉ በማክበር ፈተናችሁን በስኬት ታጠናቅቁ ዘንድ እንመኛለን። መልካሙ ሁሉ ይግጠማችሁ ፤ መልካም ፈተና !

#ለማህበራዊ_ሚዲያ_ተጠቃሚዎች

ዩኒቨርሲቲ ገብተው ፈተና የወሰዱት / በቀጣይ ቀናት የሚወስዱት ታዳጊዎች ለፈተና ስርዓቱ ብቻ ሳይሆን ለዩኒቨርሲቲ ዓለም አዲስ በመሆናቸው መደገፍ ፣ ማበረታታት  እና በራሳቸውን እንዲተማመኑ ማድረግ ፣ እንጂ በሀሰተኛ እና ባልተረጋገጠ ወሬ እንዲረበሹ እና ይህን ገና ብዙ የሚሰሩበትን እድሜ የፖለቲካ ቁማር መጫወቻ ማደርግ ፣ ተስፋቸው እንደጨለመ አድርጎ ወሬ መንዛት የአይገባም።

#TikvahFamily

@tikvahethiopia
#UN

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብአዊ ጉዳዮች ረዳት ዋና ጸሃፊና የአስቸኳይ ድጋፍ አስተባባሪ ማርቲን ግሪፊትስ በሽሬ ያሉ ሲቪሎች እና የሰብዓዊ እርዳታ ሰራተኞች ደህንነት ያሳስበኛል ብለዋል።

ግሪፊትስ ፤ በአካባቢው ያለው የፀጥታ ሁኔታ እየተባባሰ መምጣቱን ገልፀው ፤ " ትላንት ሁለት የፊት መስመር ሰራተኞች መቁሰላቸውን ሰምቼ ደንግጫለሁ " ብለዋል።

" ጦርነቱ እነሱ ወዳሉበት እየቀረበ መሆኑን ተከትሎ ያደረባቸውን ጭንቀት እጋራለሁ " ያሉት ግሪፊትስ ፤ " ሁሉም ወገኖች ወደ ውይይት እንዲመጡ እስከዚያው ድረስ ግን ሲቪሎችን እና የረድኤት ሰራተኞችን እንዲጠብቁ በድጋሚ ጥሪዬን አቀርባለሁ " ብለዋል።

@tikvahethiopia