TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ችሎት

ባለሀብቶችን በመሰለል፣ በማገት እና በማስፈራራት ገንዘብ በጠየቁ እና በተቀበሉ አራት የመከላከያ ሚኒስቴር አባላትና ግብረአበሮቻቸው ላይ ስልጣንን አላግባብ በመገልገል ከባድ የሙስና ወንጀል ስር ክስ ተመሰረተ።

የመከላከያ መኪና በመያዝ ከጠቅላይ ዐቃቤ ህግ ሃብት ማስመለስ የመጣን ዐቃቤ ህጎች ነን ህገ ወጥ ዘይት߹ ስኳር እና የጦር መሳርያ ስለምትሸጡ በወንጀል ትፈለጋላችሁ በማለት 8 ነጥብ 5 ሚሊየን ብር በጠየቁ የመከላከያ ሚኒስቴር አባላትና ግብረ አበሮቻቸው ላይ ክስ ተመስርቷል።

የተለያዩ የምርምራ ሂዶትችን ከፖሊስ ጋር ሲያከናውን ቆይቶ በግለሰቦች ላይ ክሱን የመሰረተው ደግሞ በጠቅላይ ዐቃቤ ህግ ዘርፍ የሙስና ወንጀል ጉዳዮች ዐቃቤ ህግ ዳይሬክቶሬት ጄነራል ነው ።

ወንጀሉን ፈጽመዋል በሚል ክስ የተመሰረተባቸው በመከላከያ ሚኒስቴር በ93ኛ እና 94ኛ እግረኛ ክፍለ ጦር አባል የሆኑት ፦

• 1ኛ መቶ አለቃ ሀጂ ቱሉ ߹
• 2ኛ ኦፊሰር መንግስቱ በቀለ ߹
• 3ኛ ሻምበል ካህሊ መላክ ߹
• 4ኛ ሻለቃ ዱጉማ ዲምሳ እና በተለያዩ የንግድ ስራዎች ውስጥ ተሰማርተው የሚገኙት ግብረ-አበሮቻቸው ከ5ኛ-8ኛ ስማቸው በክሱ የተጠቀሰው ተከሳሾች ሹምበዛ ፍቃዱ፣ አዲስ አለሙ፣ ተስፋዬ ለሚ እና አሸናፊ ወልደ ሰማያት ናቸው፡፡

➡️ ተከሳሾች ከጳጉሜ 03/2013 ዓ.ም እስከ የካቲት 13/2014 ዓ.ም ባሉት ጊዚያት ውስጥ በቡድን በመደራጀት ባለሀብቶችን ኢላማ አድርገው ጥናት በማድረግ የማይገባቸውን ጥቅም ለማግኘት በማሰብ በዐቃቤ ህግ ክስ ላይ እንደተመለከተው 2ኛ ፣ 4ኛ እና 5ኛ ተከሳሾች ታርጋ የለጠፈ የመከላከያ መኪና ይዘው ወደ ግል ተበዳይ መኖርያ ቤት በመሄድ ተበዳይ በወንጀል እንደተጠረጠረ በማስመሰል በመኪና አግተው ከወሰዱት በኋላ ህገ ወጥ ዘይት߹ ስኳርና የጦር መሳርያ ትሸጣለህ እንድንለቅህ የምትፈልግ ከሆነ 5 ሚሊየን ብር ክፈል ካልከፈልክ ግን ልጆችህን ጭምር እንገላቸዋለን ብለው ካስፈራሩ በኋላ 710,000 ( ሰባት መቶ አስር ሺ ) ብር ተቀብለዋል።

➡️ በሌላ ሁለተኛ ክስ ደግሞ ሌላ ተበዳይ መኪና እያሽከረከረ እያለ 5ኛ እና 7ኛ ተከሳሽ በመከላከያ መኪና ሲከተሉት ስጋት ስለገባው ለላፍቶ ፖሊስ ጣቢያ ኣዛዥ ጉዳዩን ያስረዳ ቢሆንም ሁለቱ ተከሳሾች የፖሊስ ጣቢያ አዛዡን ”ከደህንነት ነው የመጣነው” ግለሰቡ በብዙ ወንጀሎች ይፈለጋል አለቃችንም እየመጣ ነው ካሉ በኋላ 8ኛ ተከሽ አንደ አለቃቸው ሆኖ በመምጣት ፖሊስ ጣቢያ እንደሚታሰር ገልፀው ተበዳይ እህቱን አንዲጠራት ካደረጉ በኋላ እህቱንም ጭምር በመያዝ ይሄ የሕይወት ጉዳይ ነው እህትህን እንድንለቃት የምትፈልግ ከሆነ 3 ሚሊየን ብር ክፈል ብለውታል።

➡️ በ3ኛ ክስ ቀኑ በውል ባልታወቀ በመስከረም ወር 2014 ዓ.ም ደግሞ ወ/ሮ አዜብ በርሔ የተባለች ግለሰብን 5ኛ እና 7ኛ ተከሳሽ ”ከጠቅላይ ዐቃቤ ህግ ሃብት ማስመለስ ዐቃቤ ህጎች ነን” በማለት ተበዳይን ባለቤትሽ ጄነራል ነው ትግራይ በመሄድ እያዋጋ ነው ቤትሽን በተመለከተም እያጣራን ስለሆነ አጠቃላይ የቤት ካርታና ሌሎች ሰነዶችን ኮፒ አድርገሽ አምጭ ብለው ከተቀበሏት በኋላ እንድንረዳሽ ከፈለግሽ 500 ሺህ ብር ክፈይ ሲሏት የመክፈል አቅም እንደሌላት ገልፃ ህጋዊነታቸውን ስትጠይቃቸው 8ኛ ተከሳሽን አናግሪው በማለታቸው 8ኛ ተከሳሽ የመከላከያ ታርጋ የለጠፈ መኪና ይዞ በመምጣት ተበዳይን አግኝቶ “ሰዎቹ ህጋዊ ናቸው የሚሉሽን አድርጊ እኔ የመከላከያ ሚኒስቴር አባል ነኝ አሁን ሃብት ማስመለስ ስራ ላይ ነው የምሰራ ” በማለት ከሁለቱ ተበዳዮች በአጠቃላይ 405 ሺ ብር ተቀብለዋል።

በዚህም ተከሳሾች በዋና ወንጀል አድራጊነትና ተካፋይ በመሆን በፈፀሙት ስልጣንን ያለአግባብ መገልገል ከባድ የሙስና ወንጀል ነው እንደ ወንጀል ተሳትፏቸው በዐቃቤ ህግ ክስ የተመሰረተባቸው።

ከ1ኛ - 6ኛ ያሉት ተከሳሾች ዛሬ ግንቦት 22 ቀን 2014 በፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ 5ኛ ወንጀል ችሎት ቀርበው የክስ ማመልከቻው አንዲደርሳቸው ተደርጎ ክሱ በንባብ እንዲሰማ ተደርጓል።

ችሎቱ በቁጥጥር ስር ያልዋሉትን 7ኛና 8ኛ ተከሳሽን ፖሊስ አፈላልጎ አንዲያቀርብ ትዕዛዝ የሰጠ ሲሆን ተከሳሾች በተመሰረተባቸው ክስ ላይ የመጀመርያ የክስ መቃወሚያ እና ባልተያዙ ተከሳሾች ላይ የፖሊስን ምላሽ ለመጠባበቅ ለግንቦት 29/2014 ዓ.ም ቀጠሮ ተሰቷል።

ምንጭ፦ የፍትህ ሚኒስቴር

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#የነዳጅ_ዋጋ_ጭማሪ ከነገ ሚያዚያ 30 ጀምሮ የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ላይ ጭማሪ ተደርጓል። በዚህም ፦ 👉 ቤንዚን በሊትር 36 ብር ከ87 ሳንቲም ፣ 👉 ነጭ ናፍጣ በሊትር 35 ብር ከ43 ሳንቲም፣ 👉 ኬሮሲን በሊትር 35 ብር ከ43 ሳንቲም፣ 👉 ቀላል ጥቁር ናፍጣ በሊትር 52 ብር ከ45 ሳንቲም፣ 👉 ከባድ ጥቁር ናፍጣ በሊትር 51 ብር ከ78 ሳንቲም 👉 የአውሮፕላን ነዳጅ በሊትር…
#ሰኔ

የቤንዚን፣ የናፍጣ እና የኬሮሲን የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ባለበት ይቀጥላል።

የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ፤ በሰኔ ወር 2014 ዓ.ም የቤንዚን፣ የናፍጣ እና የኬሮሲን የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በግንቦት ወር ሲሸጥበት በነበረው እንደሚቀጥል አስታውቋል።

የአውሮፕላን ነዳጅ፣ የቀላል ጥቁር ናፍጣ እና የከባድ ጥቁር ናፍጣ የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በዓለም አቀፍ ዋጋ ተሰልቶ የመጣው ልዩነት ሙሉ በሙሉ ወደ ተጠቃሚው እንዲተላለፍ መወሰኑን ገልጿል።

