TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ኢሰመኮ

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ፦

#አማራክልል

በአዊ ብሔረሰብ ዞን አስተዳደር በአየሁ ጓጉሳ ወረዳ አምበላ ቀበሌ በዚገም ወረዳ ሶሪት ቀበሌ ከጥቅምት 29 ቀን 2016 ዓ.ም. ጀምሮ በተለያዩ ቀናት በተፈጠረው ብሔር ተኮር ግጭት ሞት እና የአካል ጉዳት እንዲሁም በኢንቨስትመንት ቦታዎች ላይ ጉዳት ደርሷል።

በምዕራብ ጎጃም ዞን፣ ቡሬ ዙሪያ ወረዳ፣ ፈጣም ሰንቶም እና በቆጣቦ ቀበሌዎች ጥቅምት 30 ቀን 2016 ዓ.ም. እና በኅዳር 1 ቀን 2016 ዓ.ም. " ኢመደበኛ " የአማራ ታጣቂዎች መሆናቸው የተገለጸ ቡድኖች በሰነዘሩት ብሔር ተኮር ጥቃት እና ይህንኑ ተከትሎ በተፈጠረው ግጭት በርካታ ሰዎች ላይ የሞት፣ የአካልና የንብረት ጉዳት ደርሷል።

በተፈጠረው ግጭት ምክንያት ነዋሪዎች ተፈናቅለው በቡሬ ዙሪያ ወረዳ በሚገኙ አጎራባች ቀበሌዎች እና ወደ ኦሮሚያ ክልል ለመሄድ ተገደዋል። የቀንድ ከብቶች ተዘርፈዋል።

#ቤኒሻንጉልጉሙዝ

አሶሳ ዞን፣ ኦዳ ብልድግሉ ወረዳ ሥር በሚገኙ ቤልሚሊ፣ አልከሻፊ እና ቤላደሩ ቀበሌዎች በሚኖሩ የቤኒሻንጉል ብሔር ተወላጆች እና አብረው በሚኖሩት የኦሮሞ ብሔር ተወላጆች ላይ ኅዳር 19 ቀን 2016 ዓ.ም ከንጋቱ 11፡00 ሰዓት ጀምሮ እስከ ቀኑ 5፡00 ሰዓት አካባቢ በኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት (በተለምዶ ኦነግ-ሸኔ) ታጣቂ ቡድን አባላት በተፈጸመ ጥቃት በሰው ሕይወትና በንብረት ላይ ጉዳት ደርሷል፡፡

በጥቃቱ 17 ሰዎች መገደላቸው ፣ አንድ ሽማግሌ ታፍነው መወሰዳቸው፣ በ7 ሰዎች ላይ ደግሞ ከባድ የአካል ጉዳት የደረሰ መሆኑን ማወቅ ተችሏል።

በሦስቱ ቀበሌዎች ያሉ መንደሮች በአብዛኛው የተቃጠሉና የወደሙ መሆኑን፣ የእርሻ ሰብልና የቤት እንስሳትን ጨምሮ የንብረት ውድመት ደርሷል።

የቀበሌዎቹ ነዋሪዎች ጥቃቱን በመሸሽ ወደ አጎራባች ቀበሌዎችና በአቅራቢያው ወደ ሚገኘው መነሲቡ ወረዳ (ኦሮሚያ ክልል) ተፈናቅለዋል።

#ኦሮሚያክልል

- በአርሲ ዞን፣ ሸርካ ወረዳ ኅዳር 13 ቀን 2016 ዓ.ም. በጢጆ ለቡ ቀበሌ በግምት ከምሽቱ 1፡00 ሰዓት በኋላ ማንነታቸው በውል ያልተለየ ታጣቂዎች በፈጸሙት ብሔር/ማንነት ተኮር ጥቃት 7 የአንድ ቤተሰብ አባላት እና 3 ጎረቤቶቻቸው ጨምሮ በአጠቃላይ 10 ሰዎችን ገድለዋል።

በዚያው ዕለት ታጣቂዎቹ በሶሌ ዲገሉ ቀበሌ ቢያንስ 12 ሲቪል ሰዎችን ገድለዋል።

በሶሌ ዲገሉ ቀበሌ ከተገደሉ 12 ሰዎች መካከል አሥራ አንዱ የአንድ ቤተሰብ አባላት ናቸው።

በኅዳር 17 ቀን 2016 ዓ.ም. በወረዳው በኮኘ ቀበሌ ታጣቂዎቹ በፈጸሙት ጥቃት የአንድ ቤተሰብ አባላት የነበሩ 8 ሰዎችን ገድለዋል።

ጥቃት አድራሾች ሟቾችን ከቤት እያስወጡ #አሰልፈው_እንደገደሏቸው፣ የተወሰኑትም በቤታቸው ውስጥ እንደተገደሉ ለማወቅ ተችሏል።

ከሟቾች መካከል #ጨቅላ_ሕፃንን ጨምሮ ነፍሰጡር ሴቶች እና ከ80 ዓመት በላይ የሆናቸው አረጋዊ ይገኙበታል፡፡

ከተገደሉት ሰዎች በተጨማሪ ቁጥራቸው በውል ያልታወቀ ሰዎች ጉዳት ደርሶባቸው በሕክምና ላይ ይገኛሉ፡፡

የአካባቢው ነዋሪዎች አሁንም ተደጋጋሚ ዛቻ እየደረሳቸው መሆኑን ለኮሚሽኑ ገልጸው፤ መንግሥት በአስቸኳይ እንዲደርስላቸው ተማጽነዋል፡፡

