TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ሀሰተኛ የትምህርት መረጃ ...

(በዳውሮ ዞን)

በዳውሮ ዞን ፤  ከጪ በተባለው ወረዳ ለመጀመሪያ ዙር በተደረገ ማጣራት ከ264 የትምህርት መረጃ 127 #ሀሰተኛ ሆኖ መገኘቱ ተሰምቷል።

ሀሰተኛ ሆኖ ከተገኘው የትምህርት መረጃ መካከል 6ቱ #የአመራርና ቀሪው #የመንግስት_ሰራተኞች ነው።

የሁለተኛ ዙሪ የማጥራት ስራ እንደሚቀጥል ተገልጿል።

በዚሁ ዞን ፤ ቶጫ በተባለው ወረዳ በመጀመሪያ ዙር ከተደረገው ማጣራት ከ565 የትምህርት መረጃ የ218 ሰዎች #ሀሰተኛ ሆኖ ተገኝቷል።

መረጃቸው ወደ ግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ተልኮ ከተጣራው ከ565 የመንግስት ሰራተኞች መካካል የ210 ባለሙያዎችና የ8 #አመራሮች የትምህርት መረጃ ነው ሀሰተኛ ሆኖ የተገኘው።

ይኸው የማጣራት ስራ ይቀጥላል ተብሏል።

መረጃው ከዳውሮ ኮሚኒኬሽን የተገኘ ነው።

@tikvahethiopia