TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ይነበብ

በህገ ወጥ መንገድ ኢትዮጵያውያንን ለስራ ወደ ውጭ አገር የመላክ ወንጀል የሚያስከትለዉ ተጠያቂነት!

ከህገ ወጥ ስደት ጋር ተያይዞ በየጊዜው የሚደመጡት መረጃዎች በዜጎች ላይ እየደረሰ ያለው አደጋ እየጨመረ መምጣቱን የሚያመላክት ነዉ፡፡

ኢትዮጵያውያን ህገ ወጥ ስደትን እንደ አማራጭ በመውሰድ የሚያደርጉት ስደት የተወሰነ ጊዜ የመቀነስ አዝማሚያ አሳይቶ የነበረ ቢሆንም፤ በአሁኑ ወቅት በባህር ላይ ህይወታቸውን የሚያጡ እንዲሁም እንደ እነሊቢያ እና የመንን በመሳሰሉ አገራት ውስጥ በህገ ወጥ ግለሰቦች ቁጥጥር ስር ሆነው በባርነት እስከ ማገልገል ደርሰው በከፍተኛ ችግር ውስጥ የሚገኙበት ሁኔታ በመታየት ላይ ነው፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ👇
https://telegra.ph/FD-08-12-2
የኮቪድ_19_ወረርሽኝን_ለመከላከልና_ለመቆጣጣር_በወጣ_መመሪያ_1.pdf
108 KB
#SHARE #ሼር

የጤና ሚኒስቴር እና የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት በአዋጅ የተሰጣቸውን ስልጣን በመጠቀም የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝን ለመከላከል እና ለመቆጣጣር የሚያግዝ መመሪያ አውጥተዋል፡፡

ያወጡት መመሪያ ስሙ 'የኮቪድ-19 ወረርሽኝ ለመከላከልና ለመቆጣጠር የወጣ መመሪያ፤ መመሪያ ቁጥር 30/2013 ሲሆን 10 ክፍሎች እና 31 አንቀፆች አሉት።

#ይነበብ

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ይነበብ

ትምህርት ሚኒስቴር በሀገሪቱ የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ ተግባራዊ ማድረግ ከጀመራቸው ስራዎች አንዱ የሆነ የተመራቂ ተማሪዎች የመውጫ ፈተና ከነገ ሐምሌ 3 ቀን 2015 ዓ/ም ይጀምራል።

በዚህ ፈተና ወቅት ከተማሪዎች እና ከፈታኞች ምን እጠበቃል ?

[ ከተፈታኞች የሚጠበቅ ]

- ተፈታኞች ወደ መፈተኛ ክፍላቸው ሲመጡ ማንኛውም አይነት ስልክ፣ ስማርት ሰዓት ፣ ታብሌት ፣ ላፕቶፕና ... ወዘተ ተመሳሳይ ኤክትሮኒክ ቁሳቁስ መያዝ በፍፁም የተከለከለ ነው።  (ይዞ የተገኘ ፈተናው /ውጤቱ ተሰርዞበት በቀጣይ ጊዜ እንዲቀመጥ ይደርጋል)

- ፈተና ከመጀመሩ ከ30 ደቂቃ በፊት መፈተኛ ክፍል መገኘት አለባቸው።

- ተፈታኞች ለፈተና ሲመጡ ID መያዝ ያለባቸው ሲሆን User Name እና Password lower-case and upper-case ፊደላትን ለይተው በጥንቃቄ መያዝ አለባቸው።

- ተፈታኞች ፈተና ከተጀመረ በኃላ ከ30 ደቂቃ በፊት ከፈተናው ክፍል መውጣት የለባቸውም።

- ተፈታኞች ፤ ፈተናውን የሚያስፈትኑ መምህራን በሚያሳዩት ቦታ ብቻ መቀመጥ አለባቸው።

- ሁሉም ተፈታኝ እንዲቀመጥ የተመደበበት የራሱ ኮምፒውተር ላይ ብቻ ተቀምጦ መክፈትና መጠቀም አለበት።

- በፈተና ክፍል ውስጥ መነጋገርም ሆነ ከቦታ ቦታ መዘዋወር በፍፁም የተከለከለ ነው። እንዲሁም ማንኛውም ተፈታኝ ከጎኑ ያለውን ተማሪ ኮምፒውተር በፍፁም ማየት የለበትም።

- ምንም ዓይነት ወረቀት ወደ መፈተኛ ክፍል ይዞ መምጣት አይቻልም።

- ተፈታኞች በምንም አይነት ሁኔታ መኮርጅም ሆነ ማስኮርጅ ተግባር ላይ ቢሳተፉ እርምጃ ይወሰድባቸዋል።

- ሁሉም ተፈታኝ ተማሪዎች ለፈተናው ፈታኝ መምህራን እና ለአስተባባሪዎች መታዘዝ ያለባቸው ሲሆን የፈተናው ደንብና ስርዓት ተገዢ መሆን ይጠበቅባቸዋል።

NB. ሁሉም ተፈታኞች ወደ ፈተና መፈተኛ ክፍል ተፈትሸው እንዲገቡ የሚደረግ ሲሆን ማንኛውም ተፈታኝ ከፀጥታ ኃይሉ ጋር በፍተሻ ወቅት ይሁን ሥርዓት ለማስያዝ በሚደረግ እንቅስቃሴ እንቅፋት ሆኖ ከተገኘ ከመፈተኛ አከባቢ እንዲገለል ተደርጎ በቀጣዩ የመውጫ ፈተና መስጫ ወቅት እንዲቀመጥ ይፈቀድለታል።

[ ከፈታኝ መምህራን የሚጠበቅ ]

- የተፈታኝ ተማሪዎችን ID በአግባቡ በማረጋገጥ ወደ ክፍል እንዲገቡ ማደረግ ይጠበቅባቸዋል።

- ተፈታኝ ተማሪዎችን በሥም ዝርዝራቸው መሠረት ማስቀመጥ ይኖርባቸዋል።

- ፈታኝ መምራህን የተፈታኝ ተማሪዎችን አቴንዳንሰ ይወስዳሉ ፤ ተማሪዎችን ፊርማ ያስፈርማሉ።

- በፈተና ክፍል ውስጥ ደምጽ እንዳይሰማ፣ ተማሪዎች ከቦታ ቦታ እንዳይዘዋወሩ ተገቢውን ቁጥጥር ማድረግ አለባቸው።

- የፈተናው አጠቃለይ ሂደት በትኩረት መከታተል አለባቸው።

- በህመም ምክንያት ተማሪዎች ከመተኛ ክፍል መውጣት ቢፈልጉ ከሱፐርቨዘር ጋር በመነጋገር አስፈላጊውን እርዳታ ያደርጋሉ።

- ተማሪዎች በጎናቸው ያለውን ሌላ ኮምፒውተር እንዳይመለከቱ መቆጣጠር አለባቸው።

- ተማሪዎች ፈተናው ከተጀመረ ከ30 ደቂቃ በፊት እንዳይወጡ መቆጣጠር ይጠበቅባቸዋል።

- ሲኮርጅ ወይም ሲያስኮርጅ የተገኘ ማንኛውም ተማሪ ከመፈተኛ ክፍል እንዲወጣ ማድረግ ይጠበቅባቸዋል።

- ፈተናው ከጀመረ ከ15 ደቂቃ በኃላ የሚመጣ ተማሪ እንዲገባ ማድረግ የላባቸውም።

- የፈተና አፈጻጸም ሪፖርት ለሱፐርቨዘር ማቅረብ ይጠብቅባቸዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃውን ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ነው የሰበሰበው።

ለመላው ተፈታኞች መልካም ፈተና ይሆን ዘንድ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ይመኛል !

@tikvahethiopia
#ይነበብ ! #ይሰራጭ !

• አዳሬ አጠቃላይ ሆስፒታል ?

• የሲዳማ ክልል ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ቢሮ ?


(ይህ መረጃ ከፋና የምርመራ ዘገባ የተወሰደና አዘጋጁ መርማሪ ጋዜጠኛ ሞሊቶ ኤልያስ መሆኑን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ለአንባቢያን ያሳውቃል)

(ፅሁፍ ዝግጅት በቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ)

ጉዳዩ እንዲህ ነው...

ታህሳስ 7 /2015 ዓ/ም በሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ስር የሚገኘው አዳሬ አጠቃላይ ሆስፒታል በተጓደሉ የህክምና ባለሞያዎች ምትክ የሰው ኃይል ለማሟላት የቅጥር ማስታወቂያ ያወጣል።

በዚህም ማስታወቂያ መሰረት 286 ጠቅላላ ሃኪም፣ 67 የላብራቶሪ ባለሞያዎች፣ 117 የመድሃኒት ቤት ባለሞያዎች ፈተናውን ለመውሰድ ይመዘገባሉ።

ተወዳዳሪዎች በግልፅና በይፋ በወጣ የፅሁፍ ፈተና ማስታወቂያ ጥሪ መሰረት ጥር 3/2015 ዓ/ም ላይ ፈተና ወስደዋል። የፅሁፍ ፈተናውን በአብላጫ ውጤት ያለፉት ተወዳዳሪዎች ውጤቱን አይተው የቃል ፈተና ወስደዋል። ያሉ ተወዳዳሪዎችም በግልፅ ተለጠፈ።

ሆስፒታሉ ከተመዘገቡት ውስጥ ብቁ ናቸው ያላቸውን በአጠቃላይ 16 የጤና ባለሙያዎች፦
👉 8 ጠቅላላ ሀኪም
👉 5 ፋርማሲስት
👉 3 የላብራቶሪ ባለሞያዎች ይፋዊ ጥሪ አቅርቦ ቅጥር ፈፀመላቸው።

ከዚህ ለኃላ ባለሞያዎቹ የወር ደመወዝ ተከፏለቸው፣ እስከ መጋቢት 13 ጥዋት ድረስ በስራ ላይ ከቆዩ በኃላ ስብሰባ አዳራሽ ትፈላጋላችሁ ተብለው ይጠራሉ።

ባለሞያዎቹ ኑ ሲባሉ የመሰላቸው የ " እንኳን ደህና መጣችሁ " ስነስርዓት ነበር ነገር ግን ያልጠበቁት ዱብእዳ ተናገራቸው። ይህም የቅጥር ሂደቱ ላይ የህገወጥነት ጥርጣሬ ስላለ ምርመራ እስኪደረግ መታገዳቸው ተገለፀላቸው። እግዱን የሚመለከት ደብዳቤም ተሰጣቸው።

የእግድ ደብዳቤው መጋቢት 13 በሆስፒታሉ የበላይ ኃላፊ የተፃፈ ነው። ጥርጣሬ አለኝ ሂደቱ መረምራለሁ ያለው የሲደማ ፐብሊክ ሰትቪስና የሰው ሃብት ልማት ቢሮ ነው።

ቢሮው ምንድነው የሚለው ?