በቄለም ወለጋ ዞን፣ ጊዳሚ ወረዳ፣ የመካነ ኢየሱስ ቤተ-ክርስቲያን አባላት የነበሩት 9 ምዕመናን፣ ሽማግሌዎች፣ የወጣቶች ኮሚቴ አባላት እንዲሁም ሌሎች አገልጋዮችን ኅዳር 14 ቀን 2016 ዓ.ም. ከሌሊት 8፡00 ሰዓት አካባቢ እስካሁን ማንነታቸው ባልተለዩ በታጠቁ ቡድኖች ተገድለዋል።

ግድያው የተፈፀመድ መላኮ መናሞ ቀበሌ ባለው ጫካ ውስጥ ሲሆን ገዳዮችን  አስክሬናቸውን መጣላቸው ለማረጋገጥ ተችሏል።

(የኢሰመኮ መግለጫ ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia
#አማራክልል

በደብረ ብርሃን በፋኖ እና በመከላከያ መካከል ተደረገ በተባለ የተኩስ ልውውጥ ንጹሐን ሰዎች መገደላቸውን ነዋሪዎችና የከተማው ከንቲባ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለጹ።

በአማራ ክልል ደብረ ብርሃን ከተማ ሰሞኑን በፋኖ ከታጣቂዎችና በመከላከያ ሠራዊት ተደረገ በተባለ የተኩስ ልውውጥ፣ “በርካታ ንጹሐን ተገድለዋል። ባለሥልጣናትም ታግተው ተወስደዋል” ሲሉ አንድ የከተማው ነዋሪ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

ሌላኛው ስማቸው እንዳይጠቀስ የጠየቁ ነዋሪ፣ “እኔ ባለኝ መረጃ 5 ንጹሐን ተገድለዋል” ብለው፣ ከንጹሐን ሰዎች በተጨማሪ የብልጽግና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ የአቶ ሰለሞን ጌታቸው ሹፌርም እንደተገደሉ፣ የፋኖ ታጣቂዎች ኃላፊውን ጨምሮ በርካታ ሠራተኞችን አግተው እንደወሰዱ አስረድተዋል።

የደብረ ብርሃን ከተማ ከንቲባ አቶ በድሉ ውብሸት ምን ያህል ሰዎች እንደተገደሉ ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ለቀረባለቸው ጥያቄ በሰጡት ማብራሪያ፣ የተወሰኑ ሰዎች ላይ ጉዳት እንደደረሰ፣ የሟቾችን ብዛት እያጣሩ መሆኑን፣ እስካሁን (ይህ ዘገባ እስከተጠናቀረበት ጊዜ) ድረስ ከአራት ሰዎች በላይ መገደላቸውን ተናግረዋል።

አክለውም፣ የብልጽግና ጽሕፈት ኃላፊው ሹፌር ተገድሏል መባሉ እውነት መሆኑን፣ ይሁን እንጂ ኃላፊውና ሌሎች ሠራተኞች ታግተው #እንዳልተወሰዱ አስረድተው፣ የጸጥታውን ሁኔታ በተመለከተም፣ “ወደ መደበኛ ሥራው ተመልሷል። መደበኛ እንቅስቃሴ ላይ ነው” ብለዋል።

ከደብርሃን ከተማ በተጨማሪ በሰሜን ወሎ የተለያዩ አካባቢዎች፣ በጎንደርና በጎጃም መስመሮች በተለያዩ አካባቢዎች በየወቅቱ የተኩስ ልውውጥ እንደሚደረግ ነዋሪዎች ይናገራሉ።

ሰሞንኛውን የደብረ ብርሃን የጸጥታ መደፍረስ ተከትሎ ወደ ሸዋ ሮቢት፣ ደሴ፣ ወልዲያና ሌሎች አካባቢዎች መጓዝ አለመቻላቸውን፣ አሁንም ለገና በዓል ወደ ቤተሰብ ለመሄድ የመንገዱ ደህንነት ሥጋት እንደደቀነባቸው ተጓዦች ሲያማርሩ ተስተውለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከላም በረት መናኸሪያ ስምሪት ባደረገው ቅኝት ከአዲስ አበባ ወደ ደሴ መስመር ስምሪት እንደሌለ፣ ለዚሁ መስመር የጉዞ ትኬት የሚጠይቁ ሰዎችም የለም እየተባሉ መሆኑን ተመልክቷል።

በሌላ በኩል በሰሜን ወሎ ዞን ራያ ቆቦ ከተማ ወጣ ብሎ በስተምዕራብ በኩል ጠበለት ተራራ ተብሎ በሚጠራው ቦታ ሰሞኑን ከፍተኛ የተኩስ ልውውጥ እንደነበር፣ ከቆቦ ወደ ተኩለሽ ታዳጊ ከተማ በጸጥታው ችግር ምክንያት የትራንስፖርት አገልግሎት ከቆመ ዓመታት ማስቆጠሩን ነዋሪዎቹን አማሯል።

ከዚህም ባሻገር በክልሉ በተለይ ድርቅ በተከሰተባቸው ዋግኽምራ አስተዳደር ዞን፣ በሰሜን ጎንደር አካባቢዎች እርዳታ ለማድረስ የጸጥታው ችግር ፈተና እንደሆነ የአካባቢዎቹ ባለሥልጣናት በተደጋጋሚ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ መግለጻቸው፣ ነዋሪዎች በበኩላቸው የጸጥታው ችግር የኑሮ ውድነቱን እንዳባባሰው ተናግረዋል።

በፋኖ ታጣቂዎችና መከላከያ ሠራዊት መካከልበአማራ ክልል በተለያዩ አካባቢዎች በየወቅቱ የተኩስ ልውውጥ ሲደረግ ይስተዋላል።

ዘገባውን የላከው የአ/አ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ነው።

@tikvahethiopia