TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ኢሉአባቦር ዞን‼️

በኢሉአባቦር ዞን ቡሬ ወረዳ በህገወጥ መንገድ ሲዘዋወር የነበረ 43 #ክላሽንኮቭ ጠመንጃና 44 የጥይት ካዝና መያዙን ፖሊስ አስታወቀ፡፡

የወረዳው ፖሊስ አዛዥ ኮማንደር ታረቀኝ አሰፋ ለኢዜአ እንደገለፁት ህገ ወጥ የጦር መሳሪያዎቹ የተያዙት ከትላንት በስቲያ ሲሆን ከጋምቤላ ክልል በኮድ 3 -92943 ኢትዮጵያ ሲኖትራክ ተሽከርካሪ በአንድ ግለሰብ አማካኝነት ወደ መሀል ሀገር በመጓጓዝ ላይ እያለ በህብረተሰቡ ተሳትፎ በቡሬ ወረዳ ሲቦ ቀበሌ በተደረገው #ፍተሻ ነው።

ምንጭ፦ኢዜአ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update በህገ ወጥ መንገድ ሲዘዋወር የነበረ 105 #ክላሽንኮቭ የጦር መሳሪያ #በቁጥጥር ስር ዋለ፡፡ ህገወጥ የጦር መሳሪያው በቁጥጥር ስር የዋለው ትናንት ለሊት #በቡራዩ_ከተማ ነው፡፡ የጦር መሳሪያው በአይሱዙ ተሽከርካሪ ውስጥ ተጭኖ #ከጋምቤላ ወደ #አማራ_ክልል ሊጓጓዙ የነበረ ነው ተብሏል፡፡ የተያዘው የጦር መሳሪያ 42 ታጣፊና 63 ባለሰደፍ በድምሩ 105 ክላሽንኮቮች፣ 95 #የክላሽንኮቭ_መጋዝኖች እና 5 ጥይት ነው፡፡ ከአይሱዙ ኤፍ.ኤስ.አር የጭነት #ተሽከርካሪው ፊት በመሄድ ሁኔታዎችን #ሲያመቻች የነበረ አንድ ዶልፊን ሚኒባስም ተይዟል፡፡

Via FBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia