TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update ከቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልል የተፈናቀሉ ዜጎችን ወደ ቀያቸው #ለመመለስ ከአካባቢው ነዋሪዎችና ከአገር ሽማግሌዎች ጋር ለመስራት በዝግጅት ላይ መሆኑን የብሔራዊ አደጋ ስጋትና ስራ አመራር ኮሚሽን አስታወቀ።

የአካባቢው ነዋሪዎችና ለጋሽ ድርጅቶች የተፈናቀሉ ዜጎችን ለመርዳት ያሳዩት ተነሳሽነት ከፍተኛ ቢሆንም ከችግሩ ስፋት አንጻር #ተጨማሪ ድጋፍ እንደሚያስፈልግ ተገልጿል።

የኮሚሽኑ የህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ደበበ ዘውዴ ለኢዜአ እንደተናገሩት የተፈናቀሉ ዜጎችን ወደ ቀያቸው ለመመለስ #በባህላዊና #ሃይማኖታዊ ስነ-ስርዓት ዕርቅ ለማውረድ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች እየተሰሩ ነው።

በተለይ የሃይማኖት አባቶች፣ የአገር ሽማግሌዎች፣ ወጣቶች፣ የየአካባቢው ነዋሪዎችና የመንግስት አካላት በተገኙበት እርቅና ሰላም የማውረድ ስራ ይሰራል ብለዋል።

ኮሚሽኑ ተፈናቃዮቹ ከሚገኙበት የኦሮሚያ ክልል መንግስት ጋር በቅንጅት በመስራት ላይ ሲሆን ድጋፉን ለማጠናከር ተጨማሪ የባለሙያዎች ቡድን ወደ ስፍራው መላኩንም ገልጸዋል።

ኮሚሽኑ እስካሁን ከአካባቢው ለተፈናቀሉ ዜጎች 17 ሺህ 468 ኩንታል ስንዴ ሩዝና አልሚ ምግብ፣ 146 ሺህ 194 የመመገቢያ ቁሳቁስ መጠለያና አልባሳትና 1 ሺህ 101 ካርቶን የዱቄት ወተት ወደ ስፍራው መላኩን ገልጸዋል።

ከዚህ በተጨማሪ ለተፈናቀሉ ዜጎች ከዳሸን ባንክ አምስት ሚሊዮን ብር ድጋፍ ሲደረግ ከቡራዩና አካባቢዋ ለተፈናቀሉም እንዲሁ በሲውዘርላንድ የሚገኙ ትውልደ ኢትዮጵያዊያንና ኤርትራዊያን 600 ሺህ ብር ድጋፍ አድርገዋል።

ኮሚሽኑ እንዳስታወቀው ሰሞኑን ከቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልል ተፈናቅለው በምዕራብና ምስራቅ ወለጋ 10 ወረዳዎች የሚገኙ ሰዎች ቁጥር 91 ሺህ 348 ደርሷል።

▪️በተጨማሪ በመላው አገሪቱ በመደበኛነት #በድርቅ አደጋ የሚረዱ ከሰባት ሚሊዮን በላይ ዜጎች ያሉ ሲሆን ለጋሽ አካላት የተለመደ ትብብራቸው እንዲያደርጉ ጠይቋል።

በተለይ ዲያስፖራው፣ ባለሃብቶችና ሌሎችም ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪ የቀረበ ሲሆን ይህንን ለመምራት የሚያስችል ኮሚቴ መዋቀሩንም ገልጸዋል።

በቅርቡ በምዕራብ ጉጂ፣ በጌዲኦ፣ በሶማሌና በቡራዩ የተፈናቀሉ ዜጎችን ወደ ቀያቸው ለመመለስ በባህላዊ ስነ-ስርዓት የሕዝብ ለሕዝብ ስራ መሰራቱ ይታወሳል።

ምንጭ፦ ኢዜአ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ለመላው ኢትዮጵያዊያን‼️

"በመላው አገሪቱ በመደበኛነት #በድርቅ_አደጋ የሚረዱ ከሰባት #ሚሊዮን በላይ ዜጎች አሉ ለጋሽ አካላት የተለመደ #ትብብራቸው እንዲያደርጉ ተጠይቋል።"
.
.
አንዳንዶቻችን ይሄን ረስተነው ይሆን በትንንሽ ጉዳዮች ተለያይተን እየተባላን የምንውለው?? ዛሬም በብሄር ተከፋፋለን የምንበሻሸቀው?? በጥላቻ ተሞልተን ስንሰዳደብ የምንውለው?? ዛሬም ሀገራችን #ለጋሾች እጃቸውን እንዲዘረጉላት #እየተማፀነች ነው። ዛሬም በሀገራችን በድርቅ አደጋ የሚረዱ በሚሊዮኖች ናቸው። ወገኖቼ ይህን ታሪካችንን እስከወዲያኛው ልንቀይር ይገባናል። ይህን መጥፎ ስም የምንቀይረው #በፌስቡክ ብሽሽቅ እና ስድብ፤ ግለሰቦች እና ቡድኖች በሚሰጡን አጀንዳዎች እየተባላን አይደለም‼️ ተባብረን ሰርተን ከዚህ የደህነት እና የችግር ስም መውጣት አለብን‼️

ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!
ፀጋአብ ወልዴ~ኢትዮጵያ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update የአውሮፓ ህብረት በአፍሪካ ቀንድ #በድርቅ ለተጠቁ አራት ሃገራት የሚውል የ55.9 ሚሊዮን ዶላር የአስቸኳይ ጊዜ የሰብዓዊ እርዳታ ለማቅረብ እያስተባበረ መሆኑን ዘ-ኢስት አፍሪካ ዘገበ፡፡

@tsegabwolde @tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
አፍሪካ ቀንድ 🇸🇴🇪🇹🇰🇪

እንደ ዓለም ምግብ ፕሮግራም መረጃ በአፍሪካ ቀንድ ከ20 ሚሊዮን በላይ ሰዎች #በድርቅ#በግጭት እና #በምግብ_ውድነት ምክንያት አስከፊ ለሆነ ረሃብ ተጋልጠዋል።

የዓለም ምግብ ፕሮግራም በኢትዮጵያ፣ ኬንያና ሶማሊያ ላሉ ቤተሰቦች እገዛ ለማድረግ እየሰራ ይገኛል።

#ShareTheMeal (በUN | WFP ስር ያለ) በድርቅ ምክንያት ለተጎዱ ቤተሰቦች የድንገተኛ ጊዜ የገንዘብ ድጋፍ የሚያደርግ ሲሆን ለዚሁ ስራ የሚውልን ገንዘብ ከለጋሾች በመተግበሪያው እንዲሁም በድረገፁ በኩል እያሰባሰበ ይገኛል። https://t.co/rjY1JlrJTl

@tikvahethiopia