TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#Sudan #June30March

ዛሬ በሱዳን ከፍተኛ ተቃውሞ ይካሄዳል ተብሎ ይጠበቃል።

ዛሬ #June30 በጎረቤት ሱዳን በሌ/ጄነራል አብዱል ፈታህ አል ቡርሃን የሚመራውን ወታደራዊ ጁንታን በመቃወም ከፍተኛ የሆነ የተቃውሞ ሰልፍ ይካሄዳል ተብሎ ይጠበቃል።

በተቃውሞ ሰልፉ ወታደራዊው ክንፍ በመፈንቅለ መንግስት የያዘውን ስልጣን ለሲቪል አስተዳደር እንዲያስረክብ እና የሲቪል መንግስት እንዲቋቋም ይጠየቅበታል ነው የተባለው።

ተቃውሞውን ተከትሎ የፀጥታ ኃይሎች የተለያዩ መንገዶችን ዘግተዋል። በተጨማሪ የፀጥታ ኃይሎች ሰልፍ የሚያስተባብሩትን አክቲቪስቶች እያደኑ እያሰሩ ነው ተብሏል።

የሱዳን ወታደራዊ ክንፍ በመፈንቅለ መንግስት ስልጣን ከተቆጣጠረ በኃላ በሱዳን ዜጎች የሚደርስበት ተቃውሞ እስካሁን የቀጠለ ሲሆን ስልጣኑን ለሲቪል አስተዳደር እንዲያስረክብ ግፊት እየተደረገበት ይገኛል።

እስከዛሬ ድረስ በነበሩት ተቃውሞዎች የመንግስት ፀጥታ ኃይሎች በወሰዷቸው እርምጃዎች ብዙ ሰዎች ሞተዋል፤ በርካቶችም ቆስለዋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Sudan #June30March ዛሬ በሱዳን ከፍተኛ ተቃውሞ ይካሄዳል ተብሎ ይጠበቃል። ዛሬ #June30 በጎረቤት ሱዳን በሌ/ጄነራል አብዱል ፈታህ አል ቡርሃን የሚመራውን ወታደራዊ ጁንታን በመቃወም ከፍተኛ የሆነ የተቃውሞ ሰልፍ ይካሄዳል ተብሎ ይጠበቃል። በተቃውሞ ሰልፉ ወታደራዊው ክንፍ በመፈንቅለ መንግስት የያዘውን ስልጣን ለሲቪል አስተዳደር እንዲያስረክብ እና የሲቪል መንግስት እንዲቋቋም ይጠየቅበታል…
ሱዳን ኢንተርኔት ዘጋች።

ሱዳን ዛሬ ሀሙስ ከሚካሄደው ታላቁ የ #June30 የተቃውሞ ሰለፍ ጋር በተያያዘ ከጥዋት ጀምሮ የኢንተርኔት አገልግሎት አቋርጣለች።

የኢንተርኔት ጉዳይን የሚከታተለው ኔት ብሎክስ ፤ ዛሬ #June30 ሊካሄድ ከታሰበው የሱዳን ፀረ ጁንታ (ወታደራዊ አገዛዝ) ተቃውሞ እና የሲቪል አስተዳደር እንዲመሰረት ከሚጠይቀው ሰልፍ ጋር በተገናኘ የኢንተርኔት አገልግሎት መቋረጡን ገልጿል።

@tikvahethiopia