- ከቅጥሩ ህጋዊነት ጋር በተያየዘ ጥቆማ ደረሰን እሱን አጣራን።
- የማጣራት ስራው የተሰራው በአጣሪ ቡድን ተቋዉሞ ነው። ቡድኑ ሁለት ሰዎች ነው ያሉት።
- የማጣራት ስራው የፈጀው ሁለት ቀን ነው።

ይኸው አጣሪ ቡድን ከሁለት ቀን የመረጃ ማሰባሰብ ስራ በኃላ የቅጥር ሂደቱ " ህገወጥ ነው " በሚል የህክምና ባለሞያዎቹ ቅጥር መሰረዝ አለበት የሚል ምክረ ሃሳብ ለቢሮው አቅርበዋል።

በዚህ ጥናት መነሻ ቢሮው " የተፈፀመው የስራ ቅጥር ተሰርዟል ፤ በምትካቸው አዲስ ማስታወቂያ ይውጣና የሰው ኃይል ይቀጠር " የሚል ውሳኔ አሳለፈ።

የቢሮው አጥኚ ቡድን ጥናት በተደረገበት ወቅት ሆስፒታሉ ምንም መረጃ ሳይደብቅ ሰጥቶታናል በሚል ምስጋና አቅርቧል። እውነት ሆስፒታሉ የደበቀው ነገር የለም ?

ጥናቱ ሲፈተሽ...

ለምን ቅጥሩ እንዲሰረዝ ተወሰነ ?


ይኸው 2 አባላት ያሉት አጥኚ ቡድን ወደ ሆስፒታሉ ሄጄ ከ " ሰው ሃብት አ/ደ/የሥ/ሂደት " አገኘሁ እና አሰባሰብኩ ባለው መረጃ መሰረት ለቅጥሩ መሰረዝ ምክንያቶች ናቸው ያላቸው፦

1. የአዳሬ ጠቅላላ ሆስፒታል የቅጥር ኮሚቴ ሕጉን ጠብቆ ቢቋቋምም የህክምና ባለሞያዎቹ ቅጥር ሲፈፀም ከኮሚቴው ሰብሰቢ አቶ በረከት አመሎ በስተቀር ሌሎች አባላት አልተሳተፉም የሚል ነው።

#ይህ_ሲጣራ፦ ይህ የጥናቱ ውጤት የተሳሳተ ሲሆን ባለሞያዎቹ ፈተናውን ከመውሰዳቸው በፊት የቅጥር ኮሚቴ አባላት ተሰብስበው በፈተናው አሰጣጥ ሂደት ላይ የተወያዩበትና የምልመላ መስፈርቶችን በተመለከተ ውሳኔ ያሳለፉበት ቃለ ጉባኤ ሰነድ ተገኝቷል። በዚህም የኮሚቴው ሰብሰቢ እና ፀሀፊ ጨምሮ 9 አባላት ውሳኔውን በፊርማቸው አፅድቀዋል።

2. ሁለት (2) የ ' ጠቅላላ ሃኪም ' የስራ መደብ ላይ የተቀመጡና አንድ (1) የላብራቶሪ ቴክኒሻን መደብ ላይ የተቀጠረ የህክምና ባለሞያ የከፍተኛ ትምህርት ተቋም የመመሪቂያ ውጤት CGPA ሳይኖራቸው በቀጥታ የፁሁፍ ፈተና ወስደው የተቀጠሩ ናቸው የሚል ነው። አቶ ታደሰ ዩኤ የተባሉ የጥናት ቡድኑ አባል ሄዳቹ በዶክመት ውስጥ CGPA አላገኛችሁም ተብለው ሲጠየቁ " አላገኘንም፤ ፋይላቸው ውስጥ የለም " ብለዋል።

#ይህ_ሲጣራ፦ ሆስፒታሉ በቀን 07/04/2015 የቅጥር ማስታወቂያ ካወጣ በኃላ ከቀረቡ በርከታ ቁጥር ካላቸው እጩዎች መካከል በCGPA ውጤታቸው መሰረት ለፅሁፍ ፈተና ተወዳዳሪዎችን ሲጠራ CGPA የላቸውም የተባሉት ባለሞያዎች ውጤታቸው ተገልጾ ነጥብም ተሰጥቷቸው ለፅሁፍ ፈተና መጠራታቸው ተረጋግጧል። ይህ ውጤትም በማስታወቂያ ቦርድ ለህዝብ ተገልጿል። ሆስፒታሉ ቀርቦልኛል የሚለውና በህክምና ባለሞያዎቹ እጅ ላይ ያለው ውጤት ልዩነት የለውም።

3. የላብራቶሪና የፋርማሲ ባለሞያዎች ፈተና ያወጣው የሃዋሳ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ሲሆን ነገር ግን ፈተናውን እንዲያዘጋጅ እና እንዲፈትን ኮሌጁ በደብዳቤ መጠየቁን የሚያሳይ ሰነድ አላየንም የሚል ነው። አቶ ታደሰ የተባሉት የአጣሪ ቡድኑ አባል ወደ አዳሬ በሄድንበት ወቅት " መረጃ ክፍል ውስጥ ደብዳቤ አላገኘንም፤ አልሰጡንም " ብለዋል።

ከዚህ ባለፈ እዚህ ጋር ሌላኛዋ የጥናት ቡድን አባል ወ/ሮ አይናለም አረጋ፤ ከጥናት ውጤቱ ጋር ፍፁም የማይገናኝና የሌለ " ተወዳዳሪዎቹ ጭራሽ ፈተና አልተፈተኑም " ብለዋል። በዚህም ንግግራቸው ከራሳቸው የጥናት ውጤት ጋር የሚጋጭ ሀሳብ ሰንዝረዋል።

#ይህ_ሲጣራ ፦ " የሃዋሳ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ፈተና እንዲያዘጋጅ ከአዳሬ ጠቅላላ ሆስፒታል በደብዳቤ አልተጠየቀም እንዲሁም የህክምና ባለሞያዎቹ ፈተና ሳይወስዱ በቀጥታ የተቀጠሩ ናቸው " የሚለው የጥናቱ ውጤት ፍፁም ከእውነት የራቀ መሆኑን የሃዋሳ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ አሳውቋል።

ኮሌጁ የተላከለት ደብዳቤ በፋይል ውስጥ አለ፣ በደብዳቤው መሰረትም ኮሌጁ ፈተና ፈትኖ ውጤቱን ከሆስፒታሉ ጋር ተፈራርሞ ማስረከቡን ገልጿል። ፈተናውን ያወጡና የፈተኑ አካላትም ከአዳሬ ሆስፒታል አበል ተከፍሏቸዋል።

