TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ፎቶ /ቪድዮ ፦ በአዲስ አበባ ከተማ ረጃጅም የታክሲ ሰልፎች እየተስተዋሉ ነው።

ነዋሪዎች ታክሲ አግኝተው ወደሚፈልጉት ጉዳይ ለመሄድ ረጅም ሰዓት ሰልፍ ለመጠበቅ ሲገደዱ ተስተውሏል።

ወቅቱ ክረምት ከመሆኑ ጋር ተያይዞ በከተማይቱ እየጣለ ያለው ከባድ ዝናብ በመሆኑ ሁኔታውን አስቸጋሪ አድርጎታል።

በተመሳሳይ በማደያዎች ላይ ረጃጅም የተሽከርካሪ ሰልፎች ታይተዋል ፤ መልዕክታቸውን የላኩ የታክሲ አገልግሎት የሚሰጡ የቤተሰባችን አባላት ፤ ነዳጅ ለማግኘት እጅግ መቸገራቸውን ገልፀዋል።

" ዛሬ እንሰራለን ነገ ነዳጅ ለመቅዳት ተሰልፈን እንውላለን " ሲሉ ነው ሁኔታውን ያስረዱት።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ጥንቃቄ " FIAS 777 " የተባለ ሰዎችን ትርፋማ አደርጋለው በሚል ከበርካቶች ኤጀንት በሚላቸው አካላት በኩል ገንዘብ ሲሰበስብ ከርሞ ዛሬ አድራሻውን ጥፍትፍት አድርጓል። #ሌሎችም፦ መሰል ስራ የሚሰሩ አሉ፤ መደረግ ስላለበት ጥንቃቄ ከዚህ በፊት ያሰራጨነውን በድጋሚ ለማቅረብ ወደድን ፦ #REPOST " የተለያዩ ገንዘብ የማግኛ ማትረፊያ መንገዶች " እየተባለ በዲጅታል ሚዲያው በኩል ከቀርብ ጊዜ…
" ወንጀል ላይ ተሳትፎ ያላቸውን አካላት በመለየት ህጋዊ እርምጃ እንዲወሰድባቸው ለማድረግ ከባለድርሻ አካላት ጋር እየሰራን ነው " - FIS

የፋይናንስ ደህንነት አገልግሎት ፥ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ አንዳንድ አካላት በአጭር ጊዜ ውስጥ ‘ትርፋማ እናደርጋለን‘ በሚል በተለያዩ የመገናኛ ዘዴዎች በሚያደርጉት የቅስቀሳ ተግባር ከህብረተሰቡ በርካታ ገንዘቦችን በተለያዩ የክፍያ አማራጮች እየሰበሰቡ እንደሆነ ገልጿል።

እነዚሁ አካላት በተለይ ማህበራዊ ሚዲያውን በመጠቀም ህብረተሰቡ ያለበት የኢኮኖሚ ጫና ተገን በማድረግ ባዘጋጁት የገንዘብ መሰብሰቢያ አማራጮች ላይ ማንኛውም ግለሰብ ገንዘብ የሚያስገባ ከሆነ ካስገባው ገንዘብ የበለጠ ትርፋማ እንደሚሆን በሚያቀርቧቸው የማሳመኛ መንገዶች ከበርካታ ሰዎች በህገ-ወጥ መንገድ ገንዘብ እየሰበሰቡ እንደሆነ አሳውቋል።

ገንዘቡን በተለያዩ የክፍያ መነገዶችን በመጠቀም ሊሰበስቡ እንደቻሉ ነው የገለፀው።

ከእነዚሁ አካላት መካከል የበርካታ ግለሰቦችን ገንዘብ ከሰበሰቡ በኋላ አድራሻቸውን በማጥፋት #የተሰወሩ አካላት እንዳሉ ከህብረተሰቡ በደረሰው ጥቆማ መረዳቱን አሳውቋል።

