TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
አሜሪካ የአየር ጥቃት ፈፀመች።

አሜሪካ #በአፍጋኒስታን ፣ ካቡል በፈፀመችው የድሮን ድብደባ አሸባሪዎችን ሳይሆን ንፁሃንን መግደሏን ካመነች ከቀናት በኃላ #በሶሪያ የአየር ጥቃት ፈፅማለች።

የአሜሪካ ጦር የአየር ጥቃቱ አንድ ከፍተኛ የአል-ቃይዳ የአሸባሪ በድን