TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
" ጽኑ ሀገር " - በአቶ እስክንድር ነጋ

አቶ እስክንድር ነጋ የፃፉት መፅሀፍ ዛሬ ሰኞ ለገበያ ይቀርባል።

የባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ ፓርቲ ፕሬዝዳንት አቶ እስክንድር ነጋ በቂሊንጦ እስር ቤት ውስጥ ሆነው የፃፉት 'ጽኑ ሀገር' የተሰኘው አዲስ መፅሐፍ ዛሬ ገበያ ላይ እንደሚውል የመፅሐፉ አሳታሚ ሞረሽ መፅሐፍት መደብር አስታውቋል።

መፅሐፉ ጥልቅ ፖለቲካዊ ትንታኔዎችን የያዘ እና በ256 ገፆች የተቀነበበ ነው ተብሏል።

በአራት ክፍሎች የተከፋፈለው ይህ መፅሐፍ የሰሜኑን ጦርነት እንዲሁም ምርጫ 2013ን በስፋትና በጥልቀት እንደሚተነትን ነው የተገለፀው።

ከዚህ በተጨማሪም የ1997 ዓ.ም. እና የ2002 ዓ.ም. አገራዊ ምርጫዎች፣ የአረብ ፀደይ አብዮት በመባል የሚታወቀው ፖለቲካዊ ክስተት እና ሌሎች ተዛማጅ ፖለቲካዊ ጉዳዮች በመፅሐፉ መተንተናቸው ተነግሯል።

አቶ እስክንድር ነጋ ከዚህ ቀደም ድል ለዴሞክራሲ ፣ ምርጫ 97 የተባሉ መፅሐፍትን ለንባብ አብቅተው ነበር።

የመረጃ ምንጭ፦ የባልደራስ ፓርቲ የሚዲያ ክፍል ነው።

@tikvahethiopia
#BREAKING

የአፍሪካ ህብረት ቡርኪናፋሶን አገደ።

በቡርኪና ፋሶ ከተደረገው መፈንቅለ መንግሥት ጋር በተያያዘ የአፍሪካ ህብረት ሀገሪቱን ከማንኛውም የህብረቱ እንቅስቃሴ ማገዱን ዛሬ አሳውቋል።

እግዱ ህገ መንግስታዊ ስርዓቱ ወደነበረበት እስኪመለስ ይቀጥላል ተብሏል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Tigray , #Mekelle 📍

የዓለም አቀፍ ቀይ መስቀል ኮሚቴ በመቐለ ከተማ ለሚገኙ ሆስፒታሎች ወሳኝ የሆኑ የህክምና ቁሳቁሶችን ማከፋፈል መጀመሩን ትላንት አሳውቋል።

ድርጅቱ ባለፈው ሳምንት የመጀመሪያዎቹን አምስት በረራዎች ማጠናቀቁን ገልፆ በነበሩት በረራዎች ኢንሱሊንን ጨምሮ እጅግ አስቸኳይና አስፈላጊ መድሃኒቶችን ማጓጓዙን ገልጿል።

ይኸው ተግባር በዚህ ሳምንትም እንደሚቀጥል አሳውቋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#UAE

ጠ/ሚ መሀመድ ሁሴን ሮብሌ ዩኤኢ ይገኛሉ።

የሶማሊያ ጠ/ሚር መሀመድ ሁሴን ሮበል በተባበሩት አረብ ኤሜሬትስ የስራ ጉብኝት ላይ እንደሚገኙ አል ዓይን ኒውስ ዘግቧል።

ጠ/ሚ ሮብሌ በትናንትናው ዕለት ወደ አቡዳቢ ያቀኑ ሲሆን ከአገሪቱ አመራሮች ጋር በመወያየት ላይ መሆናቸውን ዘገባው ይገልፃል።

ባለፉት ቀናት የተባበሩት አረብ ኤሜሬትስ የግብፅ ፕሬዜዳንት አብዱል ፈታህ አልሲሲ ፣ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድን እንዲሁም ትላንት የእስራኤል ፕሬዜዳንት አይዛክ ሄርዞግን ተቀብላ አስተናግዳለች።

ከየሀገራቱ መሪዎች ጋርም በተለያዩ ጉዳዮች መክራለች።

ፎቶ : #SomaliPM

@tikvahethiopia
የኢትዮ ቴሌኮም ሪፖርት ፦

የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አፈፃሚ ወ/ሪት ፍሬህይወት ታምሩ የኩባንያውን የ6 ወራት የስራ አፈፃፀም ዛሬ ሪፖርት አድርገዋል።