እነዚህ የማጭበርበር ወንጀል ላይ ተሳትፎ ያላቸውን አካላት በመለየት ህጋዊ እርምጃ እንዲወሰድባቸው ለማድረግ ከባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን ስራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝ ገልጿል።

ህብረተሰቡ ከእንደነዚህ አይነት የማጭበርበር ተግባራት ራሱን ሊጠብቅ ይገባልም ብሏል።

ማንኛውም ሰው ገንዘቡን ወጪ በማድረግ ከተለያዩ አካላት ጋር ስራዎች ለመስራት ወይም ሲሰራ በቅድሚያ አብሮ ለመስራት የተስማማው አካል በኢትዮጵያ ህጋዊ እወቅና ያለው መሆኑን፣ ትክክለኛ ማንነታቸውን አድራሻቸውን በማረጋገጥ የጥንቃቄ እርምጃ እንዲወስድ አሳስቧል።

(አድራሻ፦ የኢትዮጵያ ፋይናንስ ደህንነት አገልግሎት)

@tikvahethiopia
#DoubleA

የ “Double A QR Ethiopia” የሞባይል መተግበርያን በስልክዎ  በመጫን በትክክለኛው የ Double A  ወረቀት ካርቶን ላይ የሚገኘውን የ  QR ኮድ የሞባይል መተግበሪያውን ተጠቅመው ስካን በማድረግ ልዩ ልዩ ስጦታዎችን ይሸለሙ::

መተግበርያውን ለማውረድ:
Link: https://bit.ly/3KGYCxC  Or
https://da-cloud.advanceagro.net/index.php/s/WYovIsmE4u2Kz6y

ለተጨማሪ መረጃ: https://DoubleArewards.com/Ethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ጎረቤት ሱዳኖች የጦርነት ጉሰማ ላይ ናቸው ! የሱዳን ጦር አዛዥ እና የሃገሪቱ ሉዓላዊ የሽግግር ምክር ቤት ሊቀመንበር ሌ/ጄ አብዱል ፈታህ አል ቡርሃን ከኢትዮጵያ ድንበር አቅራቢያ የሚገኘውን የሃገራቸውን ጦር መጎብኛታቸው ተነግሯል። ቡርሀን ትንሹ ፋሻጋ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በሚገኙት አል ዑስራ እና ዋድ ኮሊ አካባቢዎች የሚገኘውን የሃገራቸውን ጦር ነው ዛሬ ሰኞ ሰኔ 20 ቀን 2014 ዓ/ም የጎበኙት፡፡…
#Update

በኢትዮጵያ እና ሱዳን ድንበር እየተካሄደ ያለው ምንድን ነው ?

በምዕራብ ጎንደር ዞን የምዕራብ አርማጨሆ ወረዳ አስተዳዳሪ የሆኑት አቶ ደሳለኝ አያና ለቢቢሲ አማርኛ አገልግሎት የሰጡት ቃል ፦

- የሱዳን ሠራዊት በኢትዮጵያ በኩል ያሉ የድንበር አካባቢዎችን በከባድ መሳሪያ ደብድቧል። ድብደባው ለቀናት የዘለቀ ነው። እስከ ትላንት ማክሰኞ ከሰዓት ድረስ ሲደበድቡ ነበር።

- ነዋሪዎች ግጭቱ ሊባባስ ይችላል የሚል ስጋት አላቸው። አንዳንዶችም በአቅራቢያ ወዳሉ አካባቢዎች የመሄድ ሃሳብ አላቸው።

- ባለፉት ሶስት ቀናት በተፈጸመው የከባድ መሳሪያ ጥቃት #በሰው_ላይ_ጉዳት_አልደረሰም። የከባድ መሳሪያዎቹ በእርሻ ቦታዎችና የግብርና ካምፖች ላይ ጉዳት አድርሰዋል።

