TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ንቁ! #ሰውነት_ከምንም_ይበልጣል!
ሀገር
ብሄር
ዜግነት
ባንዲራ...ሁሉም ነገር እኛ እንደሰው ልጅ ካልተከበርን #አይጠቅሙንም። ሰው ሲገደል፣ ሰው ሲደበደብ፣ ሰው ሲፈናቀል ልባችን #ሊደማ የሚገባው የኛ #ብሄር ተወላጅ ስለሆነ አይደለም እንደኛ ሰው #ብቻ ስለሆነ መሆን አለበት። ያን ጊዜ ለሰማይም ለምድርም መልካም ስራን ሰርተን ማለፍ እንችላለን። ከሁሉም የሚበልጠው ሰውነት ብቻ ነው። ትግሬው የአማራው፤ አማራው የትግሬው ሞት ካላስለቀሰው፣ ኦሮሞው የአማራው፤ አማራው የኦሮሞው ሞት እና ስቃይ ካልተሰማው፣ ኦሮሞው የጋሞው ጋሞውም የኦሮሞው ችግር እና መከራ ካልተሰማው፣ ሲዳማው የወላይታው፤ ወላይታው የሲዳማው ሞት እና ስቃይ ካላስለቀሰው ችግሩ #የፖለቲካ ሳይሆን የሰውነት ስሜት መጥፋት ነው። የሰውነት ስሜት መጥፋት ደግሞ በቁም #መሞት ነው።

መፍትሄው....

እኔም አንተም አንቺም በገባን ልክ ስለሰው ክቡርነት እናስተምር። በየቤታችን ስለሰውነት እንነጋገር። ታች ወርደን ስለሰውነት እናስተምር። ሁላችንም ትልቅ ሀላፊነት አለብን! መጀመሪያ ሰው ሁሉ እንዲከበር፣ እንዲወደድ፣ እንዲፈቀር እንስራ!


ፀጋአብ ወልዴ
#ETHIOPIA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ንቁ‼️ያለማስተዋላችን ጥግ፣ ያለማገናዘባችን ጥግ፣ ያለማወቃችን ጥግ፣ የዝቅጠታችን ጥግ፣ ያለመማራችን ጥግ የኛ #ብሄር ተወላጆች ከኛ ጋር አብረውን የሚኖሩት #ብቻ ይመስለናል። ከብዙዎች ጋር ተጋብተው፤ ተዋልደ እንደሚኖሩ ማስተዋል አቅቶናል። ስራ ቦታ ከብዙሀኑ ጋር እንደሚሰሩ ረስተነዋል። ከብዙዎች ጋር ጎረቤት እንደሆኑ ረስተነዋል። በመላው ሀገሪቱ ውስጥ በሁሉም አቅጣጫ እንደሚኖሩ ዘንግተነዋል። ልጆቻችን ወንድሞቻችን እሩቅ ተጉዘው ከሌሎች ብሄር ወንድሞቻቸው ጋር እንደሚማሩ ዘንግተነዋል።

ዛሬ አንተ በፌስቡክ በምታሰራጨው ሀሰተኛ መረጃ፣ ያልተጣራ መረጃ፣ የጥላቻ መልዕክት፣ የእርስ በእርስ ግጭት ቅስቀሳ መልዕክቶች #እሳቱ ቢነሳ ከጫፍ ጫፍ ያለው ምስኪኑ ወገን ተቃጥሎ አመድ ይሆናል። እሳቱ ሀገር ውስጥ ብቻ ነዶ አይጠፋም ውጪ ያሉትንም ያቃጥላል። #አንተም አይቀርልህም #አመድ ትሆናለህ!

ለምናሰራጨው መረጃ እና መልዕክት ጥንቃቄ እናድርግ! የሰላም ዋጋዋን እንረዳ! ወገኖቼ እናስተውል የእርስ በእርስ ግጭት የሚቆመው ሁሉም ሲጠፋፋ ብቻ ነው!

በኃላ እንዳይፀፅተን እናስተውል!
አንድነት፤ ሰላም፤ ፍቅር!

ፀጋአብ ወልዴ
#ETHIOPIA

ፎቶ፦ የሩዋንዳው የእርስ በእርስ ግጭት
@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA(ተስፋ ኢትዮጵያ)!

በሺዎች የሚቆጠሩ አስተያየቶችን አንብቢያለሁ አብዛኛው ገንቢ እና አበረታች ነው። የሚያኮራና እኔ እንዲህ ነኝ የሚያስብል ሳይሆን ተጨማሪ ሰዓት ጨምሬ አንገቴን አቀርቅሬ እንድውል የሚያደርገኝ ነው። ትልቅ ሀላፊነት ነው ያሸከማችሁኝ። በነገራችን ላይ በስድብ ያጠረገረጉኝም እንደውም ከአንዱ #ብሄር አስገብተውኝ ለመሳደብ፤ ሞራሌን ለመንካት የጣሩም አሉ ግን ይህ የሚጠበቅ ነገር በመሆኑ እየሳቅኩ እና ለሰደቡኝ ሰዎችም ፈጣሪ ማስተዋልን እንዲሰጣቸው እየለመንኩ ነው ያነበብኩት። በአጠቃላይ ሁላችሁንም ከልቤ ተንበርክኬ አመሰግናለሁ። እውነት ተስፋ ሆናችሁኛል። ምኖርለት ነገር እንዳለኝ አሳይታችሁኛል።

*ፀጋአብ ወልዴ* ሰው ነኝ ሲቀጥል ኢትዮጵያዊ #ብቻ ነኝ!! እኔ እራሴን ማስበው ፈጣሪ ለሰው ልጅ ሁሉ የፈጠረኝ አድርጌ ነው። የሰዎችን ብሄር፣ እምነት እና ባህል እጅግ በጣም አከብራለሁ። እኔ ግን ከሁሉም ነኝ! እኔ ኦሮሞ፣ አማራ፣ ትግሬ፣ ሱማሌ፣ ሲዳማ፣ ወላይታ....ነኝ! የአንዱ ብቻ ሆኜ መኖር አልፈልግም። እንዲህ መኖር አትችልም ሰው ሆነህ መኖር አትችልም የሚለኝ አካል ከሀገሬ ያስወጣኝ።

እኔ እንደሰው የሁሉም ስቃይ እንዲሰማኝ፣ የሁሉም መከራ እንዲያሳዝነኝ፤ የሌላው ችግር የኔም ችግር እንደሆነ እንዲሰ ማኝ እፈልጋለሁ። ወዳጆቼ ከየትም ብሄር ይሁኑ እደሰው ስለማከብራቸው ቋንቋቸውን፤ ባህላቸውን እምነታቸውን አከብርላቸዋለሁ። እኔ ግን የሁሉም ሰው ልጅ ነኝ! ብሄሬ የሚያስጨንቀው ሰው ካለ ይህ ነው መልሴ እኔ ኦሮሞ፣ አማራ፣ ትግሬ፣ ሲዳማ፣ ወላይታ፣ ከንባታ፣ ሱማሌ፣ ጉራጌ፣ ስልጤ...ሁሉም ነኝ!

ሰው ሆኜ ስለተፈጠርኩ የሰው ሁሉ ስጦታ ነኝ!! ይህን ለማለት ያስገደደኝ ብሄር ተኮር ስድብ ስላስተናገድኩ ነው።

ወደ ቻናላችን ስመለስ....

1. ቻናሉን የትኛውም ድርጅት እና ግለሰብ ስለማያግዘው አሁንም ወደፊትም በማስታወቂያዎች ብቻ ነው የሚዘልቀው። ቻናሉ ብቻ ሳይሆን ምርታቸውን የሚያስተዋውቁ አካላትም የስራ እድላቸው ይሰፋል።

🔹ብዙዎች የማስታወቂያ መብዛት ቅር እንዳሰኛችሁ ግልፃችኃል ማስታወቂያዎች ይቀነሳሉ ለዚህም ዝግጅት ተደርጓል። አሁን እየተሰራበት ያለውም አሰራር ስንቀይረው በቀን የሚቀርበው ማስታወቂ ቁጥር ለመቀነስ ይሞከራል።

2. መረጃ ከበፊቱ እጅግ በጣም በተሻለ ፍጥነት ይቀርባል። ምንጮች የመንግስት ሚዲያዎች፣የግል ሚዲያዎች፣ ታዋቂ ግለሰቦች፣ እንዲሁም የTIKVAH-ETH የአይን እማኞች ይሆናሉ።

