TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#እንድታውቁት

በዝርፊያ ምክንያት ኃይል ተቋርጧል።

ከጣና በለስ ኃይል ማመንጫ ወደ ጃዊ የተዘረጋው ባለ 132 ኪሎ ቮልት የከፍተኛ የኤሌትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎች #በሌቦች በመፈታታቸው ኃይል መቋረጡ ተገልጿል።

ይህንን ያሳወቀው የሰሜን ምዕራብ ሪጅን የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን መምሪያ ነው።

ዝርፊያው የተፈፀመው አይማ ገብርኤል ቀበሌ ጌሾ ወንዝ አካባቢ ነው።

ሦስት የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎች በሌባ በመፈታታታቸው የወደቁ ሲሆን አንድ ተጨማሪ ምሰሶ በመሳሳብ ጉዳት ደርሶበት ወድቋል።

በዚህ የተነሳ ፦ ለበለስ ስኳር ፕሮጅክት፤ ለጃዊና አካባቢው የሚሰጠው የጃዊ ኤሌትሪክ ማከፋፈያ ጣቢያ የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦቱ ከጥቅምት 20 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ ተቋርጧል።

የወደቁትን ምሰሶዎች ለመጠገን የቴክኒክ ቡድን በሥፍራው ደርሶ ጥገና የጀመረ ሲሆን ጥገናውን ለማጠናቀቅ እስከ #አንድ_ሳምንት ሊፈጅ ይችላል ተብሏል።

ህብረተሰቡ የደረሰ ጉዳት እስኪጠገን በትዕግስት እንዲጠብቅ ዘራፊዎችን ለፀጥታ አካላት እንዲጠቁም ጥሪ ቀርቧል።

ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል

@tikvahethiopia