TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
ጋዜጠኛ ክብሮም ወርቁ ከእስር ተለቀቀ። ላለፉት 3 ወራት ከሶስት ቀን በእስር ላይ የነበረው የአሐዱ ሬዲዮ የዜና ክፍል ሀላፊ ክብሮም ወርቁ ዛሬ ከሰአት በኃላ ከእስር ተፈትቶ ከቤተሰቦቹ ጋር መቀላቀሉን ጠበቃው አቶ ጥጋቡ ደሳለኝ መናገራቸውን አሀዱ ሬድዮ እና ቴሌቪዥን አሳውቋል። @tikvahethiopia
ፎቶ : ጋዜጠኛ ክብሮም ወርቁ ከእስር ተፈቶ ከቤተሰቦቹ ጋር ተቀላቅሏል።

ጋዜጠኛው ከእስር መፈታቱን በተመለከተ በተረጋገጠ ፌስቡክ ገፁ ላይ " ከጥቅምት 18 እስከ ጥር 18 ... በእግዚአብሔር ምህረት ተፈትቻለሁ ፤ አመሰግናለሁ " ብሏል።

ጋዜጠኛ ክብሮ ወርቁ ላለፉት 3 ወራት በእስር ቆይቷል። ዛሬ ከአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ዋናው መስሪያ ቤት በመታወቂያ ዋስትና ነው ከእስር የተፈታው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ተነስቷል ?

" የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ተነስቷል " እየተባለ በማህበራዊ ሚዲያ የሚሰራጨው መረጃ ሀሰተኛ መረጃ ነው።

ለ6 ወራት የታወጀው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የተፈፃሚነት ጊዜ እንዲያጥር የሚኒስትሮች ምክር ቤት ዛሬ ውሳኔ አሳልፋል።

በዚህም አስቸኳይ ጊዜ አዋጁ የ6 ወር ጊዜው ሳይጠናቀቅ ጊዜውን የማሳጠር ስልጣን ያለው ህ/ተ/ም/ቤት የአዋጁን ተፈጻሚነት ቀሪ እንዲያደርገው #የሚጠይቅ የውሳኔ ሃሳብ በማፅደቅ ለምክር ቤቱ እንዲተላለፍ ተወስኗል።

ጉዳዩ ይህ ሆኖ ሳለ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ እንደተነሳ ተደርጎ የሚሰራጨው መረጃ ሀሰተኛ ነው።

ኢትዮጵያ አሁንም በአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ስር ናት።

@tikvahethiopia
#Safricom_Ethiopia

ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ከመሬት ባንክ ልማት ኮርፖሬሽን ጋር በመሆን ትላንት የውይይት መድረክ አዘጋጅቶ ነበር።

በዚሁ የውይይት መድረክ ሳፋሪኮም በኢትዮጵያ ለሚያካሂደው የኔትወርክ ግንባታ ቀጥተኛ አስተዋጽዖ ካላቸው ልዩ ልዩ ሚኒስቴትር መስሪያ ቤቶችና የመንግስት ተቋማት ከፍተኛ አመራሮች ጋር ትብብሩን በማጠናከር በቀጣይ ስለሚያስፈልጉን ድጋፎች መምከሩን ገልጿል።

ሳፋሪኮም ፥ " የኢትዮጵያ መንግስት የሚያደርግልን ያልተቋረጠ ድጋፍ ለደንበኞቻችን ምርጥ የሆነውን አገልግሎት ለማቅረብ እንዲሁም የኢትዮጵያን የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን አጀንዳ በብቃት እንድንደግፍ የሚያስችለን ነው " ብሏል።

አገልግሎቱን ለመጀመር እየተጋ መሆኑንም ገልጿል።

ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ በመጪዎቹ ጥቂት ወራት ውስጥ አገልግሎቱን በይፋ ይጀምራል ተብሎ ይጠበቃል።

@tikvahethiopia
#Tigray , #Mekelle📍

በዛሬው ዕለት የዓለም አቀፍ ቀይ መስቀል ኮሚቴ (ICRC) ከባለፈው መስከረም ወር ወዲህ በትግራይ ክልል መቐለ ከተማ የመጀመሪያውን የህክምና ቁሳቁስ ድጋፎችን ማድረስ መቻሉን አሳውቋል።