ምንጭ፦ የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር

@tikvahethiopia
#Eritrea

ባለፉት ሁለት ቀናት ከጎረቤት ኤርትራ ሠራዊት ጋር አዲስ ውጊያ መካሄዱን የህወሓት ቃል አቀባይ አቶ ጌታቸው ረዳ ገልፀዋል።

አቶ ጌታቸው ዛሬ ግንቦት 22/2014 ዓ.ም አመሻሽ ላይ እንዳሉት ባለፈው ቅዳሜ እና እሑድ (ግንቦት 20 እና 21 ቀን 2014 ዓ. ም.) የኤርትራ ሠራዊት በሽራሮ ጥቃት ከፍቶ ነበር ብለዋል።

በውጊያው አንድ የኤርትራ ጦር ብርጌድ አዛዥ እና 3 የሻለቃ አዛዦች የሚገኙባቸው 120 ወታደሮችን እንደተገደሉ 195 ያህሉን እንዳቆሰሉ እና 4 ወታደሮችን እንደተማረኩ ተገልጿል። አንድ ድሽቃ፣ አምስት የወታደራዊ ሬዲዮ መገናኛዎች እና በርካታ የጦር መሳሪያዎች ከኤርትራ ጦር እንደተማረከም ተገልጿል።

ቅዳሜና እሁድ ተከሰተ ካሉት ወታደራዊ ግጭት በተጨማሪ ከ4 ቀናት በፊት ግንቦት 16 ቀን 2014 ዓ. ም. የኤርትራ 57ኛ እና 21ኛ ክፍለ ጦር ወደ ትግራይ ክልል ጥቃት ሰንዝሮ እንደነበርና አዲአዋላ በተባለው አካባቢ ይህንን ጥቃት መመከት እንደተቻለ አሳውቀዋል።

አቶ ጌታቸው ዓለማቀፉ ኅብረተሰብ የኤርትራን መንግሥት ድርጊት በቃ እንዲለው ጥሪ አቅርበዋል።

ይህን ጉዳይ በተመለከተ የኢትዮጵያ መንግሥት ቃል አቀባይ ዶ/ር ለገሰ ቱሉ ለቢቢሲ በሰጡት ቃል ተካሄደ ስለተባለው ውጊያ መረጃው እንደሌላቸው ገልጸው፣ ነገር ግን የኤርትራ ኃይሎች ጥቃት ሊፈጽሙ የሚችሉበት ሁኔታ የለም ብለዋል።

ዶ/ር ለገሰ " ህወሓቶች ራሳቸው ትንኮሳ ፈጽመው " የሚያሰሙት ክስ ሊሆን ይችላል ሲሉ ገልፀዋል። በአሁኑ ጊዜ " በኤርትራ በኩል ጦርነት ይከፈታል የሚል እምነት የለንም " ያሉት ዶ/ር ለገሰ የተከሰተ ነገር ካለም አጣርተው መረጃ እንደሚሰጡ መግለፃቸውን ቢቢሲ ዘግቧል።

በኤርትራ መንግስት በኩል እስካሁን የተባለ ነገር የለም።

@tikvahethiopia
" የጋዜጠኞች የዘፈቀደ እስር እንቃወማለን ፤ የህግ የበላይነት ይከበር "

የመብቶች ዴሞክራሲ ዕድገት ማዕከል (ካርድ) እና 7 የተለያዩ ማህበራት በጋራ ባወጡት አጭር መግለጫ በጋዜጠኞች ላይ የዘፈቀደ እስር እየተፈፀመ መሆኑን በመግለፅ ድርጊቱን እንደሚቃወሙ ገልፀዋል።

በመግለጨው ባለፉት 2 ሳምንታት 18 ጋዜጠኞች እና የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች በድንገተኛ ዘመቻ መታሰራቸውን አንስተው ፤ ጋዜጠኞች የህግ መተላለፍ ከተገኘባቸው እንደማንኛውም ዜጋ በፍትሃዊ የህግ ሂደት ተጠያቂ ሊሆኑ ይገባል ብለዋል።

