TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#SafaricomEthiopia

ሳፋሪኮም - ኢትዮጵያ በሚያዝያ ወር መጀመሪያ ላይ ሥራ እንደሚጀመር አሳውቋል።

የድርጅቱ የቁጥጥር እና የውጭ ጉዳይ ኃላፊ ማቲው ሃሪሰን ሃርቬይ ከመንግስት ጋር ያላቸው ስምምነት እንደሚያሳየው ፍቃድ ከተሰጠበት ቀን ጀምሮ በዘጠኝ ወር ወደ ስራ መግባት እንደሚኖርባቸው ገልፀው ከመጪው ሚያዝያ ወር ጀምሮ በይፋ የንግድ ሥራ ለመጀመር እየሰሩ መሆኑን ገልፀዋል።

ኃላፊው ይህን የገለፁት ለካፒታል ጋዜጣ ነው።

እ.ኤ.አ. ከሐምሌ 9፣ 2021 ጀምሮ የሚቆጠር የመሥሪያ ፍቃድ ያገኘው ሳፋሪኮም ቴሌኮሙኒኬሽን ኢትዮጵያ በሀገሪቱ የቴሌኮም ማስፋፊያ ስራዎችን ጀምሯል።

ባለፈው ወር የኩባንያው የመጀመሪያ የመረጃ ማዕከል ስራ የጀመረ ሲሆን ኩባንያው የኔትወርክ ዝርጋታውን እየሰራ ነው።

ማቲው ሃሪሰን ሃርቬይ ሳፋሪኮም ከ2 የኔትወርክ አቅራቢዎች ኖኪያ እና ሂዋዌ ጋር እየሰራ መሆኑን የገለፁ ሲሆን በአዲስ አበባ እና አካባቢው ያለውን የኮር ኔትወርክ መሠረተ ልማት በኖኪያ ኩባንያ እንደሚሰራ ሁዋዌ ቀሪውን የአገሪቱን ክፍል እንደሚሸፍን አስረድተዋል።

" የመሰረተ ልማት መጋራት በተመለከተም ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር እስካሁን በድርድር ደረጃ ላይ ነን " ሲሉም አክለዋል።

ከመሰረተ ልማት ጎን ለጎን የሳፋሪኮም ደንበኞች እና የኢትዮ ቴሌኮም ደንበኞች እንዲገናኙ ለማድረግ ስራዎች እየተሠሩ መሆኑን ገልፀዋል።

#Capital_Newspaper

@tikvahethiopia