TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#Update የኢፌዴሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት #ነገ በሚያካሂደው መደበኛ ስብሰባው ለኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ አዲስ ሰብሳቢን #ይሾማል ተብሎ ይጠበቃል።

Via-ENA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ለሁሉም የTIKVAH-ETH ቤተሰብ አባላት በሙሉ፦

▪️ጥር 1 እስከ ጥር 21-TIKVAH-ETH▪️

የሰላም፣ የፍቅር እና አንድነት ሳምንታትን በመላው ሀገሪቱ አውጀን የተለያዩ እንቅስቃሴዎችን እያደረግን እንገኛለን። በፌስቡክ ላይ ተፅእኖ እንዲፈጠር እያደረጋችሁት ላለው ትልቅ ስራ ምስጋና ይገባችኃል።

#ነገ_ሰኞ ሁሉም የቤተሰባችን አባል ተከታዮቹን ስራዎች እንዲሰራ በታላቅ ትህትና እንለምናለን፦

•ሰራተኞች ወደስራ ከመግባታችሁ በፊት አንዳች መልካም ስራ እንድትሰሩ፦ በጎዳና ላይ ካሉ አቅም ከሌላቸ ወገኖች አንዱን እንኳን ቁርስ ብታበሉ። አልያም እናተ ለአእምሯቹ ደስታን የሚሰጣችሁን መልካም ስራ ብትሰሩ። ስራ ቦታ በሚኖራችሁ የእረፍት ጊዜ በሀገራችን ሰላም ማስጠበቅ ዙሪያ ከጓደኞቻችሁ ጋር ውይይት ብታደርጉ።

•የታክሲ ሹፌሮች በስራ እንቅስቃሴያችሁ ሰላም እና አንድነትን የሚያጎለብቱ ሙዚቃዎችን ለተሳፋሪዎች በመክፈት ተፅእኖ እድትፈጥሩ። ተሰብስባችሁ ምሳ በምትመግቡበት ወቅት ስለሰላም እና አንድነት እንድትመክሩ።

•ተማሪዎች በእረፍት ጊዚያችሁ ስለሰላም እንድትነጋገሩ። በቀጣይ ሳምንታት በተለያዩ መልካም ስራዎች ላይ ስለመሳተፍ ብትመክሩ። (በቡድን ሆናችሁ ደም ልገሳ፣ ህሙማንን መጠየቅ፣ የተቸገሩትን መርዳት...)

🔹ሁላችንም በፌስቡክ ብሄር ተኮር የጥላቻ መልዕክቶችን እና ግጭት ቀስቃሽ መልዕክቶችን የሚያስተላልፉ ገለሰቦችን #Block ማድረጋችንን አጠናክረን እንቀጥላልን!!

🙏መልዕክቱ ተፈፃሚ እንደሚሆን ባለሙሉ ተስፋ ነን!! በቤተሰባችን አፍረን አናውቅም!!🙏
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update የኬንያው ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ በኢትዮጵያ ይፋዊ የስራ ጉብኝት ለማድረግ #ነገ የካቲት 22 ቀን 2011 ዓ.ም አዲስ አበባ ይገባሉ።

Via ENA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ባለፈው እሁድ መጋቢት 1 ቀን፤ 2011 ዓ.ም ቢሾፍቱ አቅራቢያ የተከሰከሰው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ቦይንግ 737 ማክስ 8 አውሮፕላን የመረጃ ማከማቻ ሳጥኖች ላይ የሚካሄደው ምርመራ #ነገ እንደሚጀመር የፈረንሳይ የበረራ ደኅንነት ምርመራ ባለሥልጣን (Bureau d'Enquêtes & d'Analyses) ዐስታወቀ። ባለሥልጣኑ በትዊተር ገጹ እንዳሳወቀው የኢትዮጵያ የአደጋ ምርመራ ቡድን አደጋ የደረሰበትን አውሮፕላን የበረራ መረጃ መመዝገቢያ እና የአብራሪዎች ክፍል የድምጽ መቅጃ መሳሪያዎችን ይዞ ዛሬ ባለሥልጣኑ መሥሪያ ቤት ደርሷል። በአሁኑ ጊዜም እንዴት ተቀናጅተው መሥራት እንዳለባቸው እየመከሩ ነው። የምርመራው የመጀመሪያ ደረጃ ውጤት ላይ ለመድረስ ቀናት ሊወስድ እንደሚችል ባለሥልጣኑ ዐስታውቋል።