ነገር ግን በየጊዜው የሚደረጉ የጋዜጠኞች እስሮች በተደጋጋሚ የህግ አግባብ ሲጥሱ እየተስተዋለ ነው ሲሉ ገልጸዋል።

አክለውም ፤ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን አዋጅ ሕግ 1238/2013 አንቀፅ 86/1 " በመገናኛ ብዙሃን አማካኝነት የወንጀል ድርጊት በመፈፀም የተጠረጠረ ማንኛውም ሰው ወይም አካል በወንጀል ስነስርዓት ህግ ድንጋጌዎች መሰረት ለተጨማሪ ምርመራ በእስር እንዲቆይ ሳይደረግ ክሱ በቀጥታ በአቃቤ ህግ አማካኝነት ወደ ፍርድ ቤት መቅረብ አለበት " ይላል ፤ ይሁንና የታሰሩ የመገናኛ ብዙሃብ ሰራተኞች ምንም ክስ ሳይመሰረትባቸው ፣ ለቅድመ ክስ ምርመራ በሚሰጥ ቀጠሮ በአስቸጋሪ ሁኔታ ከቤተሰብና ወዳጅ ጥየቃ ርቀው እንዲቆዩ እየተደረገ ነው " ሲሉ አመልክተዋል።

ይህ የህግ አግባብን ያልተከተለ አሰራር ፣ ለህግ የበላይነት ፣ ለሚዲያ ነፃነት ፣ ለጋዜጠኞች ደህንነት እና ለኢትዮጵያ ሰላም እና መረጋጋት አደጋ የሚፈጥር ስለሆነ አጥብቀን እናወግዛለን ብለዋል።

የሚመለከታቸው አካላት በእስር ላይ የሚገኙ የመገናኛ ብዙሃን አካላት በአስቸኳይ ከእስር ተለቀው የህግ የበላይነት እንዲከበር ሲሉ በመግለጫቸው ጥሪ አቅርበዋል።

(መግለጫውን ያወጡት ማህበራት ዝርዝር ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia
" የዝንጀሮ ፈንጣጣ / መንኪፖክስ / ዓለም አቀፍ ወረርሽኝ ደረጃ ይደርሳል ብለን አንጠብቅም " - የዓለም የጤና ድርጅት

እስካሁን በመቶዎች የተቆጠሩ ሰዎች መያዙ የታወቀው መንኪፖክስ ወይም የዝንጀሮ ፈንጣጣ ዓለም አቀፍ ወረርሽኝ ደረጃ ይደርሳል ብለው እንደማይጠብቁ የዓለም የጤና ድርጅት ከፍተኛዋ የበሽታው ኤክስፐርት ተናገሩ።

ያን ይበሉ እንጂ በሽታው እንዴት እንደሚስፋፋ ሆነ ከአያሌ አሰርት በፊት የፈንጣጣ መከላከያ ክትባት ዘመቻ መቋረጡ ያስከተለው አንድምታ ይኖር እንደሆን ጨምሮ ብዙ የማይታወቁ ነገሮች መኖራቸውን አልደበቁም።

ዶክተር ሮዛሙንድ ሉዊስ በሰጡት ማብራሪያ ድርጅታቸው መንኪፖክስ በግብረ ስጋ ግንኙነት ወይም በአየር በትንፋሽ ይተላለፍ እንደሆን በተጨማሪም የህመም ምልክት የሌላቸው ሰዎች በሽታውን ያስተላልፋሉ ወይ የሚሉትን ጨምሮ በርካታ ጥያቄዎችን ይዞ እየመረመረ መሆኑን አመልክተዋል።

ካሁን ቀደም በሽታው በተቀሰቀሰባቸው ጊዜያት በቀላሉ የሚዛመት እንዳልሆነ ታይቷል ያሉት የዓለም የጤና ድርጅቱ ባለሙያ አሁንም ሥርጭቱን ለመቆጣጠር ጊዜ እንዳለ መግለፃቸውን ቪኦኤ /VOA ዘግቧል።

#VOA

@tikvahethiopia
#Ashewa

አሸዋ ቴክኖሎጂ የድጅታል ኢኮኖሚው ላይ የሚሰራ የዘልማዱን ግብይት በአፍሪካ ላይ የሚቀይር፣ ህይወት የሚያቀል፣ የሚያዘምን፣ የሚያሻግር ነው። ባሁኑ ሰአት በአገራችን ያለውን የንግድ ሰንሰለት ችግር ሊቀርፍ፣ አምራቹን በቀጥታ ከሸማቹ ጋር ከኑሮ ውድነት ሊገላግል ብዙ የክፍያ እና ደሊቨሪ አማራጮችን ይዞ በኢኮሜርሱ ዘርፍ በኩል ስራውን መጀመሩን ስናበስራችሁ ትልቅ ኩራት ይሰማናል።

ግዙ ሽጡ በአዲስ አበባ ላይ https://bit.ly/3smsyrx

ድርጅቱ ላይ ኢንቨስት ለማድረግ እና ትርፍ ተካፋይ ለመሆን Ashewatechnology.com
ስልክ ፦ 0976005500 or 0976005100

Join our telegram channel
t.me/ashewatechnology
ከዓለም ዙሪያ ፦

#ካናዳ ፦ የካናዳው ጠ/ሚ ጀስቲን ትሩዶ አነስተኛ የእጅ ሽጉጥ መግዛትም ሆነ መታጠቅ እንዲከለከል ጠይቀዋል። የትሩዶ መንግሥት በጠቅላላው የእጅ ሽጉጥ መግዛት ሆነ ቤት ማስቀመጥ በሕግ እንዲያስቀጣ ረቂቅ እያወጣ ነው። ረቂቁ እንደሚለው ካናዳዊያን የእጅ ሽጉጦቻቸውን ባይነጠቁም ከዚህ በኋላ አዲስ መግዛት ግን አይችሉም። ትሩዶ ይህን ሐሳብ ያፈለቁት በአሜሪካዋ ቴክሳስ ግዛት አንድ አፍላ ታጣቂ 19 ሕፃናትን ተኩሶ ከገደለ በኋላ ነው።

➡️ #እስራኤል #UAE ፦ እስራኤል እና የተባበሩት አረብ ኤሜሬትስ የነፃ ንግድ ስምምነት ተፈራርመዋል ፤ ይህ እስራኤል ከአረብ ሀገር ጋር ያደረገችው የመጀመሪው ትልቅ ስምምነት ነው።

➡️ #ሴኔጋል ፦ የሴኔጋል ፖሊስ በአንድ ሆስፒታል ውስጥ በደረሰው እና የ11 ህጻናት ህይወት ከቀጠፈው የእሳት አደጋ ጋር በተያያዘ ለመጀመሪያ ጊዜ ተጠርጣሪ በቁጥጥር ስር ማዋሉ ተሰምቷል።

➡️ #ሩስያ ፦ በያዝነው ዓመት 70ኛ ዓመታቸውን የሚደፍኑት የሩስያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን በጤና እክል ምናልባትም በካንሰር ህመም እየተሰቃዩ ሳይሆን አይቀርም የሚሉ ያልተረጋገጡ የመገናኛ ብዙኃን ሪፖርቶች እየወጡ ናቸው። የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌ ላቭሮቭ ግን ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ታመዋል መባሉን ሀሰት ሲሉ አስተባበሉ። ላቭሮቭ ፕሬዚዳንት ፑቲን በየቀኑ በአደባባይ እንደሚታዩ እና እንደማኛውም ጤነኛ ሰው የህመም ምልክት አያታይባቸውም ብለዋል።

➡️ #ሶማሊያ ፦ የሶማሊያ ባይዶዋ ከተማ ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ ሞሐመድን ለመቀበል በዝግጅት ላይ ነች። ከተማዋ ፕሬዝዳንቱ ፈርማጆን አሸንፈው ዳግም የፕሬዜዳንትነት መንበሩን ከተረከቡ በኃላ ለመጀመሪያ ጊዜ የሚጎበኟት ከተማ ትሆናለች።

#ቢቢሲ #ቲአርቲ #ሲጂቲኤን #SNTV

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Eritrea ባለፉት ሁለት ቀናት ከጎረቤት ኤርትራ ሠራዊት ጋር አዲስ ውጊያ መካሄዱን የህወሓት ቃል አቀባይ አቶ ጌታቸው ረዳ ገልፀዋል። አቶ ጌታቸው ዛሬ ግንቦት 22/2014 ዓ.ም አመሻሽ ላይ እንዳሉት ባለፈው ቅዳሜ እና እሑድ (ግንቦት 20 እና 21 ቀን 2014 ዓ. ም.) የኤርትራ ሠራዊት በሽራሮ ጥቃት ከፍቶ ነበር ብለዋል። በውጊያው አንድ የኤርትራ ጦር ብርጌድ አዛዥ እና 3 የሻለቃ አዛዦች የሚገኙባቸው…
#Update

የኢትዮጵያ መንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዶ/ር ለገሰ ቱሉ ህወሃት " የኤርትራ ጦር ጥቃት ከፈተ " በሚል የሚያሰራጨው መረጃ ትክክል አይደለም አሉ።

