TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ሰበር ዜና‼️ የጠ/ሚ ዶክተር #አብይ_አህመድ በአፍሪካ የመጀመሪያ የሆነውን 50 % በሴቶች የተዋቀረ ካቢኔ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በሙሉ ድምፅ #ፀድቋል

#TIKVAHETHIOPIA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ስልጤ_ዞን በዛሬው ዕለት የስልጤ ዞን ምክር ቤት መደበኛ ጉባዔዉን ማካሄድ ጀምሯል። ጉባኤው ሁለት ቀናት የሚቆይ ሲሆን በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ እንደሚወያይ ተገልጿል። ምክር ቤቱ ከሚወያይባቸው አጀንዳዎቹ መካከል ቀዳሚው #የክልል_አደረጃጀትን በተመለከተ በቀረበ መነሻ ሀሳብ ላይ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል። ትላንት የከምባታ፣ ሀላባ ፣ ሀዲያ ዞኖች እና የም ልዩ ወረዳ ምክር ቤቶች ከጉራጌ እና ስልጤ…
#Update #ፀድቋል

የስልጤ ዞን ም/ቤት የክልል አደረጃጀት ጥያቄን ለመመለስ በመፍትሄነት የቀረበዉን የዉሳኔ ሀሳብ ተቀብሎ አጽድቋል።

የዞኑ ም/ ቤት የክልል አደረጃጀት ጥያቄን ለመመለስ በመፍትሄነት የቀረበዉን መነሻ ሀሳብ ይኸውም ፦
- ስልጤ፣
- ጉራጌ፣
- ሀዲያ፣
- ካምባታ ጠምባሮ ፣
- ሀለባ ዞኖችና የም ልዩ ወረዳ አንድ ላይ ይደራጁ የሚለዉን መነሻ የዉሳኔ ሀሳብ በአንድ ተቃዉሞ በአብላጫ ድምጽ ተቀብሎ ማፅደቁን ለማወቅ ተችሏል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#NEBE የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በደቡብ ብሔር ብሔረሰቦች ክልል ሥር በሚገኙ ስድስት ዞኖች እና አምስት ልዩ ወረዳዎች የተካሄደው የሕዝበ-ውሳኔ ድምፅ ጊዜያዊ ውጤት ለህዝብ ይፋ መደረጉን ገልጿል። ቦርዱ የድምፅ ቆጠራው ትናንት ማታ ተጠናቆ ጊዜያዊ ውጤቱም የድምጽ አሰጣጥ በተካሄደባቸው በ31 ማዕከላት ሥር በሚገኙ 3 ሺህ 771 ምርጫ ጣቢያዎች ዛሬ ጠዋት ለህዝብ ይፋ ተደርጓል ብሏል። @tikvahethiopia
#NEBE

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ጥር 29 ቀን 2015 ዓ.ም. በደ/ብ/ብ/ሕ ክልላዊ መንግሥት ሥር በሚገኙ ስድስት ዞኖች ፦
- በኮንሶ፣
- በደቡብ ኦሞ፣
- በወላይታ፣
- በጋሞ፣
- በጌዴኦ፣
- በጎፋ እና አምስት ልዩ ወረዳዎች ማለትም ፦
• በቡርጂ፣
• በባስኬቶ፣
• በአሌ፣
• በአማሮ፣
• በዲራሼ ላይ ያካሄደውን የሕዝበ ውሣኔ ጊዜያዊ ውጤት የማዳመር ሥራ በሁሉም ዞኖችና ልዩ ወረዳዎች ላይ አጠናቆ በዞንና በልዩ ወረዳ ደረጃ ጊዜያዊ ውጤቶች ይፋ መደረጉን አስታውሷል።

ቦርዱ የመጨረሻውን ውጤት የማጣራትና የማረጋገጥ ሥራ የካቲት 6 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ አርባ ምንጭ ከተማ በሚገኘው የሕዝበ ውሣኔው ማስተባበሪያ ጽሕፈት ቤት እየሰራ እንደሚገኝ ገልጿል።

