TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ🔝 

በኢትዮጵያ በአለፉት ስምንት ወራት ሁለት #ተቃራኒ የሚመስሉ ሁነቶች እየተስተዋሉ ይገኛሉ፡፡ በአንድ በኩል ዴሞክራሲ፣ የሕግ የበላይነት፣ የኢኮኖሚ ግንባታ ይታያል፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ አለመረጋጋት፣ የሰላም መናጋት፣ ሕገወጥነት፣ በግልም ሆነ በቡድን መፃዒ #እድሎች እርግጠኛ አለመሆን ይስተዋላል፡፡

🔹VOA ከፕሮፌሰር ፕርሀኑ ነጋ ጋር ያደረገውን ቆይታ ከላይ ባለው የድምፅ ፋይል አዳምጡ።
@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
የራስ ገዟ ሶማሌላንድ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው ስብሰባ ሶማሌላንድ ዓለም አቀፍ ስምምነቶችን የመፈፀም መብትን የሚደግፍ እና የሶማሊያን መንግሥት ጣልቃ ገብነትን ውድቅ የሚያደርግ ውሳኔ አሳልፏል። ሶማሌላንድን የራሴ አካል ናት የምትለውን ሶማሊያ እያቀረበች ያለውን የይገባኛል ጥያቄ #ውድቅ በማድረግም "የሶማሌላንድ ሪፐብሊክ ሉዓላዊነትና ነጻነቷ የተረጋገጠ ነው " ብሏል። የሶማሊያው…
#Update

ራስ ገዟ ሶማሌላንድ የሁለትዮሽ ስምምነት ለማድረግ " የሶማሊያ ፍቃድ "አያስፈልገኝም ፤ አልጠይቅምም " አለች።

ከሶማሊያ ተነጥላ ሶስት አስርት ዓመታት እንደሆናት የገለፀችው ሶማሌላንድ፤ ሶማሊያ የምታቀርበው " የኔ አካል ናት " የሚለው የባለቤትነት ጥያቄ ፍፁም ሀሰት ነው ስትል ገልጻለች።

የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክን በሶማሊላንድ የወደብ ተጠቃሚ ለማድረግ የተፈረመው የመግባቢያ ስምምነት አንድ ሀገር ከሌላ ሀገር ጋር ከሚደርገው #የሊዝ_ኮንትራቶች የተለየ አለመሆኑን አመልክታለች።

ራስ ገዟ ሶማሌላንድ ፤ ሶማሊያ የመግባቢያ ስምምነቱን በተመለከተ ያየዘችውን አቋም እና ያወጣቻቸውን መግለጫዎች ሁሉ #ውድቅ አድርጋለች።

ከዚህ ባለፈ ሶማሌላንድ የሁለትዮሽ ስምምነቶችን ለማድረግ የሶማሊያን ፈቃድ ትፈልጋለች የሚባል ማንኛውም ሀሳብ ፍፁም ውሸት ነው ስትል ገልጻለች።

ሶማሊላንድ ኢትዮጵያን ጨምሮ ከበርካታ ሀገራት ጋር የራሷን ነጻ የሆነ ግንኙነት ስታደርግ እንደነበርና አሁንም የምትቀጥል መሆኑን ገልጻ ከአሁኑ የመግባቢያ ስምምነት በፊት በርካታ ዓለም አቀፍ እና የሁለትዮሽ ስምምነቶችን በተሳካ ሁኔታ መፈፀሟን አስታውሳለች።

ከእነዚህ ከተፈፀሙ ዓለም አቀፍ እና የሁለትዮች ስምምነቶች መካከል አንዳቸውም ከሶማሊያ ፈቃድ አልተጠየቁም ወይም አልተቀበሉም ብላለች።

ሶማሌላንድ ባለፉት 33 ዓመታት የሶማሌላንድ እና የሶማሊያ #ተቃራኒ ሁኔታዎችን ብዙ ይናገራሉ ስትልም ገልጻለች።

ሶማሌላንድ ፤ በአፍሪካ ቀንድ የበለፀገ ዲሞክራሲ እና የመረጋጋት ምልክት ሆና የውስጥ ጉዳዮቿን፣ አስተዳደሯን እና ምርጫዋን ያለአለም አቀፍ ድጋፍ በብቃት በመምራት ላይ እንደሆነች አመልክታችለች።

" ሀገራችን እና የባህር ዳርቻዋ ያለማቋረጥ / በወጥነት ከዘረፋ፣ ከሽብርተኝነት እና ከሽፍታነት የፀዱ ናቸው። " ስትል አክላለች።

በአንፃሩ ሶማሊያ ላለፉት 33 ዓመታት ከውስጥ ሽኩቻ፣ ሙስና እና ሽብርተኝነት ጋር ስትታገል፣ በዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ዘንድ በተደጋጋሚ " የወደቀች / የከሸፈች ሀገር " ስትባል እንደነበር እና ለራሷ ጥበቃ የዓለም አቀፍ ሰላም አስከባሪ ሃይል ያስፈለጋት ሀገር መሆኗን ሶማሌላንድ ገልጻለች።

" ሶማሊያ ብዙ ጊዜ ' ብርቅዬ አፍሪካዊ ተአምር ' እየተባለች በሚነገርላት በሶማሌላንድ ላይ ያልተገባ አረዳድ እንዲኖር ከማድረግና መሠረተ ቢስ የባለቤትነት ጥያቄ ከማቅረብ ይልቅ፣ የራሷን ቤት ብታስተካክል ይመረጣል " ብላለች።

" እርግጥ ነው፣ ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ በሁለቱ አካላት መካከል ያለውን ከፍተኛ ልዩነት ይገነዘባል " ያለችው ሶማሌላንድ " እኛ ለአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ሰላምና መረጋጋት የምናደርገውን አስተዋጽኦ ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ የሚያደንቀው ነው " ስትል ገልጻለች።

ሶማሌላንድ እንደፈለገችው በነፃነት ዓለም አቀፍ ግንኙነት የመመሥረት ሉዓላዊ መብቷን ከማስጠበቅ ወደ ኋላ ባትልም፣ ከሶማሊያ ጋር እንደ #ጎረቤት ገንቢ ውይይት ለማድረግና ሰላማዊ በሆነ መንገድ አብሮ ለመኖር ቁርጠኛ ነኝ ብላለች።

ሶማሊያ ፤ እንደ አንድ የራሷ ግዛት በምትቆጥራት ሶማሌላንድ እና በኢትዮጵያ መካከል የተፈረመውን ስምምነት " ዋጋቢስ " በማለት ውድቅ ያደረገች ሲሆን የኢትዮጵያ ድርጊት ሉዓላዊነቴን ፣ ግዛታዊ አንድነቴ የሚዳፈር ነው ብላለች።

የሀገሪቱ ፕሬዜዳንት ሀሰን ሼክ ሞሀሙድም ስምምነቱን ተከትሎ ወደ ተለያዩ ሀገራት እና ተቋማት ጋር በመደወል ውይይት አድርገዋል።

በአሁን ሰዓት ደግሞ በኤርትራ ይፋዊ ጉብኝት እያደረጉ ሲሆን የግብፅ ፕሬዜዳንት አብዱል ፈታህ አልሲሲም ወደ ግብፅ መጥተው የስራ ጉብኝት እንዲያደርጉ ጥሪ ማቅረባቸው ተሰምቷል።

#ቲክቫህኢትዮጵያ

@tikvahethiopia