በዚህ መሰረት ኢትዮ ቴሌኮም ፦

• በ6 ወር አመርቂ ትርፍ እንዳገኘ ተገልጿል።

• በ6 ወር 28 ቢሊዮን ብር አጠቃላይ ገቢ አግኝቷል። ይህም ከእቅዱ 86.4 በመቶ አሳክቷል፤ ከባለፈው ዓመት ጋር ሲነፃፀር የ6.7 በመቶ እድገት አሳይቷል።

• በውጭ ምንዛሬ ከሚያስገኙ አገልግሎቶች 74.8 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ገቢ አግኝቷል፤ የእቅዱ 89.3 በመቶ አሳክቷል።

• ጦርነት ፣ በግጭት፣ ምክንያት በ3,473 የሞባይል ጣቢያዎች፣ ታውሮች ላይ የአገልግሎት መስተጓጎል እና አደጋ እንዳጋጠመ አሳውቋል። በዚህም በ6 ወር ውስጥ 3.67 ቢሊዮን ብር ገቢ አጥቷል።

• በጦርነቱ የተጎዱ እና እስካሁን መድረስ በተቻለባቸው አካባቢዎች የወደሙ ንብረቶችን ለመተካት እንዲሁም ደግሞ አግልግሎት ለማስጀመር 328.9 ሚሊዮን ብር ወጪ ተደርጓል።

አሁን ላይ በፀጥታ ችግር ትግራይ ክልልን ጨምሮ በተለያዩ አካባቢዎች አገልግሎት መስጠት ያልተቻለባቸው ወረዳዎች እንደሚገኙ ኢትዮ ቴሌኮም አሳውቋል።

በአካባቢዎቹ ላይ ያለው የቴሌኮም መሰረተ ልማቶች ያሉበትን ሁኔታ ምንም ማወቅ እንዳልተቻለ ገልጿል።

ከዚህ ጋር በተያያዘ የአገልግሎት መቋረጥ ላጋጠማቸው ደንበኞች በሙሉ ይቅርታ ጠይቋል።

መረጃ ፦ ሸገር ኤፍ ኤም 102.1
ፎቶ : የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት

@tikvahethiopia
#Share #ሼር

ለጠቅላላ ሀኪሞች የወጣ የኮንትራት ቅጥር ፦

የደቡብ ክልል ጤና ቢሮ በዞን ጤና መምሪያ እና በልዩ ወረዳ ጤና ፅ/ቤት ክፍት የስራ መደብ ላይ ተፈላጊውን ችሎታ የሚያሟሉ ሀኪሞችን በኮንትራት ቅጥር አወዳድሮ መመደብ እንደሚፈልግ አሳውቋል።

👉 የስራው መደቡ መጠሪያ - ጠቅላላ ሀኪም
👉 የሙያ መስመር /ተፈላጊ ችሎታ - በጠቅላላ ህክምና በዲግሪ የተመረቀ/ች
👉 የስራ ልምድ- #ዜሮ_ዓመት
👉 ብዛት - 379 (#ሶስት_መቶ_ሰባ_ዘጠኝ )
👉 ደመወዝ - 9,056
👉 የስራ ቦታ - በእጣ ነው የሚለየው

ማሳሰቢያ ፦

1ኛ. በደቡብ ክልል ጤና ቢሮ በሚመደብበት በማንኛውም ዞን / ልዩ ወረዳ ሄደው ለመስራት ፍቃደኛ የሆነ /የሆነች።

2ኛ. በዕጣ ከጤና ቢሮ ለዞን/ልዩ ወረዳ ሲመደቡ ዞን/ልዩ ወረዳ በሚሰጠው በማንኛውም ጤና ተቋማ /ምደባ / ቦታ ሄደው ለመስራት ፍቃደኛ የሆነ/የሆነች።

3ኛ. በማንኛውም የመንግስት ተቋም ውስጥ ያልተቀጠረ /ያልተቀጠረች

የመመዝግቢያ ጊዜ ፦ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 10 ተከታታይ የስራ ቀናት። (ከተሰጠው ቀን ውጭ የሚመጣ አይስተናገድም)

የመመዝገቢያ ቦታ ፡ በደቡብ ክልል ጤና ቢሮ ሰው ሀብት አስተዳደርና ልማት ዳይሬክቶሬት በአካል በመቅረብ ሲሆን ኦርጂናል የትምህርት እና የሙያ ፍቃድ ማስረጃ ከማይመለስ ፎቶ ኮፒ ጋር መያዝ እንዳትዘነጉ።

የፈተናው ቀን : በቀጣይ ይገለፃል።

@tikvahethiopia
#GoodayOn Mobile App

የፈለጉትን ባለሙያ ካሉበት ሆነው አማርጠው የሚያገኙበት መተግበሪያ!

አስጠኚ ፣ ሹፌር ፣ ቧንቧ ሰራተኛ ፣ ኤሌክትሪሺያን ፣ ዲሽ ጥገና ፣ መካኒክ ፣ የግንባታ ፊኒሺንግ ፣ ሽያጭ ፣ የሂሳብ ባለሞያ እና ...ሌሎችም

ከGoodayOn መተግበሪያ በተጨማሪ ፤ ወደ 9675 ጥሪ ማእከል በመደወል አገልግሎታችንን ማግኘት ይችላሉ።

GoodayOn መተግበሪያን ለማውረድ ፤ https://cutt.ly/JWR6vZb
ቴሌግራም ቻናል ፤ @goodayOn #ጉዳይ 9675
#ችሎት

የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ሀይለማርያም ደሳለኝ ታስረው እንዲቀርቡ ትዛዝ ተሰጠ።

ከህዳር 4 ቀን 2011ዓ/ም ጀምሮ በስር ላይ የሚገኙት የቀድሞ የሜቴክ ዳሪክተር ሜ/ጀነራል ክንፈ ዳኘውን ጨምሮ አራት ተከሳሾች ከዕርሻ መሳሪያ ግዢ ጋር ተያይዞ በዓቃቢህግ በቀረበባቸውባቸው የሙስና ክስ የመከላከያ ማስረጃ ማሰማት መጀመራቸው ይታወሳል።

በዚህም መሰረት በሀምሌ 11ቀን 2013 ዓ/ም የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ ፍርድ ቤት ቀርበው እ.ኤ. አ በ2014 ዓ/ም በተደረገ በዝቅተኛ ወለድ ስምምነት ኢትዮጲያ ከፖላንድ መንግስት ባገኘችው 50 ሚሊዮን ዶላር ገንዘብ እዛው ፖላንድ ሀገር ለሚገኙ የዕርሻ መሳሪያ መለዋወጪያ ኩባንያዎች መከፈሉን እና ገንዘቡ ወደ ሀገር ውስጥ አለመምጣቱን በማብራራት የመከላከያ የምስክርነት ቃላቸው ተሰምቶ ነበር።

በዚሁ የክስ መዝገብ በመከላከያ ምስክርነት እንዲቀርቡ በተደጋጋሚ መጥሪያ እንዲደርሳቸው ትዛዝ ተሰቶባቸው የነበሩት የቀድሞ አቶ ሀይለማርያም ደሳለኝ ናቸው።

ለአቶ ሀይለማርያም ደሳለኝ መጥሪያ እንዲያደርስ የታዘዘው የፌደራል ፖሊስ በቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት በኩል አፈላልጌ ላገኛቸው አልቻልኩም ሲል መልስ ሰቶ ነበር።

 የተከሳሽ ጠበቆች በበኩላቸው አቶ ሀይለማርያም ደሳለኝ በግላቸው የሮማን ፉውንድሽን እንደሚሰሩና በመንግስ ፖሊስ እጀባ እየተደረገላቸው እንደሚቀሳቀሱ ጠቅሰው ይህ በሆነበት ሁኔታ ፖሊስ ላገኛቸው አልቻልኩም በማለት የሰጠው ምላሽ  አግባብነት የሌለው ነው ሲሉ በድጋሚ ትዛዝ እንዲሰጥላቸው ፍርድ ቤቱን ጠይቀዋል።

የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 5ኛ የሙስና ጉዳዮች ወንጀል ችሎት ፖሊስ አቶ ሀይለማርያምን ደሳለኝን ካሉበት አፈላልጎ አስሮ እንዲያቀርባቸው ትዛዝ ሰቷል።

ያንብቡ : https://telegra.ph/Tarik-Adugna-01-31

#TarikAdugna
#Amhara , #Dessise 📍

ዓለም አቀፍ ቀይ መስቀል ኮሚቴ (አይሲአርሲ) የደሴ አካል ተሃድሶ ማዕከልን ስራ ለማስጀመር የሚያግዙ መሰረታዊ ቁሳቁሶች እና ማሽነሪ ድጋፍ አድርጓል፡፡

ማዕከሉ ያሉበትን ክፍተቶች ለመሙላት እና የአካል ጉዳት ለደረሰባቸው ሰዎች የሚሰጠውን ድጋፍ እንዲቀጥል ለማገዝ ከግጭቱ በኋላ ማዕከሉ የሚገኝበትን ሁኔታ ላይ ዳሰሳ አድርጓል፡፡

#ICRC

@tikvahethiopia
#BahirDarUniversity

ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ከመቐለ ፣ አክሱም ፣ ዓዲግራት እና ወልድያ ዩኒቨርሲቲዎች በጊዚያዊነት ወደ ተቋሙ የተመደቡ የመደበኛ መጀመሪያ ዲግሪ ተማሪዎች ምዝገባ ከየካቲት 21 እስከ 24/2014 ዓ.ም መሆኑን አሳውቋል።

በመሆኑም በተገለጹት ቀናት የትምህርት ማስረጃችሁን (የምዝገባ ስሊፕ ፣ ግሬድ ሪፖርት እና የተማሪነት መታወቂያ) በመያዝ በተቋሙ በመገኘት ሪፖርት አድርጉ ብሏል።

የመጀመሪያ ዓመት ትምህርት ያላጠናቀቁ ተማሪዎች ደግሞ ለ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ተፈታኞች (አዲስ ገቢዎች) ጥሪ እስከሚደረግ መጠበቅ ይኖርባቸዋል ተብሏል።

More : @tikvahuniversity
TIKVAH-ETHIOPIA
#Afar #Abala #Tigray • " ወደታች ከባድ መሳሪያ እየጣሉ ነው። እንኳን የእርዳታ መኪኖች እና እዛ ያሉ የሚሸሹ ማህበረሰብ አባላት በትራንስፖርት እንዳይሸሹ አድርጓቸዋል ፤ ... የፌዴራል መንግስት ትኩረት ሊሰጠው ይገባል " - አቶ አብዶ አሊ • " የኢትዮጵያ ጦር ከዚህ ቀደም በተወሰነው ውሳኔ ባለበት ፀንቶ ነው የሚገኘው። በአካባቢው ላይ ምንም አይነት የመከላከያ ሰራዊት እንቅስቃሴ በሌለበት…
#Update

የአፋር ክልል ተፈናቃዮች ከ250 ሺህ በልጠዋል።

የአፋር ክልል ኮሚኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ አህመድ ካሎይታ ህወሓት በሁለት ዙር ባካሄደው ወረራ የኢትዮጵያ የወጪ እና ገቢ ንግድ የሚሳለጥበትን ሚሌን ለመያዛ እና ለመዝጋት አስቦ ነበር ያ ግን ሳይሳካ ቀርቷል አሁን ደግሞ በሶስተኛ ዙር ወራር በሰርዶ በኩል ያሰበውን ለማሳካት ተነስቷል ብለዋል።

አቶ አህመድ ፤ ክልሉ ከዚህ ቀደም ቡድኑ ባካሄደው ወረራ የተፈናቀለውን ህዝብ ለማቋቋም እየተሰራ ባለበት ሁኔታ ዳግም ለሶስተኛ ዙር ወረራ ተፈፅሞብናል ብለዋል።

አክለውም ፥ " አሻባሪው የህወሓት ቡድን 150 ኪሎ ሜትር ድረስ ወደ አፋር ክልል ዘልቆ በመግባት ከዚህ ቀደም በአፋር እና አማራ ክልል የፈፀመውን አይነት ጭካኔ እየፈፀመ ነው " ሲሉ ገልፀዋል።

ህወሓት ወደአፋር ክልል 150 ኪሎ ሜትር ዘልቆ በመግባት ኤሬብቲ ወረዳ፣ መጋሌ እና አብአላን መቆጣጠሩ ተሰምቷል።

አዲስ በተከፈተው ጥቃት ከቀደሞው በተጨማሪ ለሶስተኛ ጊዜ ከ250 ሺህ በላይ ህዝብ ከገዛ ቄየው ተፈናቅሎ መጠለያ ካምፕ ውስጥ እንደሚገኝ የአፋር ክልል ሪፖርት አድርጓል።

ከዚህ ቀደም ከ400 ሺህ በላይ ሰዎች የተፈናቀሉ ሲሆን እነሱን መልሶ በማደራጀት እና በማቋቋም ሂደት ውስጥ በተገባበት ሰዓት ነው ድጋሚ 250 ሺህ ሰዎች የተፈናቀሉት።

የአፋር ክልል ለደረሰው ጉዳት የሁሉንም እገዛ እና ትብብር እንደሚያስፈልገው አሳውቋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
ፎቶ : ዛሬ በእንጅባራ ከተማ የተከበረው 82ኛው የአገው ፈረሰኞች ማህበር በዓል ያለ ምንም የፀጥታ ችግር በሰላም ተከብሮ ነው የዋለው።

በዛሬው በዓል ላይ ከታዩት የፈረስ ትርዒቶች መካከል ጥቂቶቹ ከላይ ተያይዘዋል።

Photo Credit : APP & AMC

@tikvahethiopia