TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ተጨማሪ ማዕቀብ እንዲጣል አዘዙ። የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን ከትግራይ ክልል ቀውስ ጋር በተገናኘ ተጠያቂ ባደረጓቸው ፦ - የኢትዮጵያ ፌዴራል መንግስት - የአማራ ክልል ባለስልጣናት - የህወሓት አመራሮች - የኤርትራ መንግስት አመራሮች ላይ ተጨማሪ ማዕቀብ እንዲጣል አዘዙ። ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን ዛሬ በፈረሙት የስራ አስፈጻሚ አካል ትዕዛዝ (executive order) የትግራይ…
#DrAbiyAhmed #JoBiden

የኢትዮጵያ ጠ/ሚ ዶክተር ዐቢይ አህመድ ለአሜሪካው ፕሬዜዳንት ጆ ባይደን ግልፅ ደብዳቤ ✉️ ፃፉ።

ዶክተር ዐቢይ አህመድ ለአሜሪካው ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን በፃፉላቸው ግልፅ ደብዳቤ በአሁን ሰዓት በኢትዮጵያ 🇪🇹 ስላለው ወቅታዊ ሁኔታ ማብራሪያ ሰጥተዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ ፥ ሕወሓት በአፋርና አማራ ያፈናቀላቸው ንፁሃን ዜጎች በከፋ ችግር ውስጥ ወድቀው እንደሚገኙ የገለፁ ሲሆን ቡድኑ ቤተሰቦቻቸውን እንደገደለባቸው እንዲሁም የአገልግሎት መስጫ ተቋማትን ጨምሮ ንብረት እንዳወደመ አስረድተዋል።

በኢትዮጵያ ላይ እየደረሱ ያሉ የውጭ ጫናዎች ተገቢ አለመሆናቸውንም አሳውቀዋል።

ዶ/ር ዐቢይ ፥ በቅርቡ የተመሰረተው አዲሱ የባይደን አስተዳደር ከዚህ ቀደም ከነበረው የተሻለ እንደሚሆን ኢትጵያውያን ተስፋ እንደነበራቸው አውስተዋል።

አሜሪካ ሌሎች ሃገራት ላይ በነበራት የተሳሳተ የውጭ ፖሊሲ በሃገራቱ ላይ ያስከተለውን ቀውስ አስታውሰዋል፡፡

ኢትዮጵያ 🇪🇹 ተስፋ በቆረጡ እና ስልጣን ከሚሊዮኖች ደህንነት በላይ በሚያሳስባቸው ግለሰቦች አትሸነፍም ሲሉም ገልጸዋል፡፡ #ኢትዮጵያዊ እንዲሁም #አፍሪካዊ ማንነታችን እንዚህ ግለሰቦች እንዲያሸንፉ አይፈቅድልንም ብለዋል፡፡

@tikvahethiopia