TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram

የመግቢያ ነጥብ ዝቅ ተደረገ!

#ASTU #AASTU

የአዲስ አበበ እና አዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲትዎች መግቢያ ነጥብ ዝቅ አለ!

የተማሪዎችን ፍላጎትና በተደጋጋሚ የሚነሳውን የመግቢያ ነጥብ ዝቅ ይበልልን ጥያቄ ከግምት ውስጥ በማስገባት የAPPLIED SCIENCE መግቢያ ሆኖ በማስታወቂያ የተገለጸው ለወንድ፡190 እና ለሴት፡185 ከነበረው ዝቅ ተደርጎ

ለወንድ፡ 176 እና
ለሴት፡166

የAPPLIED SCIENCE መግቢያ ሆኖ የተወሰነ መሆኑን እያሳወቅን እስከ ነገ መስከረም 20/01/2012 ዓ.ም. ማታ 12፡00 ሰዓት ድረስ ብቻ በዚህ መስክ መመደብ የምትፈልጉ የ2011ዓ.ም. የዪኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና ተፈታኞች፤ ለት/ቤታችሁ ፍላጎታችሁን በመግለጽ ምርጫችሁን ት/ቤታችሁ እንዲያስገባላችሁ ማድረግ የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን።

http://app.neaea.gov.et/

የሀገር አቀፍ ትምህርት ምዘናና ፈተናዎች ኤጀንሲ


@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ASTU

በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ (ASTU) ዛሬ ጠዋት ለ4 ቀናት የሚቆይ የደም ልገሳ ፕሮግራም ተጀምሯል። የደም ልገሳ ፕሮግራሙን ያዘጋጁት ክለብ 20/25 ከአዳማ ከተማ ደም ባንክ ጋር በመተባበር ነው። ዛሬ በነበረው የደም ልገሳ ላይ በርካታ ተማሪዎች ተሳትፈዋል።

Via Hiwi(ቲክቫህ አዳማ-ASTU ቤተሰብ)
@tsegabwolde @tikvahethiopia
animation.gif
17.2 KB
#ASTU

የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ(ASTU) የመማር ማስተማር ሂደቱን ለማስቀጠል እየሰራ መሆኑን ገለጸ። የዩኒቨርሲቲው ፕሬዘዳንት ዶ/ር ለሚ ጉታ ዛሬ ለኢዜአ እንደተናገሩት በዩኒቨርሲቲው ሰላማዊ የመማር ማስተማር ሂደት ለማረጋገጥ እንቅስቃሴ በመደረግ ላይ ነው። በዚህም ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር በመቀናጀት ተማሪዎች ትምህርታቸውን ለማስቀጠል እየተሰራ ነው ብለዋል።

ተማሪዎች ከቤተሰቦቻቸው ተለይተው ወደ  ተቋሙ የመጡበትን ዓላማ እንዲተዉ የሚገፋፏቸውን አካላት የፖለቲካ አጀንዳ ማስፈጸሚያ እንዳይሆኑ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ጠይቀዋል። በዩኒቨርሲቲው የመማር ማስተማር ሂደቱ ሰላማዊነቱን ጠብቆ ለማካሄድ በከተማዋ ከተቋቋመው ኮማንድ ፖስት ጋር በመሆን የተማሪዎችን ደህንነት  በመጠበቅ  ላይ እንደሚገኝ ፕሬዚዳንቱ አስታውቀዋል።

(ኢዜአ)

በሌላ በኩል ከቲክቫህ ቤተሰቦች...

በASTU፣ ሀረማያ፣ ጅማ(JiT)፣ መደወላቡ፣ ደምቢ ዶሎ፣ መቱ ዩንቨርስቲዎች ውስጥ ባለው አለመረጋጋት ሳቢያ ተማሪዎች ያደረባቸውን ስጋት ዛሬም እየገለፁ ይገኛሉ። ለህይወታችን ሰግተናል ያሉ ተማሪዎች በቤተ እምነት ውስጥ ተጠለልው እንደሚገኙ ገልጸዋል። መልዕክት የላኩት ተማሪዎች ጉዳዩ ይሄ ያህል እስኪከር ድረስ ምንም መፍትሄ ባለመሰጠቱ የፌደራል መንግስቱን ወቅሰዋል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የዛሬ የህዳር 10/2012 ዓ/ም በተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ ከሚገኙ የቲክቫህ ቤተሰብ አባልት እና ከተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች እና ከሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር የተሰባሰበ መረጃ👇
https://telegra.ph/ETH-11-20-4

(TIKVAH-ETHIOPIA)

#ድሬዳዋ #ሀረማያ #ወልዲያ #መቱ #ASTU
#መደወላቡ #ባህርዳር #ደባርቅ #ደብረታቦር

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ASTU

የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ(ASTU) ዛሬ ለሶስተኛ ጊዜ ባወጣው ማስታወቂያ የመማር ማስተማ መርሃ ግብር መቆራረጡ እንደቀጠለ እንደሆነ ገልጿል። ከሰኞ ጀምሮ ሁሉም የቅድመ ምረቃ ተማሪዎች በትምህርት ገበታቸው ላይ እንዲገኙ በጥብቅ አሳስቧል። ይህ ሆኖ ባይገኝ ግን በትምህርት ገበታው ላይ ያልተገኘ ተማሪ በራሱ ፍቃድ ትምህርት እንዳቋረጠ ተቆጥሮ ዩኒቨርሲቲው አስፈላጊውን እርምጃ እንደሚወስድ ገልጿል።

ዩኒቨርሲቲው ይህን ቢልም...

