TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#SNNPRS #SouthWestEthiopia

የ8ኛ ክፍል ፈተና ውጤት ይፋ ሆነ።

የደቡብ ክልል እና የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል የ8ኛ ክፍል ፈተና ውጤት ይፋ መሆኑ ዛሬ ተገልጿል።

በሁለቱ ክልሎች ውሳኔ መሰረት የማለፊያ ነጥብ ፦

👉 ለወንዶች 41፣
👉 ለሴቶች 40 እና
👉 ለአይነ ስውራን 39 ሆኖ ተወስኗል።

በዚህ መሰረት ፦ በ2014 ዓ.ም የትምህርት ዘመን በሁለቱም ክልሎች ለፈተና ከተቀመጡ ከ257 ሺህ በላይ ተማሪዎች 187 ሺህ 500 በላይ ተማሪዎች ወደቀጣይ ክፍል የሚያሳልፋቸውን ውጤት አምጥተዋል።

ለፈተና ከተቀመጠው አጠቃላይ ተማሪ ቁጥር ሲታይ ከ73 በመቶ በላይ ተማሪዎች አልፈዋል።

በተለየ መልኩ ከጸጥታ ጋር በተያያዘ በአሉታዊ ጫና ውስጥ ሆነው የተማሩና ለፈተና የተቀመጡ የደራሼ ልዩ ወረዳ ተማሪዎችን ውጤት በተለየ መልኩ ታይቷታ።

በዚህም መሰረት ፦

👉 ለወንዶች 39፣
👉 ለሴቶች 38 እና
👉 ለአይነ ስውራን 37 ሆኖ ተወስኗል።

የሁለቱ ክልሎች ተማሪዎች ውጤታቸውን ከነገ ጀምሮ መውሰድ ይችላሉ ተብሏል።

የደራሼ ልዩ ወረዳ ተማሪዎች ግን ውጤታቸው በእጅ የሚሰራ በመሆኑ የ1 ሳምንት ጊዜ ዘግይቶ ይደርሳል እስከዛው በትዕግስት እንዲጠባበቁ መልዕክት ተላልፏል።

#ENA

@tikvahethiopia
#SouthWestEthiopia

በአንድ ሞተር ላይ ሆነው ሲጓዙ የነበሩ 3 ሰዎች ከአይሱዙ መኪና ጋር ተጋጭተው የሁሉም ህይወት ወዲያው ማለፉ ተሰማ።

ይህ አሰቃቂ አደጋ የደረሰው ትላንት መስከረም 26 ቀን 2016 ዓ/ም ልክ ከቀኑ 8:10 ላይ  በኮንታ ዞን ኮንታ ኮይሻ ወረዳ 01 ቀበሌ ልዩ ስሙ " ጥሴ " ተብሎ የሚጠራው አካባቢ ነው።

እንደ ፖሊስ መረጃ መነሻውን ከመንደር 11 ወደ ኮይሻ ገበያ 3 ሰዎችን ጭኖ ሲጓዝ የነበረ ሞተር ከኮይሻ ገበያ ወደ መንደር 11 ይጓዝ የነበረ የጭነት አይሱዚ ተሽከርካሪ ጋር በመጋጨቱ የሞተሩ አሽከርካሪ እና 2 ተሳፋሪዎች ወዲያውኑ ህይወታቸዉ አልፏል።

መረጃው ከደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የህዝብ ግንኙነትና ኮሚንኬሽን የተገኘ ነዉ።

@tikvahethiopia