ሚኒስትሩ ይህን ያሉት ለአል ዓይን አማርኛ አገልግሎት በሰጡት ቃል ነው።

ዶ/ር ለገሰ ትንኮሳ ያደረገው ህወሃት ነው ፤ የተመቱትም ራሳቸው የህወሃት ታጣቂዎች ናቸው ብለዋል።

በኤርትራና በህወሃት መካከል ግጭት እንዲፈጠር ያደረገው እራሱ ህወሃት ነው ያሉት ሚኒስትሩ በዚህ ሁኔታ ህወሃቶች " ሬሳ እንኳን መንሳት አልቻሉም፤ በጣም ብዙ ሰው ወድሞባቸዋል "ሲሉ ተናግረዋል።

በህወሃትና በኤርትራ መካከል ያለው መካረርና አልፎ አልፎ እየተደረገ ያለው ውጊያ ፤ ኢትዮጵያ እና ኤርትራን ወደጦርነት ሊያስገባ አይችልም ወይ በሚል ለቀረበላቸው ጥያቄ " ወደዚያ የሚያመራ ሁኔታ የለም " ሲሉ ተናግረዋል

ህወሃት ትንኮሰውን የሚፈፅመው ሁለቱን ሀገራት ወደ ግጭት ለማስገባት እንደሆነ የገለጹት ዶ/ር ለገሰ " ይህ መቼም ቢሆን አይሳከም " ብለዋል፡፡

መንግስት በአካባቢው ያለውን ሁኔታ በተመለከተ መረጃ እንዳለው ገልፀው፡ ህወሃት ኤርትራ እና ኢትዮጵያን ለማጋጨት እየሰራ ቢሆንም ሁለቱ ሀገራት መቸም ቢሆን ወደ ግጭት አይገቡም ሲሉ ለአልዓይን ተናግረዋል።

ትላንት ህወሓት ባሰራጨው መረጃ ባለፈው ቅዳሜ እና እሑድ የኤርትራ ሠራዊት በሽራሮ ጥቃት ከፍቶ እንደነበር እንዲሁም ከ4 ቀን በፊት በአዲአዋላ ውጊያ መደረጉን አሳውቆ ነበር።

በውጊያው አንድ የኤርትራ ጦር ብርጌድ አዛዥ እና 3 የሻለቃ አዛዦች የሚገኙባቸው 120 ወታደሮች እንደተገደሉ 195 ያህሉን እንዳቆሰሉ እና 4 ወታደሮች እንደተማረኩ ገልጿል። 1 ድሽቃ፣ 5 የወታደራዊ ሬዲዮ መገናኛዎች እና በርካታ የጦር መሳሪያዎች ከኤርትራ ጦር እንደተማረከም መገለፁ አይዘነጋም።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" የዝንጀሮ ፈንጣጣ / መንኪፖክስ / ዓለም አቀፍ ወረርሽኝ ደረጃ ይደርሳል ብለን አንጠብቅም " - የዓለም የጤና ድርጅት እስካሁን በመቶዎች የተቆጠሩ ሰዎች መያዙ የታወቀው መንኪፖክስ ወይም የዝንጀሮ ፈንጣጣ ዓለም አቀፍ ወረርሽኝ ደረጃ ይደርሳል ብለው እንደማይጠብቁ የዓለም የጤና ድርጅት ከፍተኛዋ የበሽታው ኤክስፐርት ተናገሩ። ያን ይበሉ እንጂ በሽታው እንዴት እንደሚስፋፋ ሆነ ከአያሌ አሰርት በፊት…
#Mokeypox

በናይጄሪያ አንድ የ40 ዓመት ጎልማሳ በዝንጀሮ ፈንጣጣ / Monkeypox መሞቱን የሀገሪቱ የበሽታ መቆጣጠሪያ ማዕከል (NCDC) ትላንት ምሽት አስታውቋል።

ይህ ሞት በዚህ ዓመት በሀገሪቱ ከተመዘገበው አጠቃላይ 21 ኬዝ (ቫይረሱ ከተገኘባቸው 21 ሰዎች) መካከል ነው።

በናይጄሪያ ከሚገኙት 36 ግዛቶች ዘጠኙ የዝንጀሮ ፈንጣጣ (MonkeyPox) ተመዝግቦባቸዋል።

በሌላ በኩል በኮንጎ በ2022 9 ሰዎች በበሽታው መሞታቸው ሪፖርት መደረጉን ዋሽንግተን ፖስት አስነብቧል።

ከግንቦት መጀመሪያ ጀምሮ ከ200 በላይ የተጠረጠሩ ኬዞች እና በቫይረሱ መያዛቸው የተረጋገጠ ሰዎች በአብዛኛው በአውሮፓ ውስጥ ተገኝተዋል።