- በሱዳን የከባድ መሳሪያ ጥቃት ምክንያት ነዋሪዎች ባለፉት ቀናት በእርሻ ማሳቸው ላይ የተለመደውን የዕለት ከዕለት ሥራቸውን ከማከናወን ተቆጥበዋል።

- የንግድና የሥራ እንቅስቃሴ ተስተጓግሏል። ሱዳንና ኢትዮጵያ የሚገናኙበት የድንበር ከተማ የሆነችው የገለባት መተላለፊያ #ተዘግቷል

- የሱዳን ክስን ተከትሎ የተለያዩ የመገናኛ ብዙኃን በሁለቱ አገራት ወታደሮች መካከል ከሰኞ ወዲህ #ጦርነት እየተካሄደ መሆኑን ሲዘግቡ የቆዩ ቢሆንም በአካባቢው ጦርነት አልተካሄደም፤ ያለው ሁኔታ ከሱዳን በኩል የሚፈጸመው የከባድ መሳሪያ ጥቃት ነው።

ያንብቡ : https://telegra.ph/BBC-06-29-2

@tikvahethiopia
#FDREDefenseForce

የመከላከያ መሃንዲስ ዋና መምሪያ ከግልገል በለስ እስከ አባይ ግድብ የሚደርሠውን መንገድ ስራ ማጠናቀቁ ተገልጿል።

ዋና መምሪያው 210 ኪ.ሜ ርዝማኔ ያለውን ሶስተኛ ደረጃ የጠጠር መንገድ ወደ ከፍተኛ ደረጃ የጠጠር መንገድ በማሳደግ ነው ስራውን ሰርቶ ያጠናቀቀው።

ለታላቁ የህዳሴ ግድብ ግንባታ የሚውሉ የተለያዩ ግብዓቶች ሲጓጓዙ በመንገድ ላይ እስከ ሁለት ሳምንት ይቆዩ የነበረ ሲሆን በተከናወነው መንገድ የማሻሻል ጥገና ስራ የግድቡ የግንባታ ግብዓቶች #በአንድ_ቀን ለመድረስ ይችላሉ ተብሏል።

ምንጭ፦ የኢትዮጵያ የሀገር መከላከያ ሰራዊት

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ፎቶ /ቪድዮ ፦ በአዲስ አበባ ከተማ ረጃጅም የታክሲ ሰልፎች እየተስተዋሉ ነው። ነዋሪዎች ታክሲ አግኝተው ወደሚፈልጉት ጉዳይ ለመሄድ ረጅም ሰዓት ሰልፍ ለመጠበቅ ሲገደዱ ተስተውሏል። ወቅቱ ክረምት ከመሆኑ ጋር ተያይዞ በከተማይቱ እየጣለ ያለው ከባድ ዝናብ በመሆኑ ሁኔታውን አስቸጋሪ አድርጎታል። በተመሳሳይ በማደያዎች ላይ ረጃጅም የተሽከርካሪ ሰልፎች ታይተዋል ፤ መልዕክታቸውን የላኩ የታክሲ አገልግሎት…
የናፍጣ እጥረት እና ምክንያቱ ምንድነው ?

ከ2 ሳምንታት ወዲህ ከፍተኛ የናፍጣ እጥረት በአዲስ አበባ ከተማ እየተፈጠረ ሲሆን ለምን እጥረቱ እንደተፈጠረ በሚሰጡት ምላሽ ላይ መንግሥትና የነዳጅ አቅራቢዎች ሊግባቡ አልቻሉም፡፡

ማደያዎችና ነዳጅ አመላላሾች እጥረቱ የተፈጠረው ከጂቡቲ የሚመጣ ነዳጅ በመጥፋቱ ነው በማለት መኪኖቻቸው ለቀናት ነዳጅ አጥተው ጂቡቲ መስመር ላይ መቆማቸውን ገልጸዋል፡፡

ቃላቸውን ለሪፖርተር ጋዜጣ የሰጡት የኢትዮጵያ ነዳጅ አዳዮች ማኅበር ቦርድ አባል ኤፍሬም ተስፋዬ " ከ2 ሳምንታት ወዲህ በተለይ የናፍጣ እጥረት ተፈጥሯል፡፡ ይህም እጥረት የተከሰተው ጂቡቲ ላይ ተቀብለን የምናመጣው ናፍጣ ስለሌለ ነው፡፡ መኪኖቻችን ለቀናት ያለሥራ እየቆሙ ነው " ብለዋል።

የነዳጅና ኢነርጂ ባለሥልጣን ኃላፊዎች ደግሞ እጥረቱን የፈጠሩት ነዳጅ አከፋፋዮችና ማደያዎች እንደሆነ ይገልጻሉ፡፡

ቃላቸውን ለሪፖርተር ጋዜጣ የሰጡት የነዳጅና እነርጂ ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ሆነው በቅርቡ የተሾሙት ወ/ሮ ሳህሬላ አብዱላሂ " ከጂቡቲ ወደ ኢትዮጵያ በየቀኑ የሚጫነው ነዳጅ ባለፉት 2 ሳምንታት ውስጥ ከፍተኛ ጭማሪ አሳይቷል፡፡ በፊት በቀን ዘጠኝ ሚሊዮን ሊትር (በአማካይ) ይገባ የበረው በዚህ ሳምንት በአማካይ 9.294 ሚሊዮን ሊትር እየባ ነው " ብለዋል።

ከጂቡቲ እየተጫነ ያለው 200 ሺሕ ሊትር ነዳጅ አዲስ አበባ ሳይደርስ በተለያየ ሰበብ መንገድ ላይ ቆይቶ እየተያዘ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ሰኞ ሰኔ 20 ቀን 2014 ዓ.ም. 10 ማደያዎች በአዲስ አበባ ውስጥ ነዳጅ እያላቸው መኪኖችን ሲመልሱ የተገኙ ሲሆን በነጋታው 14 ነዳጅ የጫኑ ቦቴዎች አፋር ውስጥ ተደብቀው መገኘታቸውን ተናግረዋል፡፡

ነዳጅ አከፋፋዮችና ማደያዎች አዲሱ የነዳጅ ምርቶች መሸጫ ተመን ከሐምሌ 1/2014 ጀምሮ መተግበር እስኪጀምር በእጃቸው ላይ የገባውን ነዳጅ ላለመሸጥ አዝማሚያ ማሳየታቸው እጥረት እየፈጠረ መሆኑ ዋናው ምክንያት እንደሆነ ተናግሯል፡፡

መንግሥት የነዳጅ ድጎማ ቀስ በቀስ ለማንሳት የወሰነው ውሳኔ ከሐምሌ 1 ቀን 2014 ዓ/ም ጀምሮ የሚገበር ሲሆን ይህም የነዳጅ ውጤቶችን ዋጋ ከፍ እንደሚያደርግ ይጠበቃል፡፡

ይህም ማለት አከፋፋዮችና ማደያዎች ከቀነ ገደቡ በፊት በድጎማ በዝቅተኛ ዋጋ የገዙትን ነዳጅ ከሐምሌ አንድ በኋላ ከፍ ባለው በአዲሱ ዋጋ ይሸጣል ማለት ነው፡፡

ድጎማው ሲነሳ በሊትር እስከ ዘጠኝ ብር ጭማሪ ሊኖር እንደሚችልና ይህም በአንድ ቦቴ እስከ 450 ሺሕ ብር ተጨማሪ ገቢ የሚያስገኝ እንደሆነ ባለሥልጣናቱ ገልጸዋል፡፡

በነዳጅ አቅራቢ ድርጅት የአቅርቦት እና ሽያጭ ኃላፊ አቶ አባይነህ አወል ፥" ዋናው የእጥረቱ ምክንያት እስከ ድጎማው መነሳት ነዳጅ ለመያዝ መሞከር (Hoarding) ነው፡፡ የመኪና እጥረትም አይደለም፡፡ ጂቡቲ ላይ መዘግየት ያጋጠመው ለአንድ ቀን ሲሆን እሱም የጂቡቲዎች በዓል ቀን ስለነበር ነው፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ የሚሸጠው ነዳጅ በየቀኑ እየቀነሰ የመጣ ሲሆን፣ ከጂቡቲ የሚጫነው ግን ጭማሪ አሳይቷል " ብለዋል።

ናፍጣ ከአጠቃላይ የነዳጅ ውጤቶች አቅርቦት ውስጥ እጥረት ሲያጋጥም አሁን የመጀመርያው ነው፡፡ አብዛኛው ጊዜ የሚፈጠረው የዲዝል እጥረት ነበር፡፡

በተለይም ማደያዎች ነዳጅን በብዛት ዴፖ ውስጥ መያዝ እየተው መምጣታቸው ለእጥረቱ አስተዋጽኦ እንዳደረገ አቶ አባይነህ ይገልጻሉ፡፡ " ማደያዎችና አከፋፋዮች ነዳጅ የሚወስዱት በብድር መሆኑ ቀርቶ በካሽ ክፈሉ ከተባሉ ወዲህ፣ የባንክ ወለድ በመፍራት ነዳጅ በብዛት ዴፖ ውስጥ መያዝ ትተዋል፡፡ "

ወ/ሮ ሳህረላ ድጎማው እስኪነሳ አንሸጥም ብለው በጫካ ውስጥ ጭምር ነዳጅ ጭነው ተደብቀው እየተያዙ ያሉትን እየፈለጉ መያዝና ነዳጅ ወደ ገበያው እንዲደርስ የማድረግ ሥራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልፀዋል።

Credit : ሪፖርተር ጋዜጣ

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#MoE ትምህርት ሚኒስቴር የፈተና ስርቆትን ለመከላከል ፈተና በኦንላይን የማስፈተን ፤ ይህ ባይሆን እንኳን ተማሪዎችን ወደ ማዕከል ዩኒቨርሲቲዎች በማስመጣት ፈተና ለመስጠት እያሰበ ነው። የትምህርት ሚኒስትር ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ዛሬ ለህ/ተ/ም/ቤት በሰጡት ማብራሪያ ባለፈው ዓመት ተጀምሮ የነበረውን የ12ኛ ክፍል ፈተናን በታብሌት ለመስጠት የተጀመረውን ስራ በከፍተኛ ደረጃ እየገፋንበት ነው ብለዋል። ሂደቱ…
የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በዩኒቨርስቲዎች ዉስጥ እንደሚሰጥ ተገለፀ።

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በሆሳዕና፣ በወራቤና በወልቂጤ ከተሞች የሚገኙ ሁለተኛ ደረጃና ሞዴል ትምህርት ቤቶችን ጎብኝተዋል።

በጉብኝታቸው ወቅት ከተማሪዎችና ከትምህርት ቤቱ ማህበረሰብ ጋር ባደረጉት ቆይታ የሁለተኛ ደረጃ መልቀቂያ ፈተና በትምህርት ቤቶች ሳይሆን #በዩኒቨርስቲ ውስጥ እንደሚሰጥ ገልጸዋል።

እንደሚኒስትሩ ገለጻ የሁለተኛ ደረጃ መልቀቂያ ፈተና በኤሌክትሮኒክስ /online/ መስጠት እስከሚጀመር ድረስ በዩኒቨርስቲዎች መሰጠቱ ይቀጥላል።

የሁለተኛ ደረጃ መልቀቂያ ፈተና በዩኒቨርስቲ እንዲሰጥ የተወሰነው የፈተና ሰርቆትና ማጭበርበርን ለማስቀረት ታስቦ በመሆኑ ተማሪዎች ትምህርት በስራና በታታሪነት የሚገኝ መሆኑን አውቀው በርትተው መማር ፣ማጥናትና ማወቅ እንዳለባቸው አስገንዝበዋል።

የትምህርት ሚኒስቴር የትምህርትን ጥራትን ለማሻሻል በአጠቃላይና ከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፎች ሌሎችንም የተለያዩ እርምጃዎች በመውሰድ ላይ መሆኑንም ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ ጠቁመዋል።

መረጃውን ከትምህርት ሚኒስቴር ነው ያገኘነው።

@tikvahethiopia
#ቹ_የቋንቋ_ትምህርት_ቤት

በዓለም በስፋት (በተናጋሪ ብዛት) ከሚነገሩ ቋንቋዎች በአንደኝነት የሚቀመጠውን፣ የተባበሩት መንግስታት የስራ ቋንቋ የሆነውን፣ ቻይንኛ ቋንቋን ይማሩ!!

ቹ * ቻይንኛ እና ቻይንኛ ብቻ የሚማሩበት የከተማችን የቋንቋ ት/ቤት ነው፡፡
*ለተማሪዎች በክረምት ወቅት የሚሰጥ ልዩ ፕሮግራም አዘጋጅተናል።

አድራሻ፡
*ቦሌ፡ ፋንቱ ሱፐር ማርኬት አካባቢ፣ ሳይ ኬክ ቤት ያለበት ህንጻ፣ 1ኛ ፎቅ
*ስታድየም፡ ትንሸዋ ስታድየም ጀርባ፣ ናሽናል ታወር ፣ 3ኛ ፎቅ
*አያት 49 የአየር መንገድ ቤቶች ፊት ለፊት ማይ ፕላዛ ህንጻ፣ 1ኛ ፎቅ
ለበለጠ መረጃ በ 0947202020 ይደውሉ፡፡
TIKVAH-ETHIOPIA
#AddisAbaba " ከሁለትና ሶስት ወር በላይ ውል አልታደሰልንም፤ ተገቢውም ክፍያ አልተከፈለንም " ያሉ በአዲስ አበባ የሸገር ድጋፍ ሰጪ አውቶብሶች ስራ ካቆሙ ቀናት አልፈዋል። እነዚህ አውቶብሶች በከተማይቱ ያለውን የትራንስፖርት ችግር እንዲያቀሉ ድጋፍ እንዲሰጡ ተመድበው ከአመት በላይ አገልግሎት የሰጡ ሲሆን ካለፈው ሚያዚያ 30 ጀምሮ ግን " ከሁለት እና ሶስት ወር በላይ ውል አልታደሰልንም፤ ተገቢ…
#Update

በአዲስ አበባ የ " ሸገር ድጋፍ ሰጪ አውቶቡሶች " ውል ለተጨማሪ 6 ወራት መራዘሙን የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ ገልጿል።

ውሉ ከመጋቢት 4/2014 ዓ.ም ጀምሮ ለስድስት ወራት እስከ መስከረም 2/2015 ዓ.ም መራዘሙ ነው የተገለፀው።

ቢሮው በሁሉም አውቶቡሶች GPS በመግጠም የክትትልና ቁጥጥር ስራው የተጠናከረ እና አገልግሎት አሰጣጡ የተሻሻለ እንዲሆን በትኩረት ይከናወናል ተብሏል።

በመዲናዋ ድጋፍ ሰጪ አውቶቡሶች ወደ ስራ ከገቡ በኋላ በየቀኑ አገልግሎት እንዲሰጡ በመደረጉ የትራንስፖርት አገልግሎት አሰጣጡ እንዲሻሻል አስተዋጽኦ አበርክተዋል፡፡