መልዕክቶቻቸው "ለቲክቫህ ኢትዮጵያ" የላኩ የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ (ASTU) ተማሪዎች የሆኑ የቤተሰባችን ዓባላት በግቢው ውስጥ በበራሪ ወረቀት እየተሰራጩ የሚገኙ እንዲሁም በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያዎች እየተላለፉ ያሉ የማስፈራሪያ መልዕክቶች ትምህርታችንን በአግባቡ እንዳንከታተል እንቅፋት ሆኖብናል ብለዋል።

@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
#ASTU

በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ(ASTU) ትናንት ማታ ከለሊቱ 7 ሰዓት በተማሪዎች መካከል በተነሳ ግጭት አምስት ተማሪዎች ጉዳት ደርሶባቸው ህክምና ላይ ናቸው፡፡ አጥፊዎቹን የመለየትና በቁጥጥር ስር የማዋል ስራም እየተከናወነ ይገኛል፡፡

(የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር)

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#ASTU

በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩንቨርሲቲ /ASTU/ ቅጥር ግቢ ዉስጥ በሁለት ጓደኛሞች ተማሪዎች መካከል በተፈጠረ አለመግባባት የካቲት 17/2012 ከምሽቱ ሁለት ሰዓት አካባቢ የ4ኛ ዓመት ተማሪ የሆነዉ ተማሪ ዘሪሁን መንግስቱ ህይወት ያለፈ ሲሆን በግድያዉ የተጠረጠረዉ ተማሪ እጁን ለፖሊስ ሰጥቷል፡፡

በተባባሪነት የተጠረጠረዉ ተማሪ በፖሊስ ቁጥጥር ስር ሆኖ ጉዳዩ በአዳማ ከተማ ወንጀል ምርመራ አካላት እየተጣራ ይገኛል ሲል ዩኒቨርሲቲው አስታውቋል፡፡

ዩኒቨርሲቲው እንደገለጸው በቀጣይም የተማሪዉን አሟሟት የሚገልፅ የፖሊስና የህክምና ምርመራ ዉጤት እንደደረሰ ለሚመለከተዉ አካል የሚገልጽ መሆኑን አስታውቋል፡፡

[Tikvah-family፣ አዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩንቨርሲቲ]

@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
#ASTU

አዳማ ሳይንሳና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ በታሪኩ #ለመጀመሪያ ጊዜ ለሁለት መምህራንና ተመራማሪዎች የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ ሰጠ።

ዩኒቨርሲቲው የፕሮፌሰርነት ማዕረግ የሰጠው ለፕሮፌሰር አሰፋ አባሁና እና ለፕሮፌሰር አማን ደቀቦ መሆኑን ከኤፍ ቢ ሲ ያገኘነው መረጃ ይጠቁማል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#ASTU

የአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ (ASTU) በተለያዩ መርሃግብሮች ሲያስተምራቸው የነበሩ ተማሪዎቹን በዛሬው ዕለት እያስመረቀ ይገኛል።

ዛሬ 1 ሺህ 300 ተማሪዎችን እያስመረቀ የሚገኘው፡፡

ከዚህ ውስጥ 1 ሺህ 228 በመጀመሪያ ዲግሪ ሲሆን 70 በሁለተኛ ዲግሪ እንዲሁም 2 ተመራቂዎች በሶስተኛ ዲግሪ ናቸው።

@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
#ASTU #AASTU

ሁለቱ የኢትዮጵያ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲዎች የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ተፈትነው ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የሚያስገባ ነጥብ ያዝመዘገቡ ተማሪዎችን ለመቀበል በዛሬው ዕለት ጥሪ አቅርበዋል።

ዩኒቨርሲቲዎቹ የ2014 ዓ.ም መግቢያ ፈተና የምዝገባ ጥሪ አውጥተዋል።

የመመዝገቢያ መስፈርቱ የሲቪክስ ትምህርትን ሳይጨምር የስድስት ትምህርት ድምር ውጤት ከዚህ በታች እንደተገለፀው ነው።

ለታዳጊ ክልሎች (አፋር፣ ሱማሌ፣ ቤ/ጉሙዝ ፣ ጋምቤላ) ፦

- ኢንጂነሪንግ ለወንድ 395 ለሴት 390
- አፕላይድ ሳይንስ ለወንድ 385 ለሴት 380


ለሌሎች ክልሎች ፦

- ኢንጂነሪንግ ለወንድ 400 ለሴት 395
- አፕላይድ ሳይንስ ለወንድ 390 ለሴት 385


የምዝገባ ጊዜው ከየካቲት 21 ቀን 2014 ዓ/ም እስከ የካቲት 30 /2014 ዓ/ም ሲሆን ምዝገባው የካቲት 30 /2014 ዓ/ም ከለሊቱ 6 ሰዓት ላይ ይጠናቀቃል ተብሏል።

ከላይ የተቀመጠውን የምዝገባ መስፈርት የሚያሟሉ ተማሪዎች በማንኛውም ስፍራ ሆነው በኢንተርኔት www.aastu.edu.et እና www.astu.edu.et ላይ መመዝገብ ይችላሉ።

ፈተናው መጋቢት 7 ቀን 2014 ዓ/ም እንደሚሰጥ ተነግሯል።

(ተጨማሪ መረጃ ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia
#AASTU #ASTU

በ2017 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ እና በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ገብተው በአፕላይድ ሳይንስና በኢንጂነሪንግ የትምህርት ዘርፎች ትምህርታቸውን መከታተል ለሚፈልጉ ጥሪ ቀርቧል።

ዩኒቨርሲቲዎቹ በ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና 50% እና ከዚያ በላይ ያስመዘገቡ የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎችን ተጨማሪ የመግቢያ ፈተና በቀጥታ (online) በመስጠት ነው የሚቀበሉት።

የትምህርት መስኮቹ ምን ምን ናቸው ?

/ አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ /

#ኢንጂነሪንግ ፦ አርክቴክቸር፣ ሲቪል ኢንጂነሪንግ ፣ ሜካኒካል ኢንጂነሪንግ ፣ ኬሚካል ኢንጂነሪንግ ፣ ኤሌክትሪካል እና ኮምፒዩተር ኢንጂነሪንግ ፣ ኤሌክትሮ መካኒካል ኢንጂነሪንግ ፣ሶፍትዌር ኢንጂነሪንግ ፣ ማይኒንግ ኢንጂነሪንግ ፣ ኢንቫይሮሜንታል ኢንጂነሪንግ

#አፕላይድሳይንስ ፦ ኢንዱስትሪያል ኬሚስትሪ፣ ፉድ ሳይንስ፣ አፕላይድ ኒውትሪሽን ፣ ጂኦሎጂ፣ ባዮቴክኖሎጂ

/ አዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ /

#ኢንጂነሪንግ ፦ አርክቴክቸር፣ ሲቪል ኢንጂነሪንግ ፣ ወተር ሪሶርስ ኢንጂነሪንግ ፣ ኬሚካል ኢንጂነሪንግ ፣  ሜካኒካል ኢንጂነሪንግ ፣ ማቴሪያል ሳይንስና ኢንጂነሪንግ ፣ ኤሌክትሪካል ፓወር እና ኮንትሮል ኢንጂነሪንግ፣ ኤሌክትሮኒክስ እና ኮሚኒኬሽን ኢንጂነሪንግ፣ ኮምፒዩተር ሳይንስ ኢንጂነሪንግ፣ ሶፍት ዌር ኢንጂነሪንግ

#አፕላይድሳይንስ ፦ አፕላይድ ቦዮሎጂ፣ አፕላይድ ኬሚስትሪ፣ ኢንዱስትሪያል ኬሚስትሪ፣ ፋርማሲ፣ አፕላይድ ፊዚክስ ፣ አፕላይስ ጂኦሎጂ፣ አፕላይድ ማቲማቲክስ

የምዝገባ ጊዜ፡- ከመስከረም 06 እስከ መስከረም 13 ቀን 2017 ዓ.ም እንደሆነ ተገልጿል።

ምዝገባው የሚጠናቀቀው መስከረም 13 ቀን 2017 ዓ.ም ከሌሊቱ 6 ሰዓት ላይ ነው።

የምዝገባ መስፈርቱን የሚያሟሉ አመልካቾች በማንኛውም ስፍራ በኢንተርኔት (online https://stuoexam.astu.edu.et ወይም www.aastu.edu.et / www.astu.edu.et ድረገጽን በመጠቀም መመዝገብ ይችላሉ፡፡

ፈተናው የሚሰጥበት ቀን በድህረ ገጽ የምዝገባው ቀን ካበቃ በኋላ ይደረጋል።

ፈተናው የሚሰጥበት ቦታ ፤ በምዝገባ ወቅት በመረጡት ዩኒቨርሲቲ (የፈተና ጣቢያ) በአካል በመቅረብ ይሆናል፡፡

NB. ለምዝገባና ለፈተና ምንም አይነት ክፍያ የማይጠየቅ ሲሆን የፈተና ጣቢያዎቹ ያላቸው የመፈተኛ ቦታ ውስን በመሆኑ ፍላጎቱ ያላቸው አመልካቾች ይህን አውቀው ቅድሚያ እንዲመዘገቡ ተብሏል።

@tikvahethiopia