የዓለም ጤና ድርጅት (WHO) እስካሁን በመቶዎች የተቆጠሩ ሰዎች መያዙ የታወቀው የዝንጀሮ ፈንጣጣ (Monkeypox) ዓለም አቀፍ ወረርሽኝ ደረጃ ይደርሳል ብሎ እንደማይጠብቅ ትላንት መግለፁ ይታወሳል።

ምንም እንኳን ድርጅቱ ይህን ይበል እንጂ በሽታው እንዴት እንደሚስፋፋ ሆነ ከበርካታ ዓመታት በፊት የፈንጣጣ መከላከያ ክትባት ዘመቻ መቋረጡ ያስከተለው አንድምታ ይኖር እንደሆን ጨምሮ ብዙ የማይታወቁ ነገሮች መኖራቸውን ገልጿል።

ድርጅቱ የዝንጀሮ ፈንጣጣ (Monkeypox) በግብረ ስጋ ግንኙነት ወይም በአየር በትንፋሽ ይተላለፍ እንደሆን በተጨማሪ የህመም ምልክት የሌላቸው ሰዎች በሽታውን ያስተላልፋሉ ወይ የሚሉትን ጨምሮ በርካታ ጥያቄዎችን ይዞ እየመረመረ ነው።

@tikvahethiopia
#Update #ችሎት

በአዲስ አበባ የኢድ አልፈጥር በዓል ላይ በፈነዳው የአስለቃሽ ጭስ ቦንብ ጋር በተያያዘ በቁጥጥር ስር የሚገኘው ኮንስታብል አንቡላ ኡቴ ፍርድ ቤት ቀርቧል።

የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ወንጀል የመከላከል አድማ ብተና አባል የሆነው ኮንስታብል አንቡላ ኡቴ ሶስተኛ ጊዜ በፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ 2ኛ የጊዜ ቀጠሮ ችሎት ቀረቦ ጉዳዩ ታይቷል።

መርማሪ ፖሊስ ከዚህ በፊት ከግንቦት 10 ቀን ጀምሮ በተሰጠው የ13 ቀን የምርመራ ጊዜ ውስጥ የሰራውን የምርመራ ስራ ሪፖርት ለፍርድ ቤቱ አቅርቧል።

በዚህም ፦

➡️ የተጠርጣሪው ቃል የመቀበል ስራ መሰራቱን

➡️ ለተጠርጣሪው የገንዘብ ድጋፍ መኖርና አለመኖሩን ለማጣራት ለ18 ባንኮች ደብዳቤ መላኩን

➡️ የግል ስልኩ ላይ ለኤሌክትሮኒክስ ምርመራ እንዲደረግ ለብሔራዊ መረጃ ደህንነት ተቋም ደብዳቤ ተልኮ ውጤት እየተጠበቀ መሆኑ

➡️ የስልክ ቁጥር በማን ስም እንደወጣ ለማጣራት በኢትዮ ቴሌኮም በኩል እንዲጣራ መጠየቁን

➡️ የፈነዳውን አስለቃሽ ጭስ ቦንብ ፍንጣሪ በፎረንሲክ ምርመራ እንዲደረግ መላኩንና የምስክር ቃል መቀበሉን ለችሎቱ አስረድቷል።

በፍ/ቤቱ ዳኛ በኩል የስንት ምስክር ቃል እንደተቀበለ ለመርማሪ ፖሊስ ለቀረበ ጥያቄ የአንድ ሰው ምስክር ቃል ተቀብለናል የ3 ምስክር ቃል ይቀረናል በማለት ምላሽ ሰጥቷል።

ምስክሮቹ የፌደራል ፖሊስ አባላት ከሆኑ አስካሁን ለምን አልተቀበላችሁም ? ለሚለው ጥያቄ ደግሞ አንደኛው ምስክር ለስራ ሌላ ቦታ በመሄዳቸውና ሌሎቹም ስራ ላይ በመሆናቸው ምክንያት መቀበል አለመቻሉን መርማሪ መልስ ሰቷል።

ተጠርጣሪው ኮንስታብል አንቡላ በበኩሉ ከሻንጣዬ ጀምሮ ብርበራ ተደርጎል ነገር ግን ምንም ማስረጃ አላገኙብኝም እኔ ምንም ወንጀል አልሰራሁም ከታሰርኩበት ጊዜ ጀምሮ ውሃ እንኳን የሚሰጠኝ ጠያቂ የለኝም አንድ ሳምንት በር ተዘግቶብኝ ታስሬ ነበር ሲል ለችሎቱ ገልጿል።

