TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
የ125ኛው ዓድዋ የድል በዓል እየተከበረ ይገኛል :

#Menelik_II_Square

125ኛው የዓድዋ ድል በዓል በአዲስ አበባ ከተማ በሚኒሊክ አደባባይ በተለያዩ ትዕይንቶች ታጅቦ እየተከበረ ይገኛል።

በበዓሉ ፕሬዚዳንት ሣኅለወርቅ ዘውዴ፣ ጀግኖች አርበኞች፣ የመንግሥት ከፍተኛ ባለሥልጣናት እንዲሁም የጉዞ አደዋ የዘንድሮ ተሳታፊዎች እና ከተለያዩ አካባቢዎች የመጡና የከተማዋ ነዋሪዎች ተገኝተዋል።

#MeskelSquare

የአድዋ የድል በዓል በመስቀል አደባባይ በድምቀት እየተከበረ ይገኛል።

በዓሉ የኦሮሚያ ክልል ፕሬዜዳንት አቶ ሽመልስ አብዲሳ፥ የፌዴራል እና የክልል የስራ ሀላፊዎች፥ የጥንት አርበኞች፥ የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች ፥ ከተለያዩ የፊንፊኔ ዙሪያ የኦሮሚያ ልዩ ዞን ከተሞች የታደሙ 20 ሺህ የሚሆኑ ፈረሰኞች በተገኙበት እየተከበረ ይገኛል።

#Debremarkos

በአሁኑ ሰዓት የጎጃም ደብረማርቆስና አካባቢው ማህበረሰብ የአደዋን በዓል በንጉስ ተክለሃይማኖት አደባባይ በመገኘት በማክበር ላይ ይገኛል።

#Bahirdar

በባህርዳር ከተማ 6ቱ ክፍለ ከተሞች በአንድነት 125ኛውን የአድዋ ድል በዓል በድምቀት እያከበሩ ነው።

በዓሉ የአማራ ክልል ርዕሰመስተዳድር አቶ አገኘሁ ተሻገር እና ሌሎች የመንግስት የስራ ሀላፊዎች በተገኙበት እየተከበረ ይገኛል።

#Gondar

የአድዋ ድል በዓል በጎንደር ከተማ በልዩ ልዩ ዝግጅቶች በመከበር ላይ ይገኛል፡፡

በበዓሉ አባት አርበኞች፣ ወጣቶች፣ ልዩ ልዩ የጸጥታ አባላትና ከተለያዩ የከተማዋ ክፍሎች የተወጣጡ ነዋሪዎች ታድመውበታል።

More : @tikvahethmagazine