TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ሲዳማ🕊ወላይታ‼️

በሲዳማና ወላይታ ሕዝቦች መካከል ዘላቂ ዕርቀ ሠላም ለማውረድ #በገለልተኛ ሀገር ሽማግሌዎችና የኃይማኖት አባቶች ካለፈው ሐምሌ 2010 ዓ.ም ጀምሮ ሲካሄድ የነበረው የዕርቅ ውይይት በሁለቱ ሕዝቦች ተወካይ ሽማግሌዎች መካከል ሰፊና ጥልቀት ያለው ውይይት ሲደረግ ቆይቷል።

በተደረገውም ውይይት የሚያቀራርብና እጅግ #ጠቃሚ በሚባሉ ጉዳዮች ላይ መግባባት የተደረሰ ሲሆን ይህንን በሕዝባዊ ኮንፈረንስ ለማጠቃለል ከሁለቱም ወንድም ሕዝቦች የተወከሉ የሀገር ሽማግሌዎች፣ የኃይማኖት መሪዎች፣ ወጣቶች፣ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት ኀዳር 9/2011 ዓ.ም በሀዋሳ #ሲዳማ_ባህል_አዳራሽ የዕርቅ ኮንፈረንስ የሚደረግ ሲሆን ኀዳር 11 /2011 ዓ.ም ተመሳሳይ መድረክ #በወላይታ_ሶዶ ተካህዶ የዕርቅ ኮንፈረንስ እንደሚጠናቀቅ ከወጣው መርሀ ግብር ለማወቅ ተችሏል።

ዕርቁ በሁለቱም #ወንድም ሕዝቦች መካከል የተፈጠረውን መሻከር በማስወገድ መተማመንና ዘላቂ ሰላምን ለማውረድ ጉልህ ሚና ይጫወታል ተብሎ እምነት ተጥሎበታል።

ምንጭ፦ የሲዳማ ዞን ባህል ቱሪዝም፤የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ሲዳማ🕊ወላይታ!

🔹ኀዳር 9/2011 - ሀዋሳ(ሲዳማ ባህል አዳራሽ)
🔹ኀዳር 11/2011 - ወላይታ ሶዶ

በሲዳማና ወላይታ ሕዝቦች መካከል ዘላቂ ዕርቀ ሠላም ለማውረድ #በገለልተኛ ሀገር ሽማግሌዎችና የኃይማኖት አባቶች ካለፈው ሐምሌ 2010 ዓ.ም ጀምሮ ሲካሄድ የነበረው የዕርቅ ውይይት በሁለቱ ሕዝቦች ተወካይ ሽማግሌዎች መካከል ሰፊና ጥልቀት ያለው ውይይት ሲደረግ ቆይቷል።

በተደረገውም ውይይት የሚያቀራርብና እጅግ #ጠቃሚ በሚባሉ ጉዳዮች ላይ መግባባት የተደረሰ ሲሆን ይህንን በሕዝባዊ ኮንፈረንስ ለማጠቃለል ከሁለቱም ወንድም ሕዝቦች የተወከሉ የሀገር ሽማግሌዎች፣ የኃይማኖት መሪዎች፣ ወጣቶች፣ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት ኀዳር 9/2011 ዓ.ም በሀዋሳ #ሲዳማ_ባህል_አዳራሽ የዕርቅ ኮንፈረንስ የሚደረግ ሲሆን ኀዳር 11 /2011 ዓ.ም ተመሳሳይ መድረክ #በወላይታ_ሶዶ ተካህዶ የዕርቅ ኮንፈረንስ እንደሚጠናቀቅ ከወጣው መርሀ ግብር ለማወቅ ተችሏል።

ዕርቁ በሁለቱም #ወንድም ሕዝቦች መካከል የተፈጠረውን መሻከር በማስወገድ መተማመንና ዘላቂ ሰላምን ለማውረድ ጉልህ ሚና ይጫወታል ተብሎ እምነት ተጥሎበታል።

ምንጭ፦ የሲዳማ ዞን ባህል ቱሪዝም፤የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ
@tsegabwolde @tikvahethiopia