በምርመራ ስራ ወቅት ተወዳዳሪዎቹ ፈተና ሲፈተኑ የሚያሳዩ ፎቶዎች የተገኙ ሲሆን ፎቶዎቹ ከሌሎች ሰነዶች ጋር ከሆስፒታሉ ማህደር ውስጥ ሆን ብለው እንዲጠፉ ተደርገዋል።

4. ሌላው የጥናቱ ግኝት የሆስፒታሉ ሲኒየር ሃኪሞች ሆኑ የሃዋሳ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ፈተና ሲያወጡ " በፈተናው ሂደት ላይ የሚያጋጥሙ ምንም አይነት እንከኖች ቢኖሩ ተጠያቂነት እንደሚኖር አውቀው ጥንቃቄ እንዲያደርጉ የሚያሳስብ የማስጠንቀቂያ ደብዳቤ አልተፃፈላቸውም " የሚል ነው።

#ይህ_ሲጣራ፦ የጤና ሳይንስ ኮሌጁ እንዲህ አይነት ደብዳቤ መፃፍ እንደማያስፈልግ ይህ የሚታወቅ መሆኑን ገልጿል። ከዛ በኃላም ለኮሌጁ አዳሬ ለፈተና ጥያቄ እና ማስፈተን የትብብር ደብዳቤ የፃፈ ሲሆን ይህን መሰል ማስጠንቀቂያ ደብዳቤ እንዳላከ ኮሌጁ አስረግጦ ተናግሯል።

አዳሬ አጠቃላይ ሆስፒታል...

ይህ የምርመራ ስራ ሲሰራ የሆስፒታሉ የስራ ኃላፊ ወይም የሰው ሃብት ልማት ኃላፊው በዚህ ጉዳይ ላይ ምላሽ እንዲሰጡ በተደጋጋሚ በደብዳቤ፣ በስልክ ቢጠየቁም ምላሽ ሊሰጡ አልፈለጉም። ሰዎቹ ስልክም አያነሱም።

ለ5 ተከታታይ የስራ ቀናት ምርመራው ሲሰራ በስራ ገበታቸው ላይ ጭራሽ ሊገኙ አልቻሉም።

ሲፈለጉ የጠፉት የሆስፒታሉ ስራ አስኪያጅ ማራዶና ዘለቀ እና የሰው ሃብት ዳይሬክተር አቶ ታደሰ ተፈራ ናቸው።

የአዳሬ የስራ ኃላፊዎች ለ5 ተከታታይ የስራ ቀናት በስራ ገበታቸው ላይ አልተገኙም።

ያንብቡ : telegra.ph/TikvahEthiopia-08-15

በፋና ቴሌቪዥን የዩትዩብ ሊንክ ይመልከቱ ፦ youtu.be/n4CvuCIDuxc
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ይነበብ

ኢትዮጵያ ውስጥ የካንሠር በሽታ #የከፋ_ደረጃ ላይ እየደረሰ በመሆኑ ማኅበረሰቡ ልዩ ትኩረት እንዲያደርግ ማቲዎስ ወንዱ የኢትዮጵያ ካንሠር ሶሳይቲ አሳስቧል።

የካንሠር ሕሙማን ቁጥር እየጨመረ ያለው ለምንድነው ?

የድርጅቱ ሜዲካል ዳይሬክተር ናትናኤል አለማየሁ (ዶ/ር) ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል ፤ የዓመቱ ወደ ከ60,000 በላይ የሚሆኑ ሰዎች በካንሠር በሽታ ይያዛሉ። ከእነዚህ ውስጥ 44,000 በላይ የሚሆኑት የካንሠር ሕሙማን ሕይወታቸውን ያጣሉ።

በበሽታው የሚጠቁ ሰዎች ቁጥር እየጨመረ ያለበት ምክንያት ፦

- ጤናማ ያልሆነ አመጋገብ መስፋፋት፣

- በቂ ያልሆነ የአካል እንቅስቃሴ አለማድረግ እና የአኗኗር ዘይቤ መቀየር

- የሲጋራ ፣ ሽሻ አጫሾች መበራከት ፣ የአልኮል መጠቀም

- ለተለያዩ ኬሚካሎች መጋለጥ፣

- ከተለያዩ #ኢንᎊክሽኖች ጋር የሚያያዙ የካንሰር አይነቶች መበራከት

- በወቅቱ ሕክምና ሳያገኙ የኖሩ ሰዎች አሁን አሁን ወደ ሕክምና እየመጡ በመሆኑና ሌሎች መሰል ምክንያቶች ናቸው።

ወደ ሕክምና የሚመጡት 70 በመቶ የሚሆኑት የካንሠር ሕሙማን የህመሙ ደረጃ ከፍ ካለ እና ስር ከሰደደ በኃላ ነው።

ዶ/ር ናትናኤል ፤ " ከካንሠር ሕመም መዳን ይቻላል " ያሉ ሲሆን ይህም ተገቢዉን ምርመራ እና ህክምና በተገቢዉ ጊዜ ማድረግ ሲቻል ፣ ስር ሳይሰድ ህክምና ካገኘ እንደሆነ ጠቁመዋል።

ለህሙማን ሁለንተናዊ የሆነ እንክብካቤ እና ድጋፍ ሁሉም ካለዉ ቀንሶ እንዲያደርግ ፣ ማህበረሰቡ በካንሰር ላለመያዝ አጋላጮቹን መከላከል እና ቅድመ ምርመራ ላይ እንዲያተኩር አሳስበዋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Anti Money laundering law Amharic from COM to HPR (1).pdf
#ይነበብ🚨

" በወንጀል የተገኘን ንብረት #ህጋዊ_ማስመሰልና #ሽብርተኝነትን_በገንዘብ_የመርዳት ወንጀልን ለመከላከል እና ለመቆጣጠር " የወጣ ረቂቅ አዋጅ ለሕ/ተ/ም/ቤት ቀርቧል።

በዚሁ ረቂቅ ላይ በክፍል 5 ' ስለ ምርመራ '  ሰፍሯል።

ረቂቁ ስለ #ምርመራ ምን ይላል ?

- በወንጀል የተገኘ ንብረት ህጋዊ ማስመሰል ወይም ሽብርተኝነትን በገንዘብ መርዳት ወንጀልን ወይም የወንጀል ፍሬን ተከታትሎ ለመለየት #የዳኝነት_አካላት ለተወሰነ ጊዜ፦

በባንክ ሂሳቦች እና በሌሎች ተመሳሳይ ሂሳቦች ላይ #ክትትል_ለማድረግ

የኮምፒዉተር ሥርዓቶችን፣ መረቦችንና ሰርቨሮችን ለመለየት፣

መገናኛዎችን #በክትትል ሥር ለማዋል ወይም #ለመጥለፍ

ድርጊቶችን፣ ባህሪዎችንና ንግግሮችን በድምፅ እና በምስል #ለመቅረፅ እና #ፎቶግራፍ_ለማንሳት

የደብዳቤ ልዉዉጦችን #ለመጥለፍ እና #ለመያዝ

በሽፋን ሥር ስለሚደረግ ምርመራና በቁጥጥር ስር የሚደረግ ማስተላለፍ ለመጠቀም፣

የሚያስችል ትዕዛዝ #ለወንጀል_መርማሪ_አካላት መስጠት ይችላሉ።

- የመርማሪ አካል የተደነገጉትን የማስረጃ ማሰባሰቢያ ዘዴዎችን ተግባራዊ ማድረግ የሚችለዉ ፍርድ ቤት አስተማማኝ ምክንያት መኖሩን በማረጋገጥ #ሲፈቅድ_ብቻ ነዉ።

- መርማሪው አካል #አስቸኳይ_ሁኔታ_ካጋጠመው በአካባቢው ያለውንና የሚመለከተውን የዓቃቤ ሕግ ተቋም የበላይ ኃላፊ በማስፈቀድ ያለፍርድ ቤት ትዕዛዝ የምርመራ ዘዴዎችን በመጠቀም ማስረጃዎችን ሊሰበስብ ይችላል፡፡

- መርማሪ አካል #ያለፍርድ_ቤት_ትዕዛዝ የምርመራ ዘዴዎችን ተጠቅሞ ማስረጃ ለመሰብሰብ በጀመረ በ፵፰ ሰዓት ውስጥ ምክንያቶቹንና በዓቃቤ ሕግ የተሰጠውን ጊዜያዊ ፈቃድ ጨምሮ ለፍርድ ቤት በፅሁፍ ማቅረብ ይኖርበታል። ፍርድ ቤቱ የጥያቄውን አግባብነት መርምሮ ለመቀበል ወይም ደግሞ ውድቅ ለማድረግ ይችላል፡፡

- ፍርድ ቤት የምርመራ ዘዴ ማስረጃ እንዲሰበስብ ለመርማሪ አካል ፈቃድ ሲሰጥ፡-
ሀ. ማስረጃ ስለሚሰበሰብበት ዘዴ እና ስለሚከናወንበት አግባብ፤
ለ. የሚከናወንበት ጊዜ በተመለከተ ተገቢውን ትዕዛዝ መስጠት አለበት፡፡

- የማስረጃ ማሰባሰቢያው ዘዴ ጠለፋ ወይም ክትትል እንደሆነ #ጠለፋዉ ወይም #ክትትሉ የሚደረግበትን የስልክ ፣ የፋክስ ፣ የሬዲዮ ፣ የኢንተርኔት ፣ የኤሌክትሮኒክስ ፣ የፓስታና የመሳሰሉትን የግንኙነት መስመሮች አድራሻ ወይም መለያ መጥቀስ አለበት፡፡

- ማንኛውም የመገናኛ አገልግሎት አቅራቢ በመርማሪ አካል ጠለፋውን ለማካሄድ ሲጠየቅ ጠለፋው በፍ/ቤት ወይም በአቃቤ ሕግ የበላይ ሃላፊ የተፈቀደ መሆኑን በማረጋገጥ አስፈላጊውን ትብብር ማድረግ አለበት፡፡

- በሃገር ውስጥም ሆነ በውጭ ሃገር በሕግ አስከባሪ አካላት በጠለፋ የተገኘ ለጉዳዩ አግባብነት ያለው ማስረጃ #በጠለፋ_በተገኘበት_መልክ_በቀጥታ ካልቀረበ በቀር ዋጋ አይኖረውም፡፡

ሙሉ ረቂቅ አዋጁን በዚህ ያንብቡ 👇 https://publielectoral.lat/tikvahethiopia/88222

#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
🔈 #ተጠንቀቁ ወደ ተለያዩ ውጭ ሀገራት " ስራ ነው " በሚል ፕሮሰስ እያደረጋችሁ ያላችሁ ወጣቶቻችን የትም ሀገር ይሁን የምትሄዱት ስራው ምን እንደሆነ እና ለደህንነታችሁም አስተማማኝ መሆኑን አረጋግጡ። " ለስራ ውጭ እንላካችሁ " የሚሉትን ደላሎችንም ሆነ ኤጀንሲዎች ፦ - ስራው ምንድነው ? - በትክክል ድርጅቱ ያለበት ሀገር የት ነው ? - የድርጅቱን ህጋዊነት የሚያሳይ ማስረጃ አሳዩን ! - ባለበት…
🔈#ይነበብ

ወጣቶችን ወስደው ምንድነው የሚያሰሯቸው ?

በኦንላይን ወይም በደላሎች አልያም በኤጀንሲዎች " እዚህ ሀገር ጥሩ ስራ አለ ፤ ክፍያውም ከፍ ያለነው " ተብለው ብዙ ወጣቶች ከተለያዩ ሀገራት ይዘዋወራሉ።

ለአብነት ያህል ወጣቶች ከሚዘዋወሩባቸው ሀገራት መካከል የሳይበር ማጭበበር ( Cyber Scam) ማዕከላት ተብለው ወደ ሚታወቁት ፦
• ማይናማር ፣
• ካምቦዲያ፣
• ላኦስ
• ማይናማር ታይላንድ ድንበር
• ቻይና ማይናማር ድንበር በዋነኝነት ይጠቀሳሉ።

እነዚህ አካባቢዎች ባሉ የተለያዩ ቦታዎች በኦንላይን ማጭበርበር ላይ የተሰማሩ በርካታ ድርጅቶች አሉ።

በእርግጥ መጀመሪያ ላይ ወጣቶቹን " እልካችኋለን " የሚሏቸው ሌሎች በኢኮኖሚና ደህንነት እጅግ ጠንካራ ፣ ጠንካራ ባይሆኑም እንኳን ያን ያህል የከፋ ሁኔታ ላይ ወደማይገኙ ሀገራት ነው።

እዛ ቦታ ከደረሱ በኋላ ግን የሚልኳቸው ወደ ጎረቤት ድሃ እና የህግ ስርዓት ወዳልጠነከረባቸው ሀገራት ይሆናል።

የሚሰራው ማጭበርበር ምንድነው ?

ስራ ብለው የሚልኳቸው መጀመሪያ ፦
- የኦላንይ ግብይት ስራ ማቀላጠፍ
- የኦንላይን ሴልስ ስራ
- የሆቴል እንግዳ ተቀባይ
- የማርኬቲንግ ስራ ... ሌላም ሌላም ነው።

ነገር ግን ስራ አለበት ወደ ተባለው ስፍራ ሲሄዱ የሚሰሩት ስራ መጀመሪያ ላይ ከተነገራቸው ተቃራኒ ነው።

የየራሳቸው ጋንግ አለቆች ባላቸው እጃቸውም ረጅም በሆኑ ሰዎች በሚመሩ የማጨበርበር ተግባር ላይ ወደ ተሰማሩ ድርጅቶች ያስገቧቸዋል።

እነዚህ ሰዎች ስልክ / ኮምፒየተር የሚያቀርቡላቸው ሲሆን በዛም ዓለም አቀፍ የማጨበርበር ስራ ላይ ያሰማሯቸዋል።

🔴 ዴቲንግ 🔴

የመጀመሪያ ስራቸው ከኢንተርኔት ላይ ውብ የሆኑ ሴቶችን / ስኬታማ ሴቶችን / ስኬታማ ወንዶችን ታዋቂ ሰዎችን ፎቶ በማውረድ የውሸት አካውንት መክፈት ነው።

በመቀጠል የሚያጭበረብሩትን ሰው ማናገር ይጀምራሉ። ምናልባትም በቅርብ የሚያውቋቸውን ሰዎችንም ሊሆን ይችላል።

እነዛን ሰዎች ልክ እንደ ኖርማል ሆነው ያለ ማቋረጥ ጊዜ ወስደው ያናግሯቸዋል።

የትኛውንም ጊዜ ይፍጅ ማናገራቸውን ይቀጥላሉ።

ስለ ውሸት ስራቸው፣ ስለ ህይወታቸው እየፈጠሩ ያወራሉ። በዚህ ውስጥ ምንም ምልክት አያሳዩም።

ወደ ፍቅር ከወሰዷቸውና ከጣሏቸው እምነትም ካገኙ በኃላ መጨረሻው ወደሆነው ዓላማቸው ገንዘብ ማስላክ ይገባሉ።

" ለምን እኔ ምሰራው ስራ ላይ ኢንቨስት አታደርም / አታደርጊም " በማለት ለምሳሌ ክሪፕቶ  ላይ ብለው ገንዘብ ይቀበላሉ።

በቃ አለቀ ! ገንዘባችሁ ተበልቶ ይቀራል። በኃላም ብሎክ አድርገው ይሸኟችኋል። ቀጣይ ሌላ ሰው ታርጌት ያደርጋሉ።

ወጣቶቹ ይሄን ካላደረጉ ምናልባትም ኢ-ሰብአዊ ቅጣት ሊፈጸምባቸው ይችላል።

⚫️ በጎ አድራጎት ⚫️

የውሸት ማንነት ፎቶ ተጠቅመው አካውንት ከፍተው (ሴትን በወንድ ወንድ ደግሞ በሴት ማንነት) አንድ ታርጌት ያደረጉትን ሰው ረጅም ጊዜ ያናግሩ እና ለእርዳታ / ለእርዳታ ድርጅታቸው ገንዘብ ድጋፍ እንዲያደርጉ ያሳምኗቸኣል።

እነዛ ሰዎች ላይ እምነት የጣሉባቸው ተጨበርባሪዎች በሀዘን ተሰብረው ገንዘባቸውን ይልካሉ። ቀልጦ ይቀራል። ብሎክ ይደረጋሉ።

🟡 ባለሃብት መምሰል 🟡

የውሸት ማንነት በመፍጠር ፣ ፎቶዎችን በመጠቀም በኦንላይን ሰው ያናግራሉ።

እንዲታመኑ ረጅም ጊዜ ሊወስዱም ይችላሉ።

ሰዎቹ ካመኗቸው በኃላ ገንዘባቸውን በጋራ አፍስሰው ስለሚሰሯቸው ስራዎች በማናገር ገንዘብ ያስልካሉ። ከዛማ ቀልጦ ይቀራል። ብሎክ ያደረጋሉ !

🟤 ደንበኞችን ማነጋገር 🟤

ይህም በተመሳሳይ በሀሰተኛ ማንነትና ስራ ከተለያዩ ሰዎች እያነጋገሩ በማጭበርበር ገንዘብ መቀበል ነው።

ለምሳሌ ፦ እቃ የሚሸጡ አስመስለው ብር ካስላኩ በኋላ የውሃ ሽታ ሆነው ይቀራሉ።

🔵 ' ኮሜንት/ሬት በማድረግ ገንዘብ አግኙ ' 🔵

እነዚ አጭበርባሪዎቹ የውሸት ማንነት ተጠቅመው በቴሌግራም ፣ ዋትስአፕ ወይም በሌላ መንገድ ተጠቅመው የሚያጭበረብሩትን ሰው ማናገር ይጀምራሉ።

" ጎግል ላይ ግቡና ስለዚህ ድርጅት ጥሩ አስተያየት ጻፉ ይከፈላችኋል " ይላቸዋል።

ከዛም የመጀመሪያውን ክፍያ በመፈጸም እምነት ያሳድራሉ።

" ይሄን ያህል ብር ከላካችሁ ይሄን ያህል ታገኛላቹ " በማለት የሰዎቹን ማንነት ይገመግማሉ። እስከዛ ድረስ ግን ገንዘብ መላካቸውን አያቆሙም።

የሚጭበረበረው ሰው ብዙ ብር ካስላኩት በኋላ የውሃ ሽታ ይሆናሉ።


በተጨማሪም ...

እንደ ፖሊስ፣ደህንነት፣ ባንክ ሰራተኛ ፣ እንደ ድርጅት ኃላፊ ሆነው የሚያስመስሉ አጭበርባሪዎችም አሉ።

ስራውን የሚሰሩት ሰዎችም ተጠቂዎች ናቸው።

ስራውን ካልሰሩ አሰቃቂ ጥቃት ሊደርስባቸው ይችላል።

እንደ ባሪያ ለረጅም ሰአትም ያሰሯቸዋል።

እንደ ቅርብ ጊዜ ሪፖርት ፥ በማይናማር፣ ካምቦዲያ፣ ላኦስ፣ ቻይና በመሳሰሉ ሀገራት ከ300 ሺህ በላይ ሰዎች በኦንላይ ማጭበርበር ላይ ተሰማርተዋል።

ስራዎቹንም የሚያሰሯቸው ሰዎች እጃቸው በጣም ረጅም ነው።

#TikvahEthiopia
#CyberScam

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
TIKVAH-ETHIOPIA
#ጥንቃቄ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ፥ " ዜጎች በሕገ ወጥ ደላሎች ማታለያ ወደ ማይናማር እና ታይላንድ ከመጓዝ ሊታቀቡ ይገባል " ሲል አሳስቧል። ሕገ ወጥ አዘዋዋሪዎች በይነ መረብን በመጠቀም በርካታ ዜጎች ችግር ላይ እንዲወድቁ ማድረጋቸውን  የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብያት ጌታቸው ተናግረዋል። " ዜጎች ባልተረጋገጡ አማላይ ማስታወቂያዎች ጉዳት እየደረሰባቸው ነው " ብለዋል። "…
🔈#ይነበብ

(በድጋሚ የተለጠፈ)

ወጣቶችን ወስደው ምንድነው የሚያሰሯቸው ?

በኦንላይን ወይም በደላሎች አልያም በኤጀንሲዎች " እዚህ ሀገር ጥሩ ስራ አለ ፤ ክፍያውም ከፍ ያለነው " ተብለው ብዙ ወጣቶች ከተለያዩ ሀገራት ይዘዋወራሉ።

ለአብነት ያህል ወጣቶች ከሚዘዋወሩባቸው ሀገራት መካከል የሳይበር ማጭበበር ( Cyber Scam) ማዕከላት ተብለው ወደ ሚታወቁት ፦
• ማይናማር ፣
• ካምቦዲያ፣
• ላኦስ
• ማይናማር ታይላንድ ድንበር
• ቻይና ማይናማር ድንበር በዋነኝነት ይጠቀሳሉ።

እነዚህ አካባቢዎች ባሉ የተለያዩ ቦታዎች በኦንላይን ማጭበርበር ላይ የተሰማሩ በርካታ ድርጅቶች አሉ።

በእርግጥ መጀመሪያ ላይ ወጣቶቹን " እልካችኋለን " የሚሏቸው ሌሎች በኢኮኖሚና ደህንነት እጅግ ጠንካራ ፣ ጠንካራ ባይሆኑም እንኳን ያን ያህል የከፋ ሁኔታ ላይ ወደማይገኙ ሀገራት ነው።

እዛ ቦታ ከደረሱ በኋላ ግን የሚልኳቸው ወደ ጎረቤት ድሃ እና የህግ ስርዓት ወዳልጠነከረባቸው ሀገራት ይሆናል።

የሚሰራው ማጭበርበር ምንድነው ?

ስራ ብለው የሚልኳቸው መጀመሪያ ፦
- የኦላንይ ግብይት ስራ ማቀላጠፍ
- የኦንላይን ሴልስ ስራ
- የሆቴል እንግዳ ተቀባይ
- የማርኬቲንግ ስራ ... ሌላም ሌላም ነው።

ነገር ግን ስራ አለበት ወደ ተባለው ስፍራ ሲሄዱ የሚሰሩት ስራ መጀመሪያ ላይ ከተነገራቸው ተቃራኒ ነው።

የየራሳቸው ጋንግ አለቆች ባላቸው እጃቸውም ረጅም በሆኑ ሰዎች በሚመሩ የማጨበርበር ተግባር ላይ ወደ ተሰማሩ ድርጅቶች ያስገቧቸዋል።

እነዚህ ሰዎች ስልክ / ኮምፒየተር የሚያቀርቡላቸው ሲሆን በዛም ዓለም አቀፍ የማጨበርበር ስራ ላይ ያሰማሯቸዋል።

🔴 ዴቲንግ 🔴

የመጀመሪያ ስራቸው ከኢንተርኔት ላይ ውብ የሆኑ ሴቶችን / ስኬታማ ሴቶችን / ስኬታማ ወንዶችን ታዋቂ ሰዎችን ፎቶ በማውረድ የውሸት አካውንት መክፈት ነው።

በመቀጠል የሚያጭበረብሩትን ሰው ማናገር ይጀምራሉ። ምናልባትም በቅርብ የሚያውቋቸውን ሰዎችንም ሊሆን ይችላል።

እነዛን ሰዎች ልክ እንደ ኖርማል ሆነው ያለ ማቋረጥ ጊዜ ወስደው ያናግሯቸዋል።

የትኛውንም ጊዜ ይፍጅ ማናገራቸውን ይቀጥላሉ።

ስለ ውሸት ስራቸው፣ ስለ ህይወታቸው እየፈጠሩ ያወራሉ። በዚህ ውስጥ ምንም ምልክት አያሳዩም።

ወደ ፍቅር ከወሰዷቸውና ከጣሏቸው እምነትም ካገኙ በኃላ መጨረሻው ወደሆነው ዓላማቸው ገንዘብ ማስላክ ይገባሉ።

" ለምን እኔ ምሰራው ስራ ላይ ኢንቨስት አታደርም / አታደርጊም " በማለት ለምሳሌ ክሪፕቶ  ላይ ብለው ገንዘብ ይቀበላሉ።

በቃ አለቀ ! ገንዘባችሁ ተበልቶ ይቀራል። በኃላም ብሎክ አድርገው ይሸኟችኋል። ቀጣይ ሌላ ሰው ታርጌት ያደርጋሉ።

ወጣቶቹ ይሄን ካላደረጉ ምናልባትም ኢ-ሰብአዊ ቅጣት ሊፈጸምባቸው ይችላል።

⚫️ በጎ አድራጎት ⚫️

የውሸት ማንነት ፎቶ ተጠቅመው አካውንት ከፍተው (ሴትን በወንድ ወንድ ደግሞ በሴት ማንነት) አንድ ታርጌት ያደረጉትን ሰው ረጅም ጊዜ ያናግሩ እና ለእርዳታ / ለእርዳታ ድርጅታቸው ገንዘብ ድጋፍ እንዲያደርጉ ያሳምኗቸኣል።

እነዛ ሰዎች ላይ እምነት የጣሉባቸው ተጨበርባሪዎች በሀዘን ተሰብረው ገንዘባቸውን ይልካሉ። ቀልጦ ይቀራል። ብሎክ ይደረጋሉ።

🟡 ባለሃብት መምሰል 🟡

የውሸት ማንነት በመፍጠር ፣ ፎቶዎችን በመጠቀም በኦንላይን ሰው ያናግራሉ።

እንዲታመኑ ረጅም ጊዜ ሊወስዱም ይችላሉ።

ሰዎቹ ካመኗቸው በኃላ ገንዘባቸውን በጋራ አፍስሰው ስለሚሰሯቸው ስራዎች በማናገር ገንዘብ ያስልካሉ። ከዛማ ቀልጦ ይቀራል። ብሎክ ያደረጋሉ !

🟤 ደንበኞችን ማነጋገር 🟤

ይህም በተመሳሳይ በሀሰተኛ ማንነትና ስራ ከተለያዩ ሰዎች እያነጋገሩ በማጭበርበር ገንዘብ መቀበል ነው።

ለምሳሌ ፦ እቃ የሚሸጡ አስመስለው ብር ካስላኩ በኋላ የውሃ ሽታ ሆነው ይቀራሉ።

🔵 ' ኮሜንት/ሬት በማድረግ ገንዘብ አግኙ ' 🔵

እነዚ አጭበርባሪዎቹ የውሸት ማንነት ተጠቅመው በቴሌግራም ፣ ዋትስአፕ ወይም በሌላ መንገድ ተጠቅመው የሚያጭበረብሩትን ሰው ማናገር ይጀምራሉ።

" ጎግል ላይ ግቡና ስለዚህ ድርጅት ጥሩ አስተያየት ጻፉ ይከፈላችኋል " ይላቸዋል።

ከዛም የመጀመሪያውን ክፍያ በመፈጸም እምነት ያሳድራሉ።

" ይሄን ያህል ብር ከላካችሁ ይሄን ያህል ታገኛላቹ " በማለት የሰዎቹን ማንነት ይገመግማሉ። እስከዛ ድረስ ግን ገንዘብ መላካቸውን አያቆሙም።

የሚጭበረበረው ሰው ብዙ ብር ካስላኩት በኋላ የውሃ ሽታ ይሆናሉ።


በተጨማሪም ...

እንደ ፖሊስ፣ደህንነት፣ ባንክ ሰራተኛ ፣ እንደ ድርጅት ኃላፊ ሆነው የሚያስመስሉ አጭበርባሪዎችም አሉ።

ስራውን የሚሰሩት ሰዎችም ተጠቂዎች ናቸው።

ስራውን ካልሰሩ አሰቃቂ ጥቃት ሊደርስባቸው ይችላል።

እንደ ባሪያ ለረጅም ሰአትም ያሰሯቸዋል።

እንደ ቅርብ ጊዜ ሪፖርት ፥ በማይናማር፣ ካምቦዲያ፣ ላኦስ፣ ቻይና በመሳሰሉ ሀገራት ከ300 ሺህ በላይ ሰዎች በኦንላይ ማጭበርበር ላይ ተሰማርተዋል።

ስራዎቹንም የሚያሰሯቸው ሰዎች እጃቸው በጣም ረጅም ነው።

#TikvahEthiopia
#CyberScam

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM