TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
ከሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ፦ ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ በላከልን መልዕክት በዛሬው ዕለት የመሰረተ ልማት መጋራት እና #በደንበኞች_መካከል_የግንኙነት_ልውውጥ ለማድረግ በሚያስችሉ ጉዳዮች ዙርያ ከበርካታ ዙር ውይይቶች በኋላ ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር ስምምነት ላይ መድረሱን ገልጾልናል። ውይይቶቹ በኢትዮጵያ ኮሚዩኒኬሽን ባለሥልጣን የተመሩ መሆኑን የገለፀው ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ባለሥልጣኑ ላሳየው ብቁ የአመራር ጥበብ ምስጋና…
ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ከምን ደረሰ ?

ሳፋሪኮ ኢትዮጵያ የቴሌኮም አገልግሎት ለመጀመር እያደረገ ስላለው እንቅስቃሴ እንዲሁም አሁናዊ የተቋሙን እንቅስቃሴ በተመለከተ በቀጣይ ሳምንት ለመገናኛ ብዙኃን መግለጫ እንደሚሰጥ አሳውቋል።

ተቋሙ ዛሬ ባሰራጨው መልዕክት ፤ " ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ አገልግሎት ሊጀምር ነው " የሚሉ፣ ቀኖች እና ሌሎች ተቋማዊ መረጃዎችን ያካተቱ ዜናዎችና መረጃዎች በማሕበራዊ ድረገጾች መውጣታቸውን እንዳስተዋለ ገልጿል።

#በያዝነው_የፈረንጆች_ዓመት ውስጥ ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀና #በሁሉም_የኢትዮጵያ_ክፍሎች ምርጥ የደንበኞች አገልግሎት ለማቅረብ የሚያስችሉትን ዝግጅቶች እያደረግ መሆኑን የገለፀው ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ለዚህም፦

- የኔትወርክ ግንባታ፣

- የሰው ኃብትን #በኢትዮጵያዊያን_ሠራተኞች ማደራጀት

- የጥራት ፍተሻዎችን እያደረገ እንደሚገኝ አሳውቋል።

በቀጣይ ሳምንት ስለተቋሙ እንቅስቃሴ ለመገናኛ ብዙኃን መግለጫ እንደሚሰጥ የገለፀ ሲሆን የአገልግሎቱን መጀመረ የሚጠባበቁ ሁሉ ትክክለኛ መረጃዎችን ከተቋሙ ትክክለኛ አድራሻ ብቻ እንዲካታተሉ መልዕክቱን አስተላልፏል።

ፎቶ ፦ ፋይል

@tikvahethiopia