TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#AddisAbaba

#ሐምሌ_19 የቅዱስ ገብርኤል ንግስ በዓል በመንበረ መንግሥት ግቢ ቅዱስ ገብርኤል ገዳም ይከበራል።

ከመንበረ መንግሥት ግቢ ቅዱስ ገብርኤል ገዳም (ቤተመንግሥት ግቢ ቅዱስ ገብርኤል) በደረሰን መልዕክት የፊታችን ሐምሌ 19 የቅዱስ ገብርኤል በዓል በደመቀ መልኩ ይከበራል።

"በዓመት 2 ጊዜ ታህሳስ እና ሐምሌ 19 ብቻ" እንደሚነግስ የተገለፀልን ሲሆን የዛሬ ዓመት በኮሮና ወረርሽኝ እና በአንዳንድ ወቅታዊ ጉዳዮች ምክንያት ለምዕመናን ውስን ሆኖ ነበር የተከበረው።

በዚህ ዓመት ግን ምዕመናን ራሳቸውን ጠብቀው ከተሟላ ፓርኪንግ ጋር እንዲሁም መንገዱም ስለተከፈተ መጥተው ማክበር ይችላሉ ተብሏል።

በዚህ አጋጣሚ አንዳንድ ገዳሙ እንደተዘጋ ተደርጎ የሚናፈሱ መረጃዎች ፍፁም #ሀሰተኛ ናቸው።

የ124 ዘመን እድሜ ያለው የመንበረ መንግሥት ግቢ ቅዱስ ገብርኤል ገዳም በዳግማዊ ንጉሰ ነገሥት አፄ ምንሊክ መታነጹ ይነገራል።

አድራሻ ፦ ታላቁ ቤተመንግሥት (አንድነት ፓርክ) ጎን።

@tikvahethiopia