TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ኑ ምርቃትዎን ከእኛ ጋር! ሀምሌ 21 በአበበች ጎበና ሕፃናት እንክብካቤና ልማት ድርጅት አብረን እናክብር። #ቲክቫህ_ኢትዮጵያ

በጎ ማድረግን ከበጎዋ እናት በተግባር ይማራሉ!
#እንገናኝ

#TIKVAH_ETHIOPIA🎂2⃣
Audio
AudioLab
የተቀዳሚ ሙፍቲ ሃጂ ዑመር እንድሪስ መልዕክት ለወጣቶች፦

- የበላዩ የበታቹን ማወያየት አለበት፣ ማዳመጥ፣ መስማት ይገባል፡፡ ጥሩ ሀሳብ ከሆነ መከተል ነው፡፡ የበታቹ ደግሞ የበላዩን ሊያከብር ሊሰማ ይገባል፡፡ እስልምናው ይህንን ያዛል፡፡

- ጥቅም የሚገኘው ከአንድነት ነው፣ ጥቅም የሚገኘው ከሰላም ነው፣ ጥቅም የሚገኘው ከመከበር ነው፣ ጥቅም የሚገኘው ከመተባበር ከመረዳዳት ከመሰማማት ነው፡፡

- የሚጠቅመው መቀራረብ መመካከር መረዳዳት አላግባብ እንደሆነ መመለስ መጸጸት ወደፊት አንድነቱን ማጠንከር ሰላሙን ማጎልበት ማጠንከር ነው፡፡

#ቲክቫህ_ኢትዮጵያ
@tikvahetiopia @tsegabwolde
"በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ዘላቂ ሰላምን መገንባት!" በሚል ርዕስ ሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ከኢንሼቲቭ አፍሪካ ጋር በመተባበር የተዘጋጀው መርኃግብር ነገ በUNECA መሰብሰቢያ አዳራሽ ይካሄዳል፡፡ በኮንፍረንሱ ላይ የሁሉም የዩኒቨርስቲ ፕሬዝዳንቶች፣ የተማሪዎች ህብረት ተወካዮችና የሰላም ፎረም አባላት ይገኙበታል፡፡ የTIKVAH-ETH ቤተሰቦችም ባለፈው ዓመት በተለያዩ ዩኒቨርስቲዎች ባካሄዱት "የጥላቻ ንግግር እናቁም!" ዘመቻ ምክንያት በዚህ ስብሰባ ላይ የሚገኙ ይሆናል፡፡

#ቲክቫህ_ኢትዮጵያ
@tikvahethiopia @tsegabwolde
ምንም ሁኔታዎች ባይመቹም ከበጎነት ወደኋላ የሚመልሰን ነገር አይኖርም!

#ቅዳሜን_ደሜን_ለወገኔ

ዶ/ር ሜላት ሰለሞን እባላለሁ፡፡ እኔ O+ በጎ ፈቃደኛ ደም ለጋሽ ነኝ። ለ9ነኛ ጊዜ ደም ለግሻለሁ። ደም በመለገስ ክቡር የሆነውን የሰው ልጅ ህይወትማዳን እንደሚቻል ተረድቻለሁ፡፡ ደም በመለገስ የሚያገኙትን የደስታ ጥግ የትም ፣ ምንም ላይ አያገኙትም ! ደም መለገስ ከየትኛውም ደግነት፣ ከየትኛውም ሩህ ሩህነት ይልቃል፡፡ዛሬ ጥቅምት 15 በሚደረገው የደም ልገሳ ላይ ይሳተፉ!

እርሶስ ደም ለግሰዋል?

#ቲክቫህ_ኢትዮጵያ
@tikvahethiopia @tsegabwolde
“ሁላችንም አንድ እንሁን፣ #ሰላም እናስፍን፣ ከእንደዚህ አይነቱና አላህ ከማይወደው ተግባር እንራቅ፣ እስላም ክርስቲያኑ ሁሉ በአንድ ሆነን አገራችንን እናልማ፣ ሰላም እንፍጠር፣ ከመተላለቅ እንዳን። እባካችሁ ሁላችንም ለአላህ ብለን ከዚህ ተግባር እንቆጠብ...ሰላም ማጣታችን ያሳዝናል። ፍቅር ማጣታችን ያሳዝናል። ኡለማዎችንን ማስለቀሳችን ያሳዝናል። አንድነት ማጣታችን ያሳዝናል። አሁን #አንድ_ሆነን_ቆራጥ ሆነን ልንነሳ ይገባል። አንድ እንሁን፤ የከተማውም የገጠሩም እስላም እና ክርስቲያኑም አንድ እንሁን። አንድ ሆነን ቆራጥ ሆነን እንነሳ። እውነቱም ይታወቃል፤ ውሸቱም ይታወቃል። ለእውነት እንድትሰሩ አሳስባለሁ። አደራም እላለሁ። አሚን።” ሀጂ ኡመር ሙፍቲ (ኢትዮጵያ የእስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት (መጅሊስ) ፕሬዚዳንት )

#share #ሼር

#ቲክቫህ_ኢትዮጵያ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
Vote!

ፍሬወይኒ መብራቶም የ2019 CNN Hero ምርጥ አስር ውስጥ ገብታለች፡፡ ለዚህም የበቃችው የሚታጠብና መልሶ ጥቅም ላይ መዋል የሚችል የሴቶች የንጽህና መጠበቂያ (ሞዲየስ) በመስራቷና ሴቶች ተማሪዎች ተፈጥሯዊ በሆነው የወር አበባ ምክንያት ትምህርታቸውን እንዳያቋርጡ በምትሰጠው የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዋ ነው፡፡ እንደ ዩኒሴፍ ጥናት በኢትዮጵያ ከ10 ሴቶች አንዷ በዚህ ምክንያት ትምህርቷን ታቋርጣለች፡፡ ፍሬወይኒ ይህንን ውድድር ካሸነፈች 100,000 የአሜሪካን ዶላር አሸናፊ ትሆናለች፡፡

ምረጧት 👉 https://edition.cnn.com/SPECIALS/cnn.heroes/vote/10/

የድምጽ አሰጣጥ ሂደት:
1. ሊንኩን (ማስፈንጠሪያውን) መጫን። ከተጫን ነው ቡሃላ ውደድ የCNN የአመቱ 10 ጀግኖች ዝርዝር እንግርባለን ከዛ የፍሬወይን መብራቶም ስምችና ፎቶዋ ዜግነት Ethiopian የሚል ፈልገን እንጫናለኝ።
2. የሷን ፎቶ ከተጫንን ቡሃላ ዝቅ ብለን ከሷ ፎቶ በታች 1 or 0 ቁጥር ይኖራል vote ከሚለው በላይ slide for more ከሚለው በታች የለቸውን መሳቢያ ወደቀኝ በመሳብ 10 ድምጽ መስጠት ይችላሉ።
3. Vote የሚለውን ከተጫንን ቡሃላ email or fb account ያለን ብቻ ነው የምን መርጠው ከላይ አንብባቿል ዲስኮርሱን የሚል ሲመጣ ማንበብ ወይም አንቢብያለሁ ማለት ከዛ account ይጠይቀናል እናስገባና ማረጋገጫውን እንጫን ከዛ አበቃ።

ማሳሰቢያ:- ሁሉም ሰው በየቀኑ 10 ድምጽ መስጠት ይችላል። ማብቂያው ህዳር 21 ነው፡፡

#ቲክቫህ_ኢትዮጵያ(@tikvahethmagazine)
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#CONGRATULATIONS

በአሁን ሰዓት "ጎንደር ዩኒቨርስቲ" የህክምና ተማሪዎቹን በደማቅ ሁኔታ እያስመረቀ ይገኛል፡፡ በምርቃት ስነ ስርዓቱ ላይ የተማሪ ወላጆች፣ የዩኒቨርሲቲው አመራሮችን ጨምሮ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።

#ቲክቫህ_ኢትዮጵያ

@tikvahethmagazine
#SolveITAccelerator

5 ሚሊዮን ብር ለሥራ ጀማሪዎች ማጠናከሪያ!

iCog labs,JICA ከኩዱ ቬንቸር በተገኘው የ5,000,000 ብር [አምስት ሚሊዮን ብር] የገንዘብ ድጋፍ ሥራ ላይ ያሉ እና ምርትና አገልግሎታቸውን ማሳደግ ለሚፈልጉ እንዲሁም በቴክኖሎጂ ላይ ለተሰማሩ ሰባት ድርጅቶች የአቅም ማበልጸግ ፣ የገበያ ትስስር መፍጠር እና በትንሹ 250,000 ብር ከፍ ካለ እንደ ፕሮጀክቱ ታይቶ የሚጨመር ድጋፍ ለመስጠት ጀምሯል።

የፕሮጀክቱ ማናጀር የሆኑት አቶ ህሩይ ፀጋዬ እንደገለጹት ሥራ ጀማሪዎቹ ከፕሮግራሙ ጋር በሚኖራቸው ቆይታ ማርኬቲንግ እና ቢዝነስ ፕላናቸውን ይበልጥ እንዲያሻሽሉ የሚደረግ ይሆናል።

ከ7ቱ ፕሮጀክቶች መካከል 5ቱን በመውሰድ 10 ቀን የሚቆይ የውጭ ሀገር ልምድ ልውውጥ እና የሚያስፈልጋቸው የገንዘብ ድጋፍ ተደርጎላቸው ወደ ገበያው እንዲገቡ ይደረጋል ብለዋል፡፡

"ይህንን መሰሉን ሥራ ስንሰራ በዋናነት ማወቅ የምንፈልገው የቴክኖሎጂው ዘርፍ በኢትዮጵያ ምን አይነት ደረጃ ላይ ደርሷል የሚለውን ነው" ያሉት አቶ ህሩይ "የወጣቱን አቅም ማጎልበትና ትርፋማ ማድረግም ሌላው ትኩረት የምንሰጠው ጉዳይ ነው" ብለዋል፡፡

በዚህ ስራ ላይ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳድር ፣ የከተሞች የስራ ዕድል ፈጠራ እና የምግብ ዋስትና ኤጀንሲና ጥቃቅ እና አነስተኛ ኢንተርፕራይዝ በአጋርነት ይሰራሉ ተብሏል፡፡

#ቲክቫህ_ኢትዮጵያ

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ሚዲያ የሩዋንዳውን የዘር ጭፍጨፋ (ጄኖሳይድ) እንዴት አቀጣጠለ ? በ100 ቀናት ከ800,000 እስከ 1,000,000 ቱትሲዎችና ለዘብተኛ የሚባሉ ሁቱዎች ባለቁበት የሩዋንዳው የዘር ጭፍጨፋ/ጄኖሳይድ ሚዲያዎች ከፍተኛ ድርሻ ነበራቸው። እንዴት ? - ራዲዮ-ቴሌቭዥን ሊብሬስ ዴስ ሚልስ ኮሊንስ (RTML) እንዲሁም መንግታዊው ' ሬድዮ ሩዋንዳ ' በቱትሲዎች ላይ በመላ ሀገሪቱ ጥላቻ እንዲፈጠርና የሩዋንዳ…
#Kwibuka

" ክፍፍል እና ፅንፈኝነት ካልተገታ በማናቸውም ቦታ ወደ ዘር ማጥፋት ሊያመራ ይችላል " - ፖል ካጋሜ

ከ30 ዓመታት በፊት በሩዋንዳ በ100 ቀናት ብቻ እስከ 1,000,000 ሚደርሱ ሰዎች የተጨፈጨፉበት የሩዋንዳ ዘር ፍጅት እየታሰበ ይገኛል።

የዘር ፍጅቱ የተፈፀመበትን 100 ቀናት ታሳቢ በማድረግ ከሚያዚያ 7 (እ.ኤ.አ) አንስቶ ለ100 ቀናት የዘር ጭፍጨፋው ሰለባዎች ይታሰባሉ ፤ ይህም ኪውቡካ /Kwibuka/ ይባለል።

ከሳምንት በፊት በኪጋሊ በነበረ ስነስርዓት ላይ ፕሬዜዳንት ፖል ካጋሜ ፤ ከዘር ፍጅቱ በህይወት የተረፉ ዜጎች ለብሄራዊ አንድነት ሲሉ ስላደረጉት ጥረት ምስጋና አቅርበዋል።

" እጅግ የሚከብደውን የእርቀ ሰላም ሸክም እናተ እንድትሸከሙ ጠየቅናችሁ እንሆ ለሀገራችን ስትሉ ይሄንን በየቀኑ ማድረጋችሁን ቀጥላችኃል ስለዚህ እናመሰግናችኃለን " ነው ያሉት።

ፖል ካጋሜ ፥ አሁንም ድረስ በአንዳንድ የአፍሪካ ሀገራት #የጎሳ_ፖለቲካ እየተባባሰ መሄዱን እና የብሄረሰብ ማጽዳት አደጋ መደቀኑን በማንሳት አስጠንቅቀዋል።

" ሩዋንዳ ውስጥ የደረሰው መከራ ማስጠንቀቂያ ሊሆን ይገባል። ክፍፍል እና ፅንፈኝነት ካልተገታ በማናቸውም ቦታ ወደ ዘር ማጥፋት ሊያመራ ይችላል " ብለዋል።

ሩዋንዳ መከራ ውስጥ በገባችበት ጊዜ በርካታ ሀገራት የሰላም አስከባሪ ልጆቻቸውን ሩዋንዳ መላካቸውን እና እነዛም ወታደሮች ለሩዋንዳ እንደደረሱላት ገልጸዋል።

" ነገር ግን #በጥላቻም ይሁን #በፍራቻ ያልደረሰልን ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ነው " ሲሉ ተናግረዋል።

በሩዋንዳው የዘር ጭፍጨፋ በወቅቱ በነበረው የሁቱ መንግሥት መሪነትና የሁቱ ብሄረሰብ አባላት በሆኑ ጽንፈኛ አክራሪዎች እንዲሁም በመንግሥት በሚደገፈው የ " ኢንተርሀምዌ '  ሚሊሻ አማካኝነት እስከ 1,000,000 ቱትሲዎች ፣ ለዘብተኛ ሁቱዎችና ትዋዎች ተጨፍጭፈዋል።

Rwandan genocide
Apr 7, 1994 – Jul 15, 1994
AP / VOA

#ቲክቫህ_ኢትዮጵያ

@tikvahethiopia
#ኢትዮጵያ2017

እንኳን ለአዲሱ ዓመት አደረሰን !

ፈጣሪ አዲሱን ዓመት ፦
- የሰላም
- የፍቅር
- የአንድነት
- ከተፈጥሮ ውጭ የሆነ የሰው ልጅ ሞት የማንሰማበት
- ደመ የማይፈስበት
- ሰው ታገተ፣ ተገደለ፣ ታፈነ የሚል ቅስምን ሰባሪ ዜና የማንሰማበት
- በመላ ሀገሪቱ ፍጹም እርጋታ ያለበት
- እናት የማታለቅስበት
- ሰው ወጥቶ ቀረ የማይባልበት
- ፍትሕ ለተነፈጉ ሁሉ ፍትህ የሚሰፍንበት
- ፍትሕ አጥተው የሚያነቡ ፍትሕ አግኝተው እንባቸው የሚታበስበት
- እየፈተነን ያለው የኑሮ ጫና መፍትሄ የሚያገኝበት
- በሰላም በነጻነት ያሻን ቦታ ወጥተን የምንገባበት
- በሁላችንም ዘንድ የማያስማሙን ጉዳዮች መፍትሄ የሚያገኙበት
- እርስ በእርስ ልክ እንደጠላት የማንተያይበት ፣ የማንሰዳደብበት
- እሮሮ፣ ስቃይ በደል የማንሰማበት
- ያዘንን ተስፋ የቆረጥን ፤ የምንጽናናበት ተስፋ የምናደርግበት
- ሰራተኞች ፣ ተማሪዎች ፍጹም የተሳካ ዓመት የሚያሳልፉበት
- ከምንም በላይ በሀገራችን የትኛውም ቦታ ሰላም ተረጋግጦ ፣ ስምምነት መጥቶ በሀገራችን ፍጹም ደስታ የምናገኝበት
- ሁሉም በአንድ መንፈስ ለእናት ሀገሩ " አለሁልሽ " ብሎ የሚቆምበት ያደርግል ዘንድ #ቲክቫህ_ኢትዮጵያ ይመኛል።

ፈጣሪ ምኞታችንን ያሳካልን !

መልካም አዲስ ዓመት !
ከዓመት ዓመት ያደረሰን ፈጣሪ ቀጣዩን እንድናይ ይርዳን !
ለሁላችሁም ረጅም እድሜን ከጤና ጋር እንመኛለን !

#TikvahEthiopiaFamily
#ቲክቫህኢትዮጵያቤተሰቦች

@tikvahethiopia