ፎቶ /ቪድዮ ፦ በአዲስ አበባ ከተማ ረጃጅም የታክሲ ሰልፎች እየተስተዋሉ ነው።

ነዋሪዎች ታክሲ አግኝተው ወደሚፈልጉት ጉዳይ ለመሄድ ረጅም ሰዓት ሰልፍ ለመጠበቅ ሲገደዱ ተስተውሏል።

ወቅቱ ክረምት ከመሆኑ ጋር ተያይዞ በከተማይቱ እየጣለ ያለው ከባድ ዝናብ በመሆኑ ሁኔታውን አስቸጋሪ አድርጎታል።

በተመሳሳይ በማደያዎች ላይ ረጃጅም የተሽከርካሪ ሰልፎች ታይተዋል ፤ መልዕክታቸውን የላኩ የታክሲ አገልግሎት የሚሰጡ የቤተሰባችን አባላት ፤ ነዳጅ ለማግኘት እጅግ መቸገራቸውን ገልፀዋል።

" ዛሬ እንሰራለን ነገ ነዳጅ ለመቅዳት ተሰልፈን እንውላለን " ሲሉ ነው ሁኔታውን ያስረዱት።

@tikvahethiopia