Via ዶቼ ቨለ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#NewsAlert የባሕር ዳር ኢንዱስትሪ ፓርክ ሙሉ በሙሉ ለባለሀብቶች ሊሰጥ ነው፡፡ ከሆንግ ኮንግ የመጡ የባለሀብቶች ቡድን አባላት የኢንዱስትሪ ፓርኩን #ነገ እንደሚረከቡ ታውቋል፡፡

Via #AMMA
🗞ቀን ሃምሌ 2/2011 ዓ/ም
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ጅግጅጋ ዝግጅቷን አጠናቃ እንግዶችን እየተቀበለች ነው። #የኦሮሚያ እና #የሶማሌ ክልል የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት መድረክ #ነገ ይካሄዳል።

ፎቶ፦ Mame/TIKVAH-ETH
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#AddisAbeba

በአዲስ አበባ ወጣቶች ፌደሬሽን አስተባባሪነት #ነገ መስከረም 24 በአዲስ አበባ ከተማ የሚከበረውን የእሬቻ በዓል ምክንያት በማድረግ ከከተማዋ የተለያዩ ክፍሎች የተሰባሰቡ ወጣቶች መስቀል አደባባይ እና አካባቢውን አፅድተዋል፡፡

ከ3 ሺህ በላይ ወጣቶች የተሳተፉበት የፅዳት ዘመቻ በዛሬው ዕለት ከጠዋቱ 12 ሰዓት ጀምሮ የተካሄደ ሲሆን በነገው ዕለትም በዓሉ ከተከበረ በኋላ ከቀኑ 10 ሰዓት ጀምሮ የፅዳት ዘመቻው ይካሄዳል ተብሏል፡፡

የፅዳት ዘመቻው ከ10ሩም ክፍለ ከተሞች ከሚገኙ የወጣት ፌደሬሽን አመራሮች ጋር በመሆን የአዲስ አበባ ወጣቶች ፌደሬሽን እያስተባበረው ይገኛል፡፡

Via #FBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ጥብቅ ማሳሰቢያ!

በኳታር ነዋሪ የሆናችሁ የኢትዮጵያ ዜጎች የኳታር መንግስት ያስቀመጠው የNational Address የምዝገባ ቀነ ገደብ #ነገ ይጠናቀቃል።

መንግስት ሊወስድ ከሚችለው ማንኛውም እርምጃ ራሳችሁን ለመጠበቅ እስካሁን መረጃውን ያልሞላችሁ ምዝገባውን በ #Metrash2 የሞባይል መተግበሪያ ወይም በአገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴር ድረ ገጽ www.moi.gov.qa አማካኝነት እንድታከናውኑ በዶሃ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ በጥብቅ አሳስቧል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopiaOfficial
#DrAbiyAhmed

ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ነገ ሁሉም የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች ነገ ክፍት ሆነው አገልግሎት እንዲሰጡ አሳስበዋል።

ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ ፥ ባለፈው ሳምንት ለ6ኛው ብሔራዊ ምርጫ ሰኞ በሚዘጉ የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች ምትክ ቅዳሜ የሥራ ቀን እንደሚሆን አሳውቀው እንደነበር አስታውሰዋል።

በዚህም #ነገ ሰኔ 19/2013 ሁሉም መንግሥት መሥሪያ ቤቶች ክፍት ሆነው አገልግሎት እንዲሰጡ ማሳሰቢያ አስተላልፈዋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" አጠቃላይ ሂደቱ ህግን የተከተለ ነበር " ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ትላንት ምሽት የአሜሪካ ጉዟቸውን ለማድረግ በአዲስ አበባ ኤርፖርት በተገኙበት ወቅት " ከቅዱስነታቸው ጋር ሕገ ወጥ ቅርስ ከሀገር ሊሸሽ ሲል ተያዘ " እየተባለ በማህበራዊ ሚዲያ የሚሰራጨው መረጃ ሀሰተኛ መሆኑ ተገልጿል። ቅዱስነታቸው…
#ነገ_መግለጫ_ይሰጣል !

በቅዱስ ፓትርያርኩ ጉዞ ላይ በቦሌ ኤርፖርት በተፈፀመው አሳዛኝ ድርጊት ጋር ተያይዞ ብፁዕ አቡነ አብርሃም የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ እና የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በነገው ዕለት ቀን 8:30 መግለጫ እንደሚሰጡ ታውቋል።

ብፁዕነታቸው ስለተፈፀመው ድርጊት መረጃውን እንደሰሙትና እንዳሳዘናቸው በመግለጽ ወጡ የተባሉት ጽላትና ንዋያተ ቅድሳት በሕጋዊ መንገድ መውጣታቸውንና ለዚህም ሕጋዊ ፍቃድ መያዛቸውን ተናግረዋል።

ብፁዕነታቸው አክለውም ይህ ለአዳዲስ አብያተ ክርስቲያናትም ሆነ ድርብ ለሚፈልጉ አብያተ ክርስቲያናት በሀገረ ስብከታቸው ጥያቄ መሰረት በመንበረ ፓትርያርክ ፍቃድ የሚሰጥ አስቀድሞ የነበረ የቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን አሠራር ነው ብለዋል።

#EOTC_TV

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#አዲስአበባ #ነዳጅ የኢትዮጵያ ነዳጅ አዳዮች ማህበር ፥ በአዲስ አበባ ከተማ የነዳጅ ዕጥረት መከሰቱንና ምክንያቱ ደግሞ ጅቡቲ ላይ የዘነበ ከባድ ዝናብን ተከትሎ የመንገድ መቆራረጥ በመፈጠሩ መሆኑን ገልጿል። በተጨማሪም አስቀድሞም ከቦታዉ በበቂ ሁኔታ ነዳጅ እየተጫነ ባለመሆኑ መሆኑን አመልክቷል። የማህበሩ የቦርድ አባል አቶ ደሳለኝ አበባየሁ ፥ እነዚህ ምክንያቶች ከነዳጅ አቅራቢ ኩባንያዎች የተነገራቸዉ…
#ነዳጅ

" እስከ ነገ ጠዋት ድረስ ችግሩ ይቀረፋል " - የኢትዮጵያ ነዳጅ አቅራቢ ድርጅት

የኢትዮጵያ ነዳጅ አቅራቢ ድርጅት ፥ በአዲስ አበባ የነዳጅ እጥረት የተፈጠረው ጅቡቲ ላይ የዘነበውን ከባድ ዝናብ ተከትሎ ድልድይ በመሰበሩ ነው ብሏል።

በተጨማሪም ነዳጅ የጫነ አንድ የነዳጅ ቦቴ ተገልብጦ መንገድ መዘጋጋት በማስከተሉ የነዳጅ እጥረት መከሰቱን ገልጿል።

ችግሩን ለመቅረፍ ነዳጅ የጫኑ ቦቴዎች በድሬደዋ በኩል እንዲገቡ መደረጉን የገለጸው ድርጅቱ ይሄንኑ ተከትሎ ትናንት ከሰአት ጀምሮ ነዳጅ የጫኑ ቦቴዎች መግባት መጀመራቸውን አሳውቋል።

#ዛሬ እና #ነገ ነዳጅ የጫኑ ተጨማሪ ቦቴዎች እንደሚገቡና ችግሩ እስከ ነገ ጠዋት ድረስ እንደሚቀረፍ ለብሄራዊ የቴሌቪዥን ጣቢያ በሰጠው ቃል ገልጿል።

ከሰሞኑን በአዲስ አበባ ነዳጅ ማግኘት አስቸጋሪ ሆኗል። አሽከርካሪዎች ነዳጅ ለማግኘት እጅግ ረጅም ሰልፍ ለመጠበቅ እየተገደዱ ሲሆን በዚህ ምክንያት ስራቸውም እየተስተጓጎለ ነው።

@tikvahethiopia