አስፈላጊ መድሃኒቶችን ያካተተው የአስቸኳይ ህክምና ቁሳቁሶች አቅርቦት በክልሉ በጣም ለተጎዱ የጤና ተቋማት ይደርሳል ተብሏል።

ዓለም አቀፍ ቀይ መስቀል ኮሚቴ ተጨማሪ በረራዎችን በማዘጋጀት በያዝነው እና በቀጣይ ሳምንታት የህክምና ቁሳቁስ ድጋፉን ለመቀጠል አቅዷል፡፡

በተመሳሳይ ድርጅቱ በአማራ እና አፋር ክልሎች በግጭቱ ምክንያት አገልግሎት መስጠት አስቸጋሪ ለሆነባቸው የጤና ተቋማት የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አሳውቋል።

ምንጭ : https://www.icrc.org/en/document/ethiopia-icrc-aid-flight-delivers-lifesaving-medical-supplies-tigray

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
ኮሎኔል ማማዲ ዱምበያ ስለብሄራዊ ቡድኑ ምን አሉ ?

የጊኒ ብሄራዊ ቡድን በካሜሮን የ2021 አፍሪካ ዋንጫ በጊዜ ከተሰናበቱት ሀገራት መካከል እንደምትገኝበት ይታወቃል።

ቡድኑ ወደ ካሜሮን በተሸኘበት ምሽት አሁን ጊኒን እያስተዳደር ያለው የጁንታ መሪ ኮሎኔል ማማዲ ዱምበያ ለቡድኑ አባላት ያስተላለፉት መልዕክት መነጋገሪያ ሆኖ እንደነበር የሁላችንም ትውስታ ነው።

ኮሎኔል ማማዲ ዱምበያ የሀገሪቱን ባንዲራ 🇬🇳 ለቡድኑ ካስረከቡ በኃላ ባስተላለፉት መልዕክት የቡድኑ አባላት ዋንጫውን ይዘው እንዲመጡ ካልሆነ ግን በእነሱ ላይ ኢንቨስት የተደረገውን እያንዳንዱን ገንዘብ እንዲመልሱ /እንዲተኩ ነበር ያሉት።

ቡድኑም በአፍሪካ ዋንጫው ሳይሳካለት ቀርቶ በጊዜ ተሰናብቷል ፤ ይህን ተከትሎ የጁንታውን መሪ ኮሎኔል ማማዲ ዱምበያ አስተያየት ብዙዎች ሲጠብቁት ነበር።

ኮሎኔል ማማዲ ዱምበያም ዝም አላሉም።

ኮሌኔሉ ብሄራዊ ቡድኑን 'ይቅር' እንዳሉ ገልፀው ፤ በወቅቱ ያን ንግግር የተናገሩት ቡድኑን ለማበረታታ ብቻ መሆኑ አሳውቀዋል። " የቡድን ግንባታ ጊዜ እንደሚወስድ እገነዘባለሁም " ብለዋል።

ነገር ግን ለቡድኑ የተሰጠው ገንዘብ ሩብ ፍፃሜ ፣ ግማሽ ፍፃሜ እና የፍፃሜ ጨዋታዎችን የሚሸፍን ሲሆን ያ ገንዘብ ወደ መንግስት ካዝና ይመለሳል ተብሏል።

@tikvahethiopia
#NewsAlert

የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ፕሬዚዳንት ሣህለ ወርቅ ዘውዴ ለተለያዩ ግለሰቦች የሙሉ አምባሳደርነት እና የአምባሳደርነት ሹመት ሰጡ።

በዚህም መሠረትም፡-

1/ አቶ ተፈራ ደርበው
2/ አቶ ደሴ ዳልኬ
3/ ዶክተር ስለሺ በቀለ
4/ ጄኔራል ባጫ ደበሌ
5/ ጄኔራል ሀሰን ኢበራሂም
6/ ወ/ሮ ሽትዬ ምናለ
7/ ፕሮፌሰር ፍቃዱ በየነ
8/ አቶ ረሻድ መሀመድ
9/ አምባሳደር ጀማል በከር
10/ አቶ ፈይሰል ኦሊይ
11/ አቶ ኢሳያስ ጎታ
12/ አቶ ፀጋአብ ክበበው
13/ አቶ ጣፋ ቱሉ
14/ ዶክተር ገነት ተሾመ
15/ አቶ ዳባ ደበሌ
16/ አቶ ፍቃዱ በየነ የባሉሙሉ ሥልጣን አምባሳደር ሆነው ሲሾሙ።

1/ አቶ አሳየ አለማየሁ
2/ አቶ ኃይላይ ብርሃነ
3/ አቶ አወል ወግሪስ
4/ ወ/ሮ ብዙነሽ መሠረት
5/ አቶ አንተነህ ታሪኩ
6/ አቶ አክሊሉ ከበደ
7/ አቶ ሰይድ መሐመድ
8/ አቶ ዮሴፍ ካሳዬ
9/ አቶ ዘላለም ብርሃን
1ዐ/ ወ/ሮ ፍርቱና ዲባኮ
11/ አቶ ወርቃለማሁ ደሰታ በአምባሳደርነት የተሾሙ መሆኑን ከፕሬዝዳንት ፅሕፈት ቤት የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡

@tikvahethiopia
#ETHIOPIA

የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት ለሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነርነት ከቀረቡት ዕጩዎች መካከል 42ቱን መለየቱን የም/ቤቱ አፈ-ጉባኤ የተከበሩ አቶ ታገሰ ጫፎ ዛሬ አሳውቀዋል።

አቶ ታገሰ ፥ ከመላው የሀገሪቱ ክፍሎች 632 የእጩ ኮሚሽነሮች ጥቆማ መቅረባቸውንና አብዛኛዎቹ ስራውን ለመስራት የሚያስችል ልምድና ዕውቀት ያላቸው መሆኑን መገንዘብ መቻሉን ጠቁመዋል፡፡

አዋጁ ለአፈ-ጉባኤውና ለአፈ-ጉባኤው ጽ/ቤት በሰጠው ስልጣን እንዲሁም በአዋጁ በተቀመጠው መስፈርት መሰረት ከቀረቡት 632 ዕጩዎች መካከል 42ቱ መለየታቸውን ተናግረዋል፡፡

በቀረቡ 42 ዕጩ ኮሚሽነሮች ላይ ከአማካሪዎች ጋር ምክክር እየተደረገበት መሆኑን ገልጸዋል፡፡

በቀጣይ ሳምንት ደግሞ የሲቪክ ማህበራት ተወካዮች ፣ የሀይማኖት ተቋማት ጉባኤ አመራሮች፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ም/ቤት አመራር አካላት በሚገኙበት በዕጩዎች የትምህርት ዝግጅትና የስራ ልምድ ላይ ምክክር ተደርጎ ግብአት የሚሰበሰብ መሆኑንም አብራርተዋል፡፡

በማስከተልም በም/ቤቱ ድረ-ገጽና በማህበራዊ ሚዲያ የእጩዎችን ማንነት በመግለጽ በቂ ግብአት ከተሰበሰበ በኋላ ሰብሳቢና ም/ሰብሳቢን ጨምሮ 11ዱ ዕጩ ኮሚሽነሮች ለም/ቤቱ ቀርቦ ከፀደቀና ዕጩዎች ከተሰየሙ በኋላ ወደ ስራ እንደሚገባም ገልጸዋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
" ... ከአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ጋር ተያይዞ አሁንም በቁጥጥር ስር ያሉ ሰዎች በአፋጣኝ ይለቀቁ " - ኢሰመኮ

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) የኢፌዲሪ ሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ከጥቅምት 23 ቀን 2014 ዓ.ም. ጀምሮ ተግባራዊ የነበረው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ እንዲነሳ ለሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት ያቀረበው የውሳኔ ሃሳብ አበረታች እርምጃ መሆኑን ገልጿል።

ኮሚሽኑ ፤ ለአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ምክንያት የነበረው ሁኔታ በመሻሻሉና የአስቸኳይ ጊዜ ሁኔታ በሰብአዊ መብቶች ላይ የሚፈጥረውን ተጽዕኖ ከግምት በማስገባት የአዋጁ አስፈላጊነት እየተገመገመ ተገቢው ማሻሻያ እንዲደረግ ጥሪ አቅርቦ የነበረ መሆኑ አስታውሷል።

የሕዝብ ተወካዮች ም/ ቤት በመንግስት የቀረበለትን ውሳኔ ሃሳብ በአፋጣኝ እንደሚያጸድቀው ኢሰመኮ ተስፋውን የገለፀ ሲሆን የመንግስት ስራ አስፈጻሚ አካላት ከአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ጋር ተያይዞ አሁንም በቁጥጥር ስር ያሉ ሰዎች በአፋጣኝ እንዲለቀቁ ጥሪውን አቅርቧል።

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የአስቸኳይ ጊዜ ሁኔታው አዋጅ የተነሳ መሆኑን ከሚያጸድቅበት ቀን ጀምሮ ከእስር ያልተለቀቁ ሰዎች የሚኖሩ ቢሆን፤ ከ48 ሰዓታት ባልበለጠ ጊዜ ውስጥ ወደ ፍርድ ቤት አለመቅረብ እስሩ ከሕግ ውጭ የሚያደርገው በመሆኑ የሁሉም የሕግ አስከባሪ አካላት የሕግ ማስከበር ተግባራት የሰብአዊ መብቶችን ባከበረ መልኩ በመደበኛው ሥርዓት እንዲከናወኑ አሳስቧል።

@tikvahethiopia
#USA #ETHIOPIA

የአሜሪካ መንግሥት በአሜሪካ ዓለም አቀፍ የልማት ተራድኦ ድርጅት /USAID/ አማካይነት በኢትዮጵያ በኦሮሚያ ክልል፣ 400ሺ በላይ ሰዎችን ኑሮ ሊያሻሽል የሚችል፣ በ10.2 ቢሊዮን ብር ሁለት አዳዲስ የመዋዕለ ንዋይ ፕሮጀክቶችን ተግባራዊ እንደሚያደርግ አስታውቋል።

በኢፋ /Iffa/ እና በUSAID ተግባራዊ የሚደረጉ 2ቱ የመዋዕለ ንዋይ ፕሮጀክቶች በኢትዮጵያ መንግሥት የሚመራውንና 9 ሚሊዮን ሰዎች ራሳቸውን ከድህንነት እንዲያወጡ የሚያግዘውን የማኅበራዊ የምርት ደህንነት ወይም ሴፍቲኔት መርኃግብር እንደሚያጠናክር በኢትዮጵያ የአሜሪካ ኤምባሲ ዛሬ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል፡፡

በመላው ኢትዮጵያ በተለያዩ ክልሎች እየተካሄዱት ለሚገኙ ተመሳሳይ መርኃግብሮች ቀዳሚውን ድጋፍ እየሰጠ ያለው ዩኤስኤድ መሆኑን መግለጫው ጠቅሶ እኤአ ከ2015 ጀምሮ ወደ 60 ቢሊዮን ብር ማውጣቱን አስታውቋል፡፡

አሁን የሚካሄዱት ሁለቱ መርኃግብሮችም በአሜሪካ እና በኢትዮጵያ መካከል የቆየውን ወዳጅነትና የጋራ ፍላጎት እንደሚያረጋግጡም መግለጫው አመልክቷል፡፡

በዚህ ሳምንት ውስጥ ይፋ የተደረጉት ሁለቱ ፕሮጀክቶች USAID ባላፉት 5 ዓመታት ውስጥ በ220 ቢሊዮን ብር ኢትዮጵያ ውስጥ ተግባራዊ እያደረጋቸው የሚገኙ ፕሮጀክቶች አካል መሆናቸውንም አመልክቷል፡፡

የሚሰጠው ድጋፍ በሁሉም አካባቢ ያሉ ኢትዮጵያውያን የተሻለ ጤናማና የበለጸገ ህይወት እንዲመሩ የሚያግዝ መሆኑንም በኢትዮጵያ የአሜሪካ ኤምባሲ መግለጫ አስታውቋል፡፡

ምንጭ፦ በኢትዮጵያ የአሜሪካ ኤምባሲ / ቪኦኤ

@tikvahethiopia
#ተወዳደሩ #GenerationUnlimitedEthiopia

የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የጀነሬሽን አንሊሚትድ መፍትሔ አምጪ የሥራ ሃሳቦችን ማወዳደር ጀምሯል።

ሚኒስቴሩ የወጣቶችን የሥራ ፈጠራ ሃሳቦች ለማበረታታት ከተለያዩ አጋር ድርጅቶች ጋር የሚያከናውነው የ 2014 ዓ.ም የጀነሬሽን አንሊሚትድ ለውጥ አምጪ የወጣቶች ውድድር ይፋ ሆኗል።

የዚህ ውድድር ተልዕኮ በዓለም አቀፍ ደረጃ 1.8 ቢሊዮን ወጣቶችን ከተለያዩ ዕድሎች ጋር ማገናኘት መሆኑ ተገልጿል።

አቶ ጥዑመዝጊ በርሔ በሥራ እና ክህሎት ሚኒስቴር የአጋርነት እና ፈንድ ዳይሬክተር ፥ " ወጣቶችን የማገናኘት እና አቅማቸውን የማሳደግ እንቅስቃሴ በቀድሞ ሥራ ዕድል ፈጠራ ኮሚሽን ተጀምረው በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ከቀጠሉት አንዱ ሆኖ ይህ ዓለማቀፍ መሆኑ ይለየዋል " ብለዋል።

አክለውም ፤ " 35 በሚጠጉ አገራት መካከል የሚካሄድ፣ በአገራችን 5 ከተሞች ተከናውኖ በ 8 ሳምንታት የሚጠናቀቅ ፣ ሁለት ተወዳዳሪ ቡድኖችን ለዓለማቀፍ ውድድር የሚያዘጋጅ፣ ለአገራችን ወጣቶች ትልቅ መነቃቃት የሚፈጥር መሆኑን ገልፀው ወጣት ሥራ ፈጣሪዎች ዕድሉን ይጠቀሙበት " ሲል መልዕክት አስተላልፈዋል።

የተባበሩት መንግስታት የልማት ፕሮግራም (UNDP) ተወካይ ወጣት ሥራ ፈጣሪዎች ልዩ ሃሳቦቻቸውን አዳብረው የማኅበረሰባቸውን ችግር በመፍታት ተፅዕኖ ማሳደር እንዲችሉ ድጋፍ በማድረጋችን ኩራት ይሰማናል ብለዋል።

ውድድሩ ኢትዮጵያዊ ወጣት ሥራ ፈጣሪዎች ዘላቂ የልማት ግቦችን ስኬት ለማፋጠን የሚቀርቡ የፈጠራ ሃሳቦች ላይ አትኩሮ ክትትልና ድጋፍ በማድረግ ሃሳባቸውን ተግባራዊ ለማድረግ መነሻ ገንዘብ ይመድባል።

የውድድር የማመልከቻ መቀበያው ጥር 17 ቀን 2014 ዓ.ም ሆኖ የካቲት 1 ቀን 2014 ዓ.ም ይጠናቀቅና ውድድሩ ይቀጥላል።

ይህንን ውድድር የተለያዩ ዓለማቀፍ ተቋማት የደገፉት ሲሆን ሥራው በፈርስት ኮንሰልት አማካኝነት ይከናወናል።

በኦላይን ለመመዝገብ 👉 https://bit.ly/3rQOERQ

#ሼር #Share

@tikvahethiopia
#AddisAbabaUniversity

የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ነፃ እና እራሱን የቻለ ሆኖ እንዲንቀሳቀስ ለማድረግ የተደራጀው ግብረ ሀይል ወደ ስራ መግባቱ ተገልጿል።

የትምህርት ሚኒስቴር ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሥራ አመራር ቦርድ ጋር የግብረ ሃይሉን የሥራ ማስጀመሪያና ትውውቅ መድረክ አካሂደዋል፡፡

መንግስት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተቋማዊ ነጻነት ተጎናፅፈው መስራት እንዲችሉ ባስቀመጠው አቅጣጫ መሰረት የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ተቋማዊ ነፃነት ኖሮት መልሶ እንዲደራጅ በመሰራት ላይ እንደሚገኝ ትምህርት ሚኒስቴር ገልጿል።

በውይይቱ ላይ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ፤ አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲን ተቋማዊ ነጻነት መስጠት ከመንግስትም ከማህበረሰቡም ስምምነት የተደረሰበት መሆኑን ገልፀዋል።

ይህ የለዉጥ ስራ ለአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ተቃማዊ ነጻነትን ማምጣት ብቻ ሳይሆን ለሌሎች ዩኒቨርስቲዎችም ተቋማዊ ነጻነት የሚሰጥ መሆኑንም አሳውቀዋል።

የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተቋማዊ ነፃነት በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ተጀምሮ ወደ ሌሎች ከፍተኛ ተቋማትም የሚስፋፋ መሆኑም ተገልጿል።

#MoE

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ይበቃል ሳዑዲ አረቢያ ውስጥ ያሉ ዜጎቻችን ፍትህን እንዲያገኙ የሚጠይቅ የማህበራዊ ሚዲያ ዘመቻ እየተካሄደ መሆኑን ተመልክተናል። ዘመቻው ሳዑዲ ያሉ ዜጎቻችን እምነበረድ ላይ ለብሰው የሚተኙትን ጥቁር ፌስታል በመልበስ አጋርነት የሚገለፅበት ነው። ሳዑዲ አረቢያ ውስጥ በርካታ ዜጎቻችን እጅግ አስከፊ በሆነ ሁኔታ ውስጥ እንዳሉ ይታወቃል። የሳኡዲ አረቢያ መንግስት መሰረታዊ የእስረኛ አያያዝ ህግን እንዲተገብር፣…
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#Update

በሳውዲ ታሳሪዎች ጉዳይ ከንጉሥ ሰልማን ጋር ለመወያየት ለፊታችን ቅዳሜ ቀጠሮ መያዙ ተሰምቷል።

የኢትዮጵያንና የሳውዲ ዐረቢያን ግንኙነት ለማሻሻልና በሳውዲ ታስረው የሚገኙና ወደ ሀገራቸው መመለስ በሚፈልጉ ኢትዮጵያውያንን ጉዳይ መፍትሄ እንዲያገኝ የኢትዮጵያ መንግስት የላካቸው ከፍተኛ የልዑክ ቡድን የፊታችን ቅዳሜ ከንጉስ ሰልማን ኢብኑ አብዱልአዚዝ ጋር ዉይይት ያደርጋሉ።

በተጨማሪ ልዑኩ በቆታው ከሳውዲ የዉጭ ጉዳይ ሚኒስትርና ሌሎች ባለስልጣናት ጋር ይመክራል ተብሎ ይጠበቃል።

የልዑካን ቡድኑ ከሚኒስትሮች፥ከሃይማኖት አባቶች፥ከዉጭ ጉዳይ ሚኒስትርና በኢትዮ-ሳውዲ ጉዳይ ከፍተኛ ምርምር ያደረጉ ግለሰቦች የተካተቱበት ነው።

ልዑኩ የተላከው የእስረኞችን ችግር ለመፍታትና የሀገራቱን ግንኙነት ለማሻሻል ልዑክ በመላክ ንጉሡን ማናገር እንደሚገባ በሳውዲ ዐረቢያ የኢትዮጵያ አምባሳደር ሌንጮ ባቲ ባቀረቡት ምክረ ሀሳብ መነሻነት መንግስት ልዑኩ ወደ ሳውዲ እንዲሄድ መንግስት መወሰኑን ነው የተሰማው።

ልዑኩ በአሁኑ ሰዓት በሳውዲ ዐረቢያ ዋና ከተማ በሪያድ ከተማ ይገኛል። የልዑኩ አባላት አስር ሲሆኑ የሚከተሉት ይገኙበታል።

1) አቶ አሕመድ ሺዴ
2) አምባሳደር ሪድዋን ሁሴን
3) ዶ/ር ጄይላን ከድር
4) ፕሮፌሰር አደም ካሚል
5) ሙፍቲ ሀጅ ዑመር እድሪስ
6) ቄስ ታጋይ ታደለ
7) አቶ መስፍን ገብሬ
8)አቶ ሀይደር አብደላ
9) አምባሳደር ሌንጮ ባቲ
የኢትዮጵያንና የሳውዲ ዐረቢያን ግንኙነት በተመለከተ ፕሮፌሰር አደም ካሚል በዐረብኛ ቋንቋ ለንጉሡ ገለፃ እንዲያደርጉ በልዑኩ ተመርጠዋል።

ምንጭ፦ ኡስታዝ ካሚል ሸምሱ

@tikvahethiopia