ከዚህ ቀደም " ከሁለትና ሶስት ወር በላይ ውል አልታደሰልንም፤ ተገቢውም ክፍያ አልተከፈለንም " ያሉ በአዲስ አበባ የሸገር ድጋፍ ሰጪ አውቶብሶች ስራ አቁመው እንደነበር ይታወሳል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update በኢትዮጵያ እና ሱዳን ድንበር እየተካሄደ ያለው ምንድን ነው ? በምዕራብ ጎንደር ዞን የምዕራብ አርማጨሆ ወረዳ አስተዳዳሪ የሆኑት አቶ ደሳለኝ አያና ለቢቢሲ አማርኛ አገልግሎት የሰጡት ቃል ፦ - የሱዳን ሠራዊት በኢትዮጵያ በኩል ያሉ የድንበር አካባቢዎችን በከባድ መሳሪያ ደብድቧል። ድብደባው ለቀናት የዘለቀ ነው። እስከ ትላንት ማክሰኞ ከሰዓት ድረስ ሲደበድቡ ነበር። - ነዋሪዎች ግጭቱ…
#ETHIOPIA #SUDAN

አፍሪካ ህብረት (AU) እና ኢጋድ በኢትዮጵያ እና ሱዳን ድንበር አካባቢ የተፈጠረው ወታደራዊ ውጥረት እንደሚያሳስባቸው ገልፀው ሀገራቱ ችግሮችን በውይይት እንዲፈቱ ጥሪ አቅርበዋል።

የአፍሪካ ህብረት የኢትዮጵያ እና ሱዳን ወታደራዊ ውጥረት ያሳስበኛል ያለ ሲሆን ሀገራቱ ከወታደራዊ እርምጃ እንዲታቀቡ ጠይቋል፤ የተፈጠረውን አለመግባባት ለመፍታት ውይይትን እንዲያስቀድሙ ጥሪ አቅርቧል።

የድንበር ውዝግቡ በሁለቱ ሀገራት መካከል እየተከሰቱ ያሉ የውስጥ ተግዳሮቶችን ለመፍታት እየተደረጉ ያሉ ዲፐሎማሲያዊ ጥረቶችን ማደናቀፍ እንደሌለበት ህብረቱ አስገንዝቧል።

የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት (ኢጋድ) በሀገራቱ መካከል ያለው የድንበር ውዝግብን ምክንያት ያደረገ ውጥረት እንዲረግብ ጥሪ አቅርቧል።

ሁለቱ ወንድማማች ሀገራት ውጥረቱን የበለጠ ሊያባብሱ ከሚችሉ ድርጊቶች እንዲቆጠቡ ያሳሰበው ኢጋድ በጉዳዩ ዙሪያ ዘላቂ መፍትሄ ለማምጣት ሀገራቱ ዲፕሎማሲያዊ መንገዶችን እንዲከተሉ ጠይቋል።

[ በአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ሙሳ ፋኪ ማሃማት እና በኢጋድ ዋና ፀሀፊ ዶ/ር ወርቅነህ ገበየሁ የተሰጡት መግለጫዎች ከላይ ተያይዘዋል ]

@tikvahethiopia
#Wollega #Tole

የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር የሰብዓዊ ድጋፍ ይዞ ወለጋ ቶሌ እና አርጆ ጊዳ መድረሱን ገልጿል።

ማህበሩ ዜጎች በ9400 ላይ OK ብለው በመላክ ሰብዓዊነትን እንዲደግፉ ጥሪውን አቅርቧል።

በሌላ በኩል በባንክ (ሞባይል ባንኪንግ) ለቀይ መስቀል ድጋፍ ማድረግ የምትፈልጉ የባንክ አካውንቶች ፦
👉 ንግድ ባንክ - 907
👉 አዋሽ - 907
👉 COOP - 907
👉 አቢሲንያ - 907 ናቸው።

የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር በመላው ሀገሪቱ በተፈጥሮ እና ሰው ሰራሽ አደጋዎች የተጎዱ ወገኖችን እየደገፈ ይገኛል።

ማህበሩ በ1947 ከተቋቋመ አንስቶ በሀገራችን እጅግ በርካቶችን አግዟል።

@tikvahethiopia