3. በየከተማው ያለ የመልካም አስተዳደር ቅሬታዎች ከበፊቱ በተሻለ ይቀርባል።

4. በቀን የተመጠኑ መረጃዎች ይቀርባሉ። መረጃ ነው እየተባለ እያመጣሁ ከዚህ በኃላ አለጥፍም። ጥራት እና ለህዝብ ጠቃሚነቱን አይቼ አቀርባለሁ።

5. አሁንም ገለልተኛ ሆኖ የሁሉም ድምፅ ይቀርብበታል።

6. በፍፁም የየትኛውም የፖለቲካ ድርጅት ልሳን ሆኖ አሰራም።

7. ዜናዎችን በፍጥነት ለማቅረብ ይሞከራል ። ፍጥነት ከጥንቃቄ ጋር ስለሆነ ወዲያው የሚሰራጩ መረጃዎች ችግር ፈጣሪም ስለሚሆኑ ጥንቃቄ ይደረጋል።

8. ከተለያዩ ገፆች መረጃዎችን ቀጥታ የማቀርበው በፌ ቡክ ያለውን የስድብ ኮሜንቶች እንድታነቡት ስለማልፈልግ ነው። ብዙ የtikvah ቤተሰብ አባላት ራሳቸውን ከፌስቡክ እያራቁ እንደሆነ ነግረውኛል።

የተጨመሩ፦

TIKVAH-ETH በአፕሊኬሽን ከሚተላለፉት ዜናዎች በተጨማሪ፦

.ምልከታዎች

.የውጭ ዜናዎች

.ጥቆማ

.ውይይት

. #UpdateSport የየዕለቱ ስፖርታዊ የሆኑ ጥቂት መረጃዎች

.የመዝናኛ ወሬዎች ከሀገር ውስጥ እና ከውጭ

.የቴክኖሎጂ ዜናዎች

.ልዩ ልዩ፦ ድንቃድቅ እውነታዎች

.🔹ላስተዋውቃችሁ🔹ይህ የምትኖሩበትን አካባቢ የምትገልፁበት መንገድ ነው። ከተማችሁን ታስተዋውቋታላችሁ። 15 መስመር በመሆን ፅሁፍና በፎቶ!

.የሙዚቃ ምርጫ(ሀገራዊ እና እጅግ በጣም አስተማሪ የሆኑ ሙዚቃዎች እጠቁማችኃለሁ)

.ቲፕ

ከላይ የተጨመሩት ቻናሉን የበለጠ ማራኪ ለማድረግ ታሶቦ ነው። ትልቁ ስራ ከመላው ኢትዮጵያ ምን እየሆነ እንዳለ እና በየቦታው ያሉትን መረጃዎች መዳሰስ ነው።

ሌላው አዲሱ ነገር ከዚህ ቀደም በአማርኛ ከእናተ የሚላኩ መረጃዎች የሚቀርቡ ሲሆን በእንግሊዘኛ ፅሁፍ የሚቀርቡትን ግን የመቅረብ እድላቸው አነስተኛ ነው በመሆኑም #በድምፅ መረጃዎችን ላኩ!! በድምፅ መረጃ ማስተላለፍ መጀመራችንን ስናበስ በደስታ ነው😁

🔹ማስታውቂያ የምታስነግሩ፦

1.ህጋዊ ብቻ
2.ተጠያቂ
3.እናተም ብቻ ሳይሆን ተገልጋዩን የሚጠቅም
4.አገልግሎት ሰጪዎች
5.በስራ ላይ የማይንቀሳቀሱ እና እንደው ለጊዜው ብቻ የተከፈቱ ቻናሎች አይተዋወቁም

🔹የተሻሻለውም የማስታወቂያ ህግ እና የአሰራር ሁኔታ ድርጅቶች ማየት ትችላላችሁ።

(ኮንትራት ያልጨረሳሁትን አይመለከተም። እናተ ያላችሁ ኮንትራት ሲያልቅ አዲሱን አሰራር ማየት ትችላላችሁ)

ይህ ለማድረግ የተገደድነው ገዘንብ ለማግበስበስ እና ትርፋማ ለመሆን አይደለም ማስታወቂያዎችን ለመቀነስ ብቻ ነው!!

ቻናሉ ገንዘብ ለመሰብሰብ እና ለማግበስበስ የተቋቋመ አይደለም! ሰዎችን እናግዝ ሰርተን አብረን እንስራ!!

ሌሎቹም በተመለከተ፦

.TIKVAH-EDU ለአሁን 2 ቋንቋዎች ላይ ይሰራል። ከቋንቋ በተጨማሪ ሌሎች ትምህርት ነክ ጉዳዮች ያስተናግዳል።

.TIKVAH-AID ሁሉም የሚሳተፍበት እና እገዛ ለሚያስፈልጋቸው ሰዎች በግላቸው አካውንት የምናግዝበት ነው። እንዲሁም አነቃቂ የእንተጋገዝ መልዕክቶች የሚቀርቡበት ነው።

.TIKVAH-AID 2 ይህ በኛው አካውንት እያሰባሰብን ለሰዎች የተለያዩ ድጋፎች የምናደርግበት እና የተስማሙ ብቻ የገቡበት ነው።

.TIKVAH-UNIVERSITY በዩኒቨርሲቲዎች ዙሪያ ሰፊ ስራ ለመስራት የሚቻልበት በየግቢው ያሉ እንቅስቃሴዎች የሚቀርቡበት ነው። የተለያዩ ማዕበራት በዚህ ላይ ተሳታፊ ሁኑ! አድሚም ሆናችሁ የግቢያችሁን ሁኔታ እና እንቅስቃሴ ለሌሎች አጋሩ!

አመሰግናለሁ!
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የዛሬ ውይይት‼️

በየቤታችሁ ቢያንስ ለ30 ደቂቃ ተወያዩ!!

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ፍፁም ባልተለመደ መልኩ በሀገራችን የተለያዩ ክፍሎች ግጭቶችን እያስተዋልን ነው። አንዳንዶቹ ከተማዎችማ ጭራሽ በግጭት ስማቸው ተነስቶ የማያውቅ እና በአስተማማኝ ሰላማቸው የተመሰከረላቸው ናቸው። ግጭቶቹን ከጀርባ ሆኖ የሚመራ አካል እንዳለም መንግስት በተደጋጋሚ ገልጿል። ግጭቶቹ ካለፉ በኃላም ዜጎች ድጋሚ ተመሳሳይ ነገር እንዳይከሰት ዘውትር እንደሰጉ ነው።
.
.
ዛሬ የምንወያየው ግን አሁን አሁን እየተስተዋለ ያለውን የሞራል ዝቅጠት ነው። ግለሰቦች በተጣሉ ቁጥር #ብሄራቸው ምንድነው?? ምን እና ምን #ብሄር ነው የተጣሉት? ተብሎ መጠየቅ ተጀምሯል። ይህ በእንዲህ ከቀጠለ ሀገሪቷን የማትወጣው ችግር ውስጥ እንከታታለን። ግለሰቦች እንደግለሰብ መፈረጅ እና መዳኘት ሲገባቸው የብሄር ተወካይ አድርጎ እርስ በእርስ ወደ አላስፈላጊ ግጭት መግባት ተገቢ አይደለም።

እናተስ በዚህ ጉዳይ ምን ትላላችሁ??
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ለዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች‼️

🔹የተለያዩ መረጃዎች በግቢያችሁ ውስጥ ሲሰራጩ ስለመረጃው ትክክለኝነት በደንብ አረጋግጡ። ሀሰተኛ መረጃዎችን እያሰራጩ ሀገሪቷን ለመበታተን እየሞከሩ ያሉ አካላት አሉ።

ሁሌም ጠያቂ እና ምክንያታዊ ሁኑ ከስሜታዊነት ውጡ እና ስለሰማችሁት ነገር በአግባቡ ጠይቁ፦

.ሴት ተደፈረች ስትባሉ (ማን የምትባል?? ስሟ ማነው?? የምን ተማሪ ናት?? ጓደኞቿ እነማን ናቸው?? የት ዶርም ነው የምትኖረው?? ቤተሰቦቿ ሰምተዋል?? ...)

.በሌሎች ጉዳይም ብዙ ጠይቁ። ተባራሪ ወሬ ከምትሰሙ የግቢውን አስተዳደር ለመጠየቅ ሞክሩ። ፕሬዘዳንቱን መጠየቅ ካለባችሁም ወደኃላ እንዳትሉ።

🔹ለታናናሾቻችሁ ትምህርት ሰጥታችሁ የምታልፉት መልካም እና ቀና አስተሳሰብ ሲኖራችሁ ብቻ መሆኑን አውቃችሁ በያላችሁበት ዘውትር ስለሰላም ምንነት አስቡ።

🔹በፍፁም የግለሰቦችን ፀብ ወደቡድን እንዲቀየር አትደግፉ። በእንደዚህ አይነት እንቅስቃሴ ውስጥ ያሉ ተማሪዎችንም ለመንግስት አሳልፋችሁ ስጡ። ማንም ከህግ በላይ ሆኖ መኖር አይችልምና።

🔹የሰው ልጅ ሲቸገር፣ ሲጎዳ፣ ሲደበደብ ስታዩ የምን #ብሄር ተወላጅ ነው? የሚለውን ጥያቄ ትታችሁ ሰው ክቡር ነው በማለት አጥፊውን ለመንግስት አሳልፋችሁ ስጡ። የሰውን ስቃይ በብሄር #እየከፈላችሁ የምትወዷት ሀገራችሁን ቁልቁል እንድትጓዝ በፍፁም አትፍቀዱ።

🔹ከፌስቡክ ሀሰተኛ ወሬዎች በቻላችሁት መጠን ራቁ። በፌስቡክ የሚሰራጩ መረጃዎችን እንደወረደ አትቀበሉ። የማያጋጩ የሚመስሉ ነገር ግን ሰዎችን ለግጭት የሚቀሰቅሱ መረጃዎችን ሼር ከማድረግ ተቆጠቡ።

🔹በፍፁም ታዋቂ ግለሰቦችን እንደፈጣሪ አትከተሉ። ግለሰቦቹን እና ሰፊውን ህዝብ ለዩ። ግለሰብ እና ብሄር ለዩ‼️ ግለሰብ ሲያጠፋ ብሄር አጠፋ ከሚል ዝቅተኛ አመለካከት ውጡ።

🔹ዘውትር ስለፍቅር አስቡ፤ ስለሰላም ተነጋገሩ! ሰላም ሲጠፋ የሚደርሰውን የከፋ ጉዳት ዘውትር ከማሰብ ወደኃላ እንዳትሉ።

🔹በህይወት ዘመናችሁ ሁሉ በፍፁም በሰዎች እንዳትነዱ። በመንጋ እንዳታስቡ።

🔹በእምነታችሁ ፅኑ የትኛውም ሀይማኖት ሰዎችን ስለማይከፍል በሀይማኖታችሁ በርቱ! ፈጣሪን ሁሌም ሰላም፣ አንድነት እና ፍቅር እንዲሰጠን ተማፀኑ። እውነተኛ ሰው ሁኑ! ጥዋት ቤተክርስቲያን ከሰዓት ደግሞ እርስ በእርስ ለመጋጨት ሰው ለመጉዳት ከመምከር ተቆጠቡ። መስጂድ ሄዳችሁ አላህ ማስተዋልን ብቻ እንዲሰጣችሁ ተማፀኑ! ሀይማኖት ካላችሁ ስልሰው ክቡርነት ትረዳላችሁ እና በየሀይማኖታችሁ ፅኑ! ተዋደዱ!!

በመጨረሻም፦ ኢትዮጵያን ጠብቋት! ድህነቷን ተመልከቱላት፤ ሳይበላ የሚያድረውን እዩላት፤ ተምራችሁ ወጥታችሁ በቻላችሁት መጠን ሀገራችሁን አገልግሉ።

ዩኒቨርሲቲዎች፦

🔹በዚህ በሰለጠነ ዘመን ኃላቀር አትሁኑ። ፌስቡክ ላይ ወሬ ሲወራ ጉዳዩን በአስቸኳይ አጣርታችሁ ከቻላችሁ በፌስቡክ ካልቻላችሁ በወረቀት ለተማሪው ግለፁ።

🔹ችግር ከደረሰ በኃላ ተማሪ ማወያየት ጥቅም አልባ ነውና በየትምህርት ክፍሉ ስለአንድነት እና ሰላም ውይይት እንዲደረግ አድርጉ።

🔹የተማሪ ህብረት ስራችሁን በአግባቡ ስሩ። በየዩኒቨርሲቲ ውስጥ ያላችሁ ክበባት ከወሬ ይልቅ በስራ ተጠመዱ።

🔹ጥበቃዎች ስለፈጠራችሁ ተማሪዎን ከፋፍሎ ከማየት ተቆጠቡ። የአካባቢው ልጅ ነው እያሉ ሌሎችን ጥሩ ባልሆነ መልክ ማየቱን አቁሙ። ሀላፊነታችሁን የማትወጡ ከሆነም ስራውን ልቀቁት ምክንያቱም አሁን ኢትዮጵያ የሚሰራላት ሰው ያስፈልጋታል።

🔹ዩኒቨርሲቲ ውስጥ ተማሪውን የሚያቀራርቡ ዝግጅቶች ቢኖሩ መልካም ነው!!

🔹ለሁሉም ተማሪ በቂ ጥበቃ እና ከለላ ሊደረግለት ይገባል።

ፀጋአብ ወልዴ~ኢትዮጵያ
@tsegabwolde @tikvahthiopia
ሰልፉ በሰላም ተጠናቋል~ሀዋሳ🔝

"ህገመንግሰታዊ #መብታችን_ይከበር!" በሚል መሪ ቃል በሀዋሳ ከተማ የተካሄከው ሰለማዊ ሰልፍ #በሰላም ተጠናቋል። በሰልፉ ላይ ከሲዳማ 36 ወረዳዎች እና ከተማ መስተዳድሮች የተውጣጡ እንዲሁም የሀዋሳ ከተማ ነዋሪዎች ተሳትፈውበታል።

ሰለማዊ ሰልፈኞቹ፦ “ህገ መንግስቱ እንዲከበር፤ የሲዳማ የክልልነት ጥያቄ መልስ እንዲሰጠው፤ የሪፈረንደም ቀን በአስቸኳይ ተወስኖ ለህዝብ እንዲነገር ጠይቀዋል።

በሰልፉ ላይ ሰልፈኞች ከያዟቸው መፈክሮች መካከል፦

•ሲዳማነት ከሌለ #ኢትዮጵያዊነት የለም!

•ለውጡን እንደግፋለን!

•በኮሚሽን የሚመለስ ጥያቄ የለንም!

•ለማንም ዘረኛ የማንበረከክ በባህላችን የምንኮራ ህዝን ነን!

•ህገ መንግስታዊ #መብታችን ይከበር!

•የሪፈረንደም ቀን #ተቆርጦ ይነገረን!

•የሲዳማ ህዝብ መንግስትን እንዳከበረ መንግስትም የሲዳማን ህዝብ ያክብር!

•ሁሉንም #ብሄር እንወዳለን፤ እናከብራለን!

•ሁሉንም #ሀይማኖት እንወዳለን፤ እናከብራለን!

•የሁሉንም #ባህል እንወዳለን፤ እናከብራለን! የሚሉት ይገኙበታል።

#ቲክቫህኢትዮጵያ #TIKVAHETHIOPIA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ኢትዮጵያን እንፈልጋታለን‼️

ምስኪኑ ዜጋ ሲፈናቀል፣ ሲሰቃይ፣ ሲቸገር፣ ተበደልኩ ሲል፣ ፍትህ ተነፍጊያለሁ ብሎ ሲጮህ፣ መንግስት በድሎኛል ብሎ ሮሮውን ሲያሰማ ለርካሽ #የፖለቲካ_ትርፍ እና #ሀገር_ለማትራመስ የምትሯሯጡ ጨካኝ አረመኔ ሰዎች ኢትዮጵያን ስለምንፈልጋት እጃችሁን ሰብስቡልን።

ሰዎች ሰውነታቸውን ክደው #ሀዘናቸውን እንኳን #ብሄር ለይተው እንዲገልፁ የምትገፋፉ ሰውነታችሁን የከዳችሁ ሁሉ #ኢትዮጵያን ስለምንፈልጋት እጃችሁን ከሀገራችን ላይ አንሱ።

በደንብ ስሙኝ...🔥

ህዝቡን በብሄር ከፋፍላችሁ #ወደጦርነት ለመክተት ፌስቡክ ላይ #ተዘፍዝፋችሁ የምትውሉ ሰዎች--የምትወዱትን ማጣት ስትጀምሩ፣ ምስኪን ህፃናት እንደቅጠል ሲረግፉ ማየት ስትጀምሩ፣ ሚሊዮኖች ሰላም ፍለጋ መሰደድ ሲጀምሩ ስታዩ ደም እምባ እያለቀሳችሁ እያንዳንዷን ፌስቡክ ላይ የዋላችሁበትን ቀን #ትረግሟታላችሁ
.
.
መንግስት በአስቸኳይ #ፍትህ እንፈልጋለን ብለው የሚጮሁ ዜጎች ካሉ ያዳምጥ፤ ምላሽ ይስጥ፤ በምስኪን ዜጎች ህይወት ላይ #ቁማር የሚጫወቱ የፖለቲካ ነጋዴዎችንም አደብ ያስገዛ!

#FACEBOOK ከብዶናል!
@tsegabwolde @tikvahethiopia
አቶ አዲሱ አረጋ‼️

"...ሰሞኑን #እርምጃ እየተወሰደባቸዉ ካሉ ከተሞች አንዱ በለገጣፎ ለገዳዲ ከተማ ነዉ፡፡ ይሁን እንጂ በማህበራዊ ሚዲያ እና በመደበኛ ሚዲያም ጭምር ህገ ወጥ ግንባታ ላይ እየተወሰደ ያለዉ እርምጃ በለገጣፎ ለገዳዲ ብቻ እየተደረገ ያለ እና #ብሄር ለይቶ #እርምጃ አስመስሎ እየቀረበ መሆኑን አስተዉለናል፡፡ ይህ #ስህተት ነዉ፡፡ እስካሁን በኦሮሚያ ክልል በሚገኙ 25 ከተሞች በተደረገ እንቅስቃሴም ህግን ብቻ ባማከለ 36,117 ህገ ወጥ ይዞታዎች እና ህገ ወጥ ግንባታዎች ላይ ህግን የማስከበር ስራ ተሰርቷል፡፡"

https://telegra.ph/ህገ-ወጥ-ግንባታን-በተመለከተ-አቶ-አዲሱ-አረጋ-02-22
8 ቀን ብቻ ቀረው! #እንገናኝ

የዚህ ገፅ ባለቤቶች ሁላችሁም እንደሆናቹ ታውቃላችሁ። ላለፉት አመታት ከተቸገረው ጋር ስትቸገሩ የቆያችሁ፣ በየቦታው ሰላም ሲደፈርስ ቁጭ ባላችሁ ስትጨነቁ ስታድሩ የቆያችሁ፣ እውነተኛና በአይናቹ ያያችሁትን የተረጋገጠ መረጃ ለህዝብ ስታደርሱ የቆያችሁ፣ የታመሙትን #ስታሳክሙ የቆያችሁ፣ በሀዘን ወቅት #ብሄር እና #ዘር ሳትለዩ ስለሰው ልጅ ሁሉ ስታለቅሱ የነበራችሁ፣ ለሀገራችሁ ሰላም መሆን የበኩላችሁን ድርሻ ስትወጡ የቆያችሁ፣ ለመልካም ነገሮ ቀድማችሁ ስትደርሱ የነበራችሁት እናተው ናችሁ!! አዎን ክብር ይገባችኃል!! በሰውነት ጥላ ስር ያሰባሰብን፤ በልዩነቶቻችን የምንከባበርበት፤ በንግግር ችግሮችን የምንፈታበት፤ ጥላቻን የምንፀየፍበት፤ ለሀገር ሰላም ቅድሚያ የምንሰጥበት TIKVAH-ETH #ቤታችን ከተመሰረተ እንሆ ሁለተኛ አመቱን ሊያከብር ሀምሌ 21 ቀጠሮ ይዟል። የዚህ ገፅ ባለቤት #እኔም ነኝ የምትሉ ሁሉ ይህ ቀን የናተ ነውና እሁድ ሀምሌ 21 በአበበች ጎበና ሕፃናት እንክብካቤ እና ልማት ድርጅት ተገኙ፤ ከእናታችሁም #ምርቃት ተቀበሉ!

@tsegabwolde @tikvahethiopia
6 ቀን ቀረው! #እንገናኝ

የዚህ ገፅ ባለቤቶች ሁላችሁም እንደሆናቹ ታውቃላችሁ። ላለፉት አመታት ከተቸገረው ጋር ስትቸገሩ የቆያችሁ፣ በየቦታው ሰላም ሲደፈርስ ቁጭ ባላችሁ ስትጨነቁ ስታድሩ የቆያችሁ፣ እውነተኛና በአይናቹ ያያችሁትን የተረጋገጠ መረጃ ለህዝብ ስታደርሱ የቆያችሁ፣ የታመሙትን #ስታሳክሙ የቆያችሁ፣ በሀዘን ወቅት #ብሄር እና #ዘር ሳትለዩ ስለሰው ልጅ ሁሉ ስታለቅሱ የነበራችሁ፣ ለሀገራችሁ ሰላም መሆን የበኩላችሁን ድርሻ ስትወጡ የቆያችሁ፣ ለመልካም ነገሮ ቀድማችሁ ስትደርሱ የነበራችሁት እናተው ናችሁ!! አዎን ክብር ይገባችኃል!! በሰውነት ጥላ ስር ያሰባሰብን፤ በልዩነቶቻችን የምንከባበርበት፤ በንግግር ችግሮችን የምንፈታበት፤ ጥላቻን የምንፀየፍበት፤ ለሀገር ሰላም ቅድሚያ የምንሰጥበት TIKVAH-ETH #ቤታችን ከተመሰረተ እንሆ ሁለተኛ አመቱን ሊያከብር ሀምሌ 21 ቀጠሮ ይዟል። የዚህ ገፅ ባለቤት #እኔም ነኝ የምትሉ ሁሉ ይህ ቀን የናተ ነውና እሁድ ሀምሌ 21 በአበበች ጎበና ሕፃናት እንክብካቤ እና ልማት ድርጅት ተገኙ፤ ከእናታችሁም #ምርቃት ተቀበሉ!

@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ሙስና📈 " ዛሬ እኮ አገልግሎት ተፈልጎ ክፍለ ከተማ ቢኬድ በግልፅ የሚጠየቅበት (ጉቦ) ሁኔታ ላይ ደርሰናል። ከዚህ በፊት እንደውም በካኪ ታሽጎ ፣ ተደብቆ ነው ሲሰጥ የነበረው " በኢትዮጵያ ውስጥ #ሙስና ከመቀነስ ይልቅ ከጊዜ ወደጊዜ እየጨመረ ፣ የሚፈፀምበትም መንገድ እየተራቀቀ ነው። የኢትዮጵያ ህዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም ፤ የትራንስፖርት ፣ የመሬት፣ የካርታ፣ የግንባታ ፍቃድ ፣ የመታወቂያ ...…
የሙስናው መባባስ . . .

የህግ ባለሙያ አቶ ጥጋቡ ደሳለኝ ፦

" ሙሰኞች ላይ የሚወሰድ እርምጃ ጠንካራ ስላልሆነ ሙስና ከመቀነስ ይልቅ እንዲጨምር ሆኗል።

የፖለቲካ መዋቅሩ በራሱ አጥፊዎች እንዳይጠየቁ እድል የሚሰጥ ነው።

ሰዎች ሙስና ሰርተው ሲያጠፉ በግልፅ ማስረጃ ቀርቦባቸው ጥፋተኛ መሆን ሲገባቸው እንደውም ከለላና ሽፋን ሲያገኙ ፣ ከበሉበት ቦታ ወደሌላ ቦታ ዘወር ሲሉ ፣ ሃብትና ንብረት እንዲያገኙ ሲመቻችላቸው ይታያል።

ይሄ ሁሉ የፖለቲካ ስሪቱ ነው። የፖለቲካ ስሪቱ ብሄርን መሰረት ያደረገ መሆኑነው። ይሄ ብሄርን መሰረት ያደረገ አደረጃጀት በሙስና ላይ የሰላ ትግል እንዳይደረግና ተጠያቂነት እንዳይመጣ ያደርጋል።

የፖለቲካ ስርዓቱ #ብሄር እና #ትውውቅን መሰረት ያደረገ በመሆኑ በአጥፊውና በጠያቂው መካከል ልዩነት እንዳይኖር ሆኗል።

መፍትሄው ሙስና የሚፈፅሙ አጥፊዎችን ተጠያቂ ለማድረግ ህጉን ጠንካራ ማድረግ ብቻ ነው። "

@tikvahethiopia