TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ተከልክሏል

ማንኛውም ሰው ፈቃድ ሳይወስድ የ 'በጎ አድራጎት ኮሚቴ ' በማቋቋም ገንዘብ የማሰባሰብ ስራ እንዳይሰራ መከልከሉን የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን አስታወቀ።

ከዚህ ቀደም ፈቃድ ሳይኖራቸው የበጎ አድራጎት ኮሚቴ አቋቁመው በገንዘብ ማሰባሰብ ላይ የሚገኙ ግለሰቦችና ቡድኖች ከባለስልጣኑ ፈቃድ በመውሰድ ወደ ህጋዊ አሰራር መግባት እንዳለባቸውም አሳስቧል።

ይህንን ተግባራዊ በማያደርጉ አካላት ላይ ተገቢ የሆነ ማጣራት በማድረግ አስፈላጊውን ርምጃ እንደሚወስድ አስጠንቅቋል።

ከባለስልጣኑ ፈቃድ ሳይኖራቸው በህዝብ ስም በማንኛውም መንገድ ገንዘብ የማሰባሰብ ስራዎችን መስራት የተከለከለ መሆኑን የገለጸው የባለስልጣኑ መረጃ፤ በህዝብ ስም የሚሰበሰብ ገንዘብ በህገ ወጥ መንገድ እንዳይባክን የመከላከልና የመጠበቅ ስልጣን እንዳለው አመልክቷል።

#ENA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ATTENTION ደባርቅ ! የደባርቅ ከተማ አስተዳደር የፀጥታ ምክር ቤት ከወቅታዊ ፀጥታ ስጋት ጋር በተያያዘ የተለያዩ ውሳኔዎች ማሳለፉን አሳውቋል። የፀጥታ ምክር ቤቱ በከተማው ውስጥ የሚገኘው የተፈናቃይ መጠለያ ነዋሪ ከ12:00 በሗላ ወደ ውስጥም ሆነ ወደ ከተማ መግባት እንደማይችል ከልክሏል። የባጃጅ ተሽከርካሪችም ከምሽቱ 1:00 በሗላ መንቀሳቀስ እንደማይችሉ ይህን በሚያደርጉ ላይ እርምጃ እንደሚወሰድ…
#ATTENTION

ወልድያ !

የወልድያ ከተማ አስተዳደር የከተማዋን አካባቢ ወቅታዊ የጸጥታ ሁኔታ መነሻ በማድረግ ከነሐሴ 22 ቀን 2014 ዓ/ም ጀምሮ የሰዓት እላፊ ገደብ አስቀምጧል።

በዚህም ፦

• ከተመደበው የጸጥታ ኃይል በስተቀር ከምሽቱ 1:00 ሰዓት ጀምሮ እስከ ንጋቱ 12:00 ሰዓት ድረስ ማንኛውም ሰው መንቀሳቀስ #ተከልክሏል

• ለጸጥታ ስራ ስምሪት ከተሰጠው ተሽከርካሪ ውጭ ማንኛውም ተሽከርካሪ ከምሽቱ 12:00 ሰዓት ጀምሮ መንቀሳቀስ እንደማይችል ማሳሰቢያ ተላልፏል።

@tikvahethiopia