TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update አዲስ አበባ - ዛሬ⬇️

🔹1

ዛሬም በአዲስ አበባ አንዳንድ አካባቢዎች #ስንደቅ_አላማ በመስቀልና የከተማዋን ጎዳናዎች በማቅለም ዙሪያ አለመግባባቶች ታይተዋል። #አዲሱ_ገበያ አካባቢ የኦነግን አርማ ይሰቀል/ይቀባ በሚሉና ቀድሞ የተሰቀለው አረንጓዴ ቢጫ ቀዩ ስንደቅ #አናስነካም ባሉ ወጣቶች መካከል ግብ ግብ ተነስቶ ፖሊስ ጣልቃ ገብቷል። በአስለቃሽ ጭስ ወጣቶቹን መበተን ያቃተው ፖሊስ ጥይት ወደ ስማይ #ተኩሷል። ኋላም በዶፍ ዝናብ ምክንያት ወጣቶቹ #ተበትነዋል
.
.
🔹2

የአዲስ አበባ ወጣቶችም ሆኑ የኦነግ ደጋፊዎች ከጠብ #አጫሪነት እንዲቆጠቡ ይህ ካልሆነ ግን ፖሊስ የህዝቡን ደህንነት ለማስከበር #እርምጃ እንደሚወስድ የፌደራል ፖሊስ ኮምሽነር ዘይኑ ጀማል አስታወቁ። ባለፉት ሁለት ቀናት ለንብረት ውድመት ምክንያት የሆኑ ግጭቶች መከሰታቸውንና ሁኔታው ተባብሶ በፖሊስ ጣቢያዎች ላይ ጉዳት ለማድረስ ሙከራ መደረጉን የተናገሩት ኮምሽነር ዘይኑ ማናቸውም ዜጋ ያመነበትን የፖለቲካ ድርጅት አርማ ይዞ #የመውጣትና ተገቢ በሆኑ አካባቢዎች የመስቀል መብቱ የተከበረ ሲሆን፣ ጎዳናዎችንና የጋራ መገልገያዎችን #ቀለም መቀባት ግን ተገቢ አለመሆኑን አስረድተዋል።
.
.
🔹3

#የኦነግ አቀባበል ኮሚቴ በሰጠው መግለጫ የድርጅቱ ደጋፊዎች ከግጭት እራሳቸውን በማራቅ በሰላማዊ መንገድ እንዲንቀሳቀሱ #አሳስቧል

ምንጭ፦ ዋዜማ ራድዮ
@tsegabwolde @tikvahethiopia