TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#Update የፕሬዝዳንት #ኢማኑኤል_ማክሮን መንግስት በነዳጅ ላይ ተጨማሪ ቀረጥ አስከትሎ በፓሪስና አካባቢዋ ሰዎች ሰልፍ ወጥተዋል፡፡ የፈረንሳይ መንግስት በፓሪስ ከተማ ብቻ 8 ሺህ የፖሊስ አባላትን አሰማርቶ አመፁን ለማስቆም ያደረገው ጥረት ብዙም ውጤታማ አልሆነም ተብሏል፡፡ በሳምንቱ መጨረሻ ቀናት ብቻ ፓሪስ ውስጥ በሰልፈኞች በፖሊሶች መካከል በተፈጠረ ግጭት ከ135 በላይ ሰዎች #ቆስለዋል፡፡

ምንጭ፦ ሲ ኤን ኤን
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ፈጣሪ ያውቃል⁉️

በረሐ እና ባሕር አቋርጠው ወደ ሳዑዲ አረቢያ የሚተሙት ኢትዮጵያውያን በየመን ጦርነት እንዳለ እንኳ አያውቁም። አንድ ወደ #ጅቡቲ የተሰደደ #የመናዊ በመንገድ ያገኟቸውን ኢትዮጵያውያን «ወዴት ነው የምትሔዱት? በመንገዳችሁ ጦርነት አለ ስንላቸው ፈጣሪ ያውቃል» የሚል መልስ ሰጡን ሲል ለኢኤንኤን ተናግሯል።

የአምነስቲ ኢንተርናሽናል ድረ-ገፅ እደሚጠቁመው በየመን የርስ በርስ #ጦርነት

•5,900+ ሰላማዊ ሰዎች #ተገድለዋል

•9,400+ ሰላማዊ ሰዎች #ቆስለዋል

•3 ሚሊዮን ከመኖሪያ ቀያቸው #ተፈናቅለዋል

•22.2 ሚሊዮን ሕይወታቸውን ለማቆየት የለት ደራሽ ዕርዳታ #ጥገኛ ናቸው

•2.5 ሚሊዮን ሕፃናት ከትምህርት ገበታ እርቀዋል፤ ቢሆንም #ኢትዮጵያውያኑ ፈጣሪ ያውቃል እያሉ መንገድ ላይ ናቸው።

Via Eshet Bekele
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ኒፕሲ ሐስል ተገደለ‼️

ትውልደ ኤርትራዊው የሎስ አንጀለሱ ታዋቂ ራፐር፣ #ኤርምያስ_አስገዶም (ኒፕሲ ሐስል) በተከፈተበት ተኩስ ሎስ አንደለስ ውስጥ መገደሉን የአሜሪካ መገናኛ ብዙሀን ዘግበዋል።

የ33 ዓመቱ ራፐር በርካታ ቦታዎች ላይ በጥይት መመታቱን እና ሆስፒታል እንደደረሰ ሕይወቱ ማለፉን ሎስ አንጀለስ ታይምስ ዘግቧል። ሌሎች ሁለት ሰዎችም በተተኮሰባቸው ጥይት #ቆስለዋል

ከኤርትራዊ አባት እና ጥቁር አሜሪካዊ እናት የተወለደው ኤርሚያስ አስገዶም በዚህ ዓመት ለሽያጭ ያበቃው አልበሙ በግራሚ የምርጥ ራፕ አልበሞች ምርጫ ላይ እጩ ለመሆን በቅቶ ነበር።

ሞቱ ካስደነገጣቸው ታዋቂ ሰዎች መካከል አንዷ ሪሃና ስትሆን "በዚህ ዜና መንፈሴ ታውኳል" ስትል የቲውተር ገጿ ላይ አስፍራለች።

ኤርሚያስ አስገዶም ተወልዶ ያደገው በደቡባዊ ሎስ አንጀለስ ሲሆን በተለያዩ የማህበረሰብ አቀፍ ስራዎችና በኪነጥበብ ስራዎች ላይ በመሳተፍ ይታወቃል።

"ያደኩት በውንብድና ቡድኖች ውስጥ ነው" ሲል ለሎስ አንጀለስ ታይምስ በአንድ ወቅት ቃለ መጠይቅ ሰጥቶ ነበር "... ሞት፣ ግድያ የየእለት ትዕይንቶቻችን ነበሩ። በጦርነት ቀጠና ውስጥ እንደመኖር ነው፤ ከዚህ መንደር ሰዎች ሲሞቱ ከቁብ አይቆጠርም ነበር።"

ኤርሚያስ ከመገደሉ በፊት በነበረ አንድ እሁድ "አምርሮ የሚጠላህ ሲኖር መባረክ ነው" በማለት በቲውተር ገፁ ላይ አስፍሯል።

Via BBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia