TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#udate ጅቡቲ⬆️

"ታሪካዊ የዲፕሎማሲ ድል!! ከረጅም አመት መለያየት ቡሀላ ኤርትራና ጅቡቲ ግንኙነታቸውን ለመቀጠል #ተስማምተዋል። ለመላው #የኤርትራ አና #የጅቡቲ ህዝብ እንኳን ደስ ያላችሁ!!"

©ዶክተር ወርቅነህ ገበየሁ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ኦነግ እና ODP‼️

የኦሮሞ ዴሞክራቲክ ፓርቲ (ODP) እና የኦነግ አመራሮች ዛሬ በጋራ በሰጡት መግለጫ በሁለቱ መካከል ያለውን ስምምነት በማጠናከርና ችግሮችን በመፍታት #አብረው ለመስራት #ተስማምተዋል፡፡

የODP ምክትል ሊቀመንበር አቶ #ለማ_መገርሳ ከዚህ በኋላ ከኦነግ ጋር በመደማመጥ ለአገር እድገት በጋራ እንደሚሰሩ ገልጸዋል፡፡

አቶ ለማ ከኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ) ጋር አብሮ ለመስራትና የኦነግ ሰራዊት የመንግስት አካል ሆኖ ተጨማሪ አቅም እንዲሆን በአስመራ ስምምነት መደረሱን ገልጸዋል፡፡

በዚህ ስምምነት መሰረት ኦነግ ወደ አገር ገብቶ ስራ መጀመሩን የገለጹት አቶ ለማ፣ አለመረጋጋት የተፈጠረው ስምምነቱ ፈርሶ ሳይሆን ካለመረዳዳት የመነጫ ነው ብለዋል፡፡

ከእንግዲህ ሰላምና መረጋጋት እንዲፈጠር ሁለቱ ፓርቲዎች መስማማታቸውን አቶ ለማ ተናግረው፣ የODP አባላትና የጸጥታ ኃይሎች ይህንን ስምምነት ተረድተው መንቀሳቀስ አለባቸው ብለዋል፡፡

ወደ ትናንትናው ላለመመለስ በጋራ ቃል ተገባብተው አብረው ለመስራት እንደተስማሙም አቶ ለማ ተናግረዋል፡፡

የኦነግ ሊቀመንበር አቶ #ዳውድ_ኢብሳ በበኩላቸው፣ በአስመራ የተደረሰውን ስምምነት በመተግበር ከODP ጋር አብሮ ለመስራት መስማማታቸውን ገልጸዋል፡፡

አቶ ዳውድ ኢብሳ ከODP አብረው ለመስራት መስማማታቸውንና የኦነግ አባላትና ደጋፊዎች ለዚህ ስምምነት የበኩላቸውን አስተዋዕኦ እንዲያደርጉ ጠይቀዋል፡፡

ምንጭ:- OBN
@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETH ማጠቃለያ🗞ጥር 16/2011 ዓ.ም.

የሶማሌ ክልል መንግሥት ካቢኔ ባካሄደው ስብሰባ አንድ የካቢኔ አባልን ጨምሮ ስድስት ከፍተኛ አመራሮችን #ከኃላፊነታቸው አንስቷል።


በድሬዳዋ የጥምቀትን በዓል ተከትሎ በተከሰተው ግጭት የተጠረጠሩ 84 ግለሰቦች በቁጥጥር ሥር ማዋሉን የድሬዳዋ አስተዳደር ፖሊስ ኮሚሽን ገልጿል።


ድሬዳዋ ዛሬ በተቃውሞ ስትናጥ ውላለች። በተለያዩ የከተማዋ አካባቢዎች የጥይት ተኩስ ድምጽ ሲሰማ ውሏል። እስካሁን ድረስ በሰዎች ላይ ስለደረሰው ጉዳት በግልፅ የታወቀ ነገር ባይኖርም የቆሰሉ ሰዎች መኖራቸው ተሰምቷል።


አባይ ኢንዱስትሪያል የልማት ማህበር በአማራ ክልል ደጀን ከተማ በ8.8 ቢሊዮን ብር ሲሚንቶ ፋብሪካ ለመገንባት ከቻይናው HY እና ከዴንማርኩ FLS ኩባንያዎች ጋር ሥምምነት ተፈራርሟል፡፡


የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥትና ኦነግ ዛሬ እንደገና አምቦ ላይ #ዕርቅ ፈጽመዋል፡፡


ሰሞኑን በአፋርና ሶማሌ ክልሎች አዋሳኝ አካባቢዎች ተፈጥሮ የነበረውን #ግጭት ለመፍታት የሁለቱ ክልሎች የሃይማኖት መሪዎችና የሀገር ሽማግሌዎች #ተስማምተዋል


የፋሲል ከነማ ደጋፊዎች አሳፍሮ ከባህርዳር ወደ ጎንደር በማምራት ላይ ያለ አውቶብስ #ተገልብጦ በሰው ህይወት እና አካል ላይ ጉዳት መድረሱ ተነግሯል። ሁለት ሰዎች ሞተዋል ቁጥራቸው ያልታወቀ ሰዎች የአካል ጉዳት ደርሶባቸዋል።