በአሁን ወቅት ያለበት የስር ሁኔታ ምን ደረጃ ላይ እንዳለ በችሎቱ ዳኛ የተጠየቀው ኮንስታብል አንቡላ አሁን አ/አ ፖሊስ ከሌሎች እስረኞች ጋር እንዲሆን መደረጉን መልስ ሰቷል።

ፍርድ ቤቱ የፖሊስ የምርመራ መዝገብ አስቀርቦ የተመለከተ ሲሆን ፖሊስ በተሰጠው ጊዜ ማስረጃ ማሰባሰቡን እንዲሁም የ3 ሰዎች ምስክር ቃል መቀበልና ቀሪ ማስረጃ መሰብሰብ እንደሚቀረው ማረጋገጡን ፍርድ ቤቱ ገልጿል።

በዚህ መልኩ የጀመረውን ምርመራውን ፖሊስ አጠናቆ እንዲቀርብ ፍርድ ቤቱ የ10 ቀን ተጨማሪ ጊዜ ፈቅዷል። የምርመራ ውጤቱን ለመጠባበቅ ለሰኔ 3 ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰጥቷል።

ምንጭ፦ ጋዜጠኛ ታሪክ አዱኛ

@tikvahethiopia
#እናት #መኢአድ #ኢሕአፓ

ሶስት የፖለቲካ ፓርቲዎች በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ዛሬ መግለጫ አውጥተዋል።

በወቅታዊ ጉዳይ መግለጫ ያወጡት እናት ፓርቲ ፣ መኢአድ እና ኢሕአፓ ሲሆኑ ፓርቲዎቹ " ሀገር በህግ እና በስርዓት እንጂ በአፈና አትመራም " ሲሉ ነው ወግለጫ ያወጡት።

ፓርቲዎቹ በመግለጫቸው የኑሮ ውድነት፣ በአዲስ አበባ እየተሰራ ነው ስላሉት ደባ ፣ የመሬት ማዳበሪያ ጉዳይ፣ የሰሜኑ ኢትዮጵያ ክፍል ጉዳይ፣ የፋኖን ጉዳይ፣ መንግስት እየወሰድኩ ነው ስላለው የህግ ማስከበር እርምጃ እና ሌሎች ጉዳዮችን በስፋት አንስተዋል።

ፓርቲዎቹ በሕግ ማስከበር ላይ የማያወላዳ አቋም እንዳላቸው የገለፁ ሲሆን በአፈናና በግድያ ሕግ ማስከበር እንደማይቻል አጠንክረን እናሳስባለን ብለዋል።

" ማፈን መግደልና የማኅበረሰብን ቅስም የመስበር አካሄድ በአፋጣኝ እንዲቆም " ሲሉ ጠይቀዋል።

አክለውም ፤ በሕግ ማስከበር ሰበብ የታፈኑ ንጹሓን፣ ጋዜጠኞች፣ ማኅበረሰብ አንቂዎች፣ የፋኖ አባላትና ቤተሰቦቻቸው፣ ምሑራን፣ የጸጥታ ተቋማት ተመላሾችና አባላት፣ የፓርቲ አመራርና አባላት እንዲለቀቁ ጠይቀዋል።

መንግስት ጠረጥሬያቸዋለሁ ብሎ ካሰበም ተገቢውን የሕግ ሂደት በመከተል ለፍርድ ቤት ከማቅረብ ጀምሮ መሰል ሰብዓዊ መብቶቻቸው እንዲከበሩ ጥሪ አቅርቧል።

ሶስቱ ፓርቲዎች " ፋኖ " በጭንቅ ጊዜ ሀገር " ድረስልኝ " ብላ የጠራችው ባለውለታ እንጂ ለሹመትና ለሽልማት የመጣ ባለመሆኑ መንግስት አጉል ሥጋቱን አስወግዶ የያዘውን አካሄድ ይፈትሽ ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።

በሌላ በኩል መንግስት ያለው የኑሮ ውድነትና የዋጋ ግሽበት ሚሊዮኖችን ለጎዳና እና ለከፋ ረሃብ ከመዳረጉ በፊት በኢኮኖሚው ውስጥ ጣልቃ ገብቶ ያለውን የገበያ ምስቅልቅል እንዲያርምና እንዲያረጋጋ ጠይቀዋል።

(ሙሉ መግለጫቸው ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia