TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
አጫጭር ዓለም አቀፍ መረጃዎች፦

- ሼንዠን ውሻና ድመት ለምግብነት እንዳይውሉ ያገደች የመጀመሪያዋ የቻይና ከተማ ሆናለች።

- በሊባኖስ የፊሊፒንስ አምባሳደር በኮሮና ቫይረስ [ኮቪድ-19] ተጠቅተው መሞታቸው ተሰምቷል።

- በሩስያ ተጨማሪ 6 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መሞታቸው ተሰምቷል።

- በዓለም ላይ በኮሮና ቫይረስ የተያዙ ሰዎች ቁጥር ከ950,000 በልጧል። ከ48,000 በላይ ሰዎች ሞተዋል፣ ከ200,000 በላይ ሰዎች አገግመዋል።

- በዓለም ላይ የኮቪድ-19 ተጠቂ 1 ሚሊዮን ሊደርስ በተቃረበበት ወቅት ሰሜን ኮሪያ አሁንም አንድም የኮሮና ቫይረስ ተጠቂ በሀገሬ የለም ብላለች።

- የሩዋንዳ መንግሥት የኮሮና ቫይረስ [ኮቪድ-19] ስርጭትን ለመቆጣጠር ተግባራዊ ያደረገውን ጥብቅ ከቤት ያለምውጣት ክልከላ ለተጨማሪ 3 ሳምንታት አራዝሟል።

- በአውሮፓ የኮሮና ቫይረስ ተጠቂዎች ቁጥር ግማሽ ሚሊዮን ደርሷል።

- በስፔን በኮሮና ቫይረስ የሞቱ ሰዎች ቁጥር ከ10,000 በልጣል። በ24 ሰዓት የ950 ሰዎች ሞት ተመዝግቧል።

#SkyNews #BBC #Euronews #Aljazeera

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
አጫጭር ዓለም አቀፍ መረጃዎች፦

- የሩሲያ ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን በአገሪቱ የጣሉትን በቤት የመቀመጥ ውሳኔ በአንድ ወር አራዝመዋል

- እስካሁን ቫይረሱ ሀገሯ ሳይገባ የቆየችው ማላዊ በዛሬው ዕለት ሶስት ኬዞችን ሪፖርት አድርጋለች።

- የኢራን ፓርላማ አፈጉባኤ በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል።

- በምዕራብ አፍሪካ የነበሩ 3 የፈረንሳይ ወታደሮች በኮሮና ቫይረስ መጠቃታቸው ተሰምቷል። ወታደሮቹ ወደፈረንሳይ እንዲመለሱም ተደርጓል።

- በጣልያን በ24 ሰዓት ውስጥ የ760 ሰዎች ሞት ሪፖርት ተደርጓል። አጠቃላይ የሟቾች ቁጥር 13,915 ደርሷል። በቫይረሱ የተጠቁ ሰዎች ቁጥርም ከ115,000 በልጧል።

- በአሜሪካ በኮሮና ቫይረስ የሞቱ ሰዎች ቁጥር 5,626 ደርሰዋል። 235,860 ሰዎች በቫይረሱ ተጠቅተዋል።

- በመላው ዓለም የኮሮና ቫይረስ ተጠቂዎች ቁጥር ከአንድ ሚሊዮን በልጧል። ከ51,000 በላይ ሰዎችም ሞተዋል። 210,308 ሰዎች ደግሞ አገግመዋል።

-ሳዑዲ አረቢያ የ24 ሰዓት የሰዓት እላፊ በቅዱስ ከተሞቿ ላይ ጥላለች። በመካ እና በመዲና የተጣለው የሰዓት እላፊ የኮሮናቫይረስን ስርጭት ለመከላከል ነው ተብሏል።

#SkyNews #BBC #Euronews #Aljazeera

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia