TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
የሀይቲ ፕሬዝዳንት ተገደሉ። የሀይቲው ፕሬዝዳንት ጆቭኔል ሞይስ ማክሰኞ ለረቡዕ አጥቢያ በግል መኖሪያ ቤታቸው ውስጥ መገደላቸው ተሰማ። የፕሬዜዳንቱ ባለቤት ጉዳት ደርሶባቸዋል። - ፕሬዚዳንቱ የተገደሉት መኖሪያ ቤታቸው ውስጥ ነው። - የፕሬዜዳንቱን ግድያ ያሳወቁት የሀገሪቱ ጊዜያዊ ጠ/ሚ ናቸው። - በሀገሪቱ የፖለቲካ አለመረጋጋት ፣ ከ2018 ጀምሮ ደግሞ በሙስና መበራከት ስልጣናቸውን እንዲለቁ የሚጠይቅ…
የሄይቲውን ፕሬዜዳት ማን ገደላቸው ?

የሄይቲ ፕሬዜዳንት ጆቭኔል ሞይስ በመኖሪያ ቤታቸው ውስጥ በተፈፀመባቸው ጥቃት መገደላቸው መገለፁ ይታወሳል።

ፕሬዝደንቱ የገደሉት 28 አባላት ያሉት ቅጥረኛ የገዳዮች ቡድን መሆኑ የሀገሪቱ ፖሊስ ስለማስታወቁ ቢቢሲ ዘግቧል።

ከእነዚህ መካከል 26ቱ #ኮለምቢያዊያን ናቸው 2ቱ ደግሞ #የአሜሪካ ዜግነት ያላቸው ሄይቲያዊያን ናቸው ሲል የሀገሪቱ ፖሊስ ለመገናኛ ብዙሃን አሳውቋል።

2ቱ አሜሪካዊያንን ጨምሮ 17 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ሥር ሲውሉ ስምንቱ ደግሞ እየታሰሱ እንደሆነ ተሰምቷል።

በሕይወት ካሉት ተጠርጣሪዎች በተጨማሪ ዋና መዲናዋ ፓርቶፕሪንስ ውስጥ ከፖሊስ ጋር በነበረ የተኩስ ልውውጥ የሞቱ እንዳሉም ታውቋል።

ጥቃቱን ማን እንዳቀደውና ዓላማው ምን እንደሆነ እስካሁን የታወቀ ነገር የለም።

ባለፈው ረቡዕ ነው የታጠቁ ሰዎች ወደ ፕሬዝደንት ጆቭኔል ሞይስ መኖሪያ ቤት ገብተው ጥቃት የፈፀሙት።

በጥቃቱ ፕሬዝደንቱ ሲገደሉ ባለቤታቸው ማርቲን ቆስለው ፍሎሪዳ ወደሚገኝ ሆስፒታል ለሕክምና ተወስደው አሁን መልካም የጤንነት ሁኔታ ላይ እንደሚገኙ ተሰምቷል።

#BBC

@tikvahethiopia