ቀደም ሲል ቦርዱ በማህበራዊ ሚዲያ ገጹ የመጨረሻውን በቦርድ የተረጋገጠ ውጤት የካቲት 8 ቀን 2015 ዓ.ም ይፋ እንደሚያደርግ የገለፀ ቢሆንም በርከት ያሉ ግድፈቶችና የምርጫ ህግ ጥሰቶች በቦርዱ የምርጫ ክትትል ቡድን እንዲሁም በምርጫ ታዛቢዎች ሪፖርት በመቅረቡ የማጣራት እና ውጤት የማረጋገጥ ስራን በታቀደበት ግዜ ለማጠናቀቅ አልተቻለም ብሏል።

በዚህም የውጤት ማጣራትና ማረጋገጥ ስራ ፦

የዲራሼ፣
አሌ፣
ደቡብ ኦሞ፣
ባስኬቶ፣
ኮንሶ
ቡርጂ ውጤቶችን የማጣራትና የማረጋገጥ ስራ ተጠናቆ ውጤታቸው በቦርዱ #ፀድቋል

በቀጣይም በቀሪዎቹ ዞኖችና ልዩ ወረዳዎች ማለትም ፦
በአማሮ፣ በወላይታ፣ በጋሞ፣ በጌዴኦ እና የጎፋ ግዜያዊ ውጤቶች የማጣራትና የማረጋገጥ ሂደት እንደተጠናቀቀ ቦርዱ ለህዝብ ይፋ የሚያደርግ ይሆናል ሲል አሳውቋል።

በቦርዱ የፀደቀውን ውጤት ከላይ ተያይዟል በተጨማሪ በዚህ ማግኘት ይቻላል : https://nebe.org.et/am/Referendum_Result

#NEBE

@tikvahethiopia
#ፀድቋል

የኢትዮጵያ ዲጂታል መታወቂያ አዋጅ በአብላጫ ድምፅ ፀደቀ።

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የኢትዮጵያ ዲጂታል መታወቂያ አዋጅን አስመልክቶ የቀረበለትን የውሳኔ ሃሳብ በአንድ ድምፀ ተአቅቦ በአብላጫ ድምፅ አጽድቋል።

የውሳኔ ሃሳቡን ያቀረቡት የሕግና ፍትሕ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ወ/ሮ እፀገነት መንግስቱ ፦ " የዲጂታል መታወቂያ ስርዓት ሁሉን አቀፍ፣ ወጥና አስተማማኝ የሀገሪቷ ነዋሪዎች የሚመዘገቡበት ሥርዓት በመዘርጋት እና የተመዝጋቢዎችን መረጃ በመያዝ የዲጂታል መታወቂያ አጠቃቀም ስርዓትን ሕጋዊ መሠረት እንዲኖረው ማድረግ ጠቀሜታው የጎላ ነው " ብለዋል።

መታወቂያውን በመጠቀም በሚሰጡ አገልግሎቶች ላይ የግልፅነትና ተጠያቂነት አሰራር ስርዓት እንዲዘረጋና የተሳለጠ አገልግሎት አሰጣጥ ስርዓት እንዲኖር አመቺ ሁኔታዎችን እንደሚፈጥር አክለዋል።

በጉዳዩ ላይ አስተያየት የሰጡ የም/ ቤቱ አባላት ፥ የዲጂታል መታወቂያውን በተጭበረበረ መንገድ በሚሰጡ ግለ-ሰቦች እና ተቋማት ላይ #የሀገር_ክሕደት ወንጀል እንደፈፀሙ ታስቦ ከበድ ያለ ቅጣት እንደሚጠብቃቸው በዝርዝር መቀመጥ አለበት ብለዋል።

ወ/ሮ እፀገነት አዋጁ ረዘም ላለ ጊዜ አገልግሎት እንዲሰጥ ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑን ገልፀው ፤ ግለሰቦችም ሆኑ ተቋማት የተጭበረበረ መታወቂያ ሰጥተው ከተገኙ ከበድ ያለ ቅጣት እንደሚጠብቃቸው እና አስተማማኝነቱም በመርህ ላይ መመስረቱን አስረድተዋል።

ምክር ቤቱ በጉዳዩ ዙሪያ ከተወያየ በኋላ ረቂቅ አዋጁን አዋጅ ቁጥር 1284/2015 አድርጎ በአንድ ድምፀ ተአቅቦ በአብላጫ ድምፅ አፅድቆታል።

ምንጭ፦ የህ/ተ/ም/ቤት

@tikvahethiopia