ዛሬ ዱራሜ ላይ በከፋ ዞን ለሞቱ የከንባታ ተወላጆች የሃዘን መግለጫ እና ሻማ የማብራት ፕሮግራም ተካሂዷል።


የትግራይ ክልላዊ መንግሥት ምክር ቤት መደበኛ ጉባዔውን ዛሬ ጀምሯል፡፡


የጉምርክ አሰራርን #ሳያሟላ ወደ መቀለ ሊገባ የነበረ ከ10 ሚሊዮን ብር በላይ ግምት ያለው የምግብ ዘይት በቁጥጥር ሥር መዋሉ ተገልጿል።


ኮሎኔል #አለበል_አማረ በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት በምክትል ቢሮ ኃላፊ ደረጃ የሰላምና የህዝብ ደህንነት ጉዳዮች ቢሮ የህዝብ ደህንነት ዘርፍ ኃላፊ ሆነው ተሹመዋል።

ምንጭ፦ አብመድ፣ ኢ.ፕ.ድ፣ ኢ.ዜ.አ.፣ fbc፣ የጀርመን ራድዮ፣ ዋዜማ ራድዮ፣ የTIKVAH-ETH ቤተሰብ አባላት


አመሰግናለሁ! ሰላም እደሩ!!
ሀገራችንም ቸር ትደርልን!!
ጥር 16/2011 ዓ.ም.
@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" ከእኔ ጋር ቁጭ ብለህ ተነጋገር " - ቮልድሚር ዜኔንስኪ የዩክሬኑ ፕሬዝደንት ቮሎድሚር ዜሌንስኪ ከሩሲያው አቻቸው ቭላድሚር ፑቲን ጋር በቀጥታ ለመነጋገር ጠያቄ አቀረቡ። ዜሌንስኪ ይህን ጥያቄ ያቀረቡት ዛሬ አመሻሽ ላይ በሰጡት መግለጫ ነው። ፕሬዜዳንቱ ፤ " ጦርነቱን ለማቆም #ብቸኛው አማራጭ ከፑቲን ጋር በቀጥታ መነጋገር ነው " ብለዋል። ዜሌንስኪ ለፑቲን ባስተላለፉት መልዕክት ፥ " ሩሲያን…
#ተስማምተዋል

ዛሬ ሀሙስ በቤላሩስ በተካሄደው 2ኛ ዙር ውይይት ሩስያ እና ዩክሬን ሰላማዊ ዜጎች ከዩክሬን የውጊያ ቀጠና የሚወጡበትን መንገዶች ለማመቻቸት ተስማምተዋል

የዩክሬን ፕሬዝዳንት ረዳት የሆኑት ሚካሂል ፖዶሊያክ " 2ቱም ወገኖች በጊዜያዊ የተኩስ አቁም የሰብአዊነት ኮሪደሮችን በጋራ ማቋቋም ላይ መግባባት ላይ ደርሰዋል። እነዚህንም ኮሪደሮችን ለማደራጀት ሩሲያ እና ዩክሬን በቅርቡ የግንኙነት እና የትብብር መንገዶችን ይፈጥራሉ " ሲሉ ተናግረዋል።

የሩሲያው ልዑካን ቡድን መሪ ቭላድሚር ሜዲንስኪ ያለውን ሂደት አረጋግጠዋል። ሁለቱ ወገኖች የሲቪሎችን ህይወት ለማዳን " ዋናውን ጉዳይ " እንደፈቱ ተናግረዋል።

ተደራዳሪዎቹ በወታደራዊ እና በሰብአዊ ጉዳዮች እንዲሁም ወደፊት በሚደረጉ የፖለቲካ ዕርቅ ጉዳዮች ላይ የጋራ አቋም መያዛቸውንም ቭላድሚር ሜዲንስኪ ገልፀዋል።

የዩክሬን ወገን ድርድሩ የሚጠብቁትን ውጤት እንዳላመጣ ገለፀው የሚቀጥለው ዙር ድርድር በቅርብ ጊዜ ይካሄዳል ተብሎ እንደሚጠበቅ ማሳወቃቸውን አር ቲ ኒውስ ዘግቧል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update

በሰላም ስምምነቱ መሠረት የህወሓት ታጣቂዎች ትጥቅ የሚፈቱበት ዝርዝር ዕቅድ ላይ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት አዛዥና የሕወሐት ታጣቂዎች አዛዥ በናይሮቢ መክረዋል።

በሰላም ስምምነቱ በተያዘው የጊዜ ገደብ ትጥቅ የሚፈታበትንና መከላከያ ወደ መቐለ የሚገባበትን ዕቅድ ላይም #ተስማምተዋል። ዕቅዱም በቀጣይ ተግባራዊ ይደረጋል።

ለዕቅዱ ተግባራዊነት የሚመለከታቸው አካላት ሁሉ በስምምነቱ መሠረት የሚጠበቅባቸውን ሊወጡ እንደሚገባ የኢትዮጵያ መንግሥት ማሳሰቡን የመንግስት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት ከናይሮቢው ስምምነት በኃላ ባወጣው መግለጫ አሳውቋል።

@tikvahethiopia