TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
የትኞቹ የህዝብ አገልግሎት መስጫ ተቋማት መስማት ለተሳናቸው ዜጎች ምቹ ናቸው? ኢትዮጵያ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዓለም አቀፍ የአካል ጉዳተኞች መብቶች ስምምነትን በአዋጅ ቁጥር 676/2002 አጽድቃ ተቀብላለች። በስምምነቱ መሰረትም ፈራሚ ሀገራት መስማት የተሳናቸው ሰዎች የሕይወትና የማኅበራዊ እድገት ክህሎት እንዲያገኙ ብሎም በማኅበረሰባቸው ውስጥ ሙሉና ውጤታማ ተሳትፎ እንዲያደርጉ የምልክት ቋንቋ…
በኢትዮጵያ የምልክት ቋንቋ ሕገ-መንግስታዊ እውቅና ሊሰጠው ይገባል !

በዓለም ላይ #ሰባ_አምስት ሀገራት የምልክት ቋንቋን እንደ ብሔራዊ ቋንቋ አድርገው ከመቀበል ጨምሮ በሰነድ የተደገፈ ሕጋዊ እውቅና ሰጥተዋል፡፡ በአፍሪካ ደግሞ ኬንያ፣ ደቡብ አፍሪካ፣ ኡጋንዳ፣ ዙምባቡዌ ብሔራዊ ቋንቋቸው አድርገው ተቀብለውታል፡፡

በኢትዮጵያ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ተጠቃሚዎች ያለው ይኽ ቋንቋ በፖሊሲም ሆነ በአፈጻጸም ትኩረት ያልተሰጠው ቋንቋ ነው፡፡

በኢትዮጵያም የምልክት ቋንቋ ሕገ-መንግስታዊ እውቅና ሊሰጠው ይገባል።

#HandsSpeakEyesListen
#እጆች_ይናገራሉ_አይኖች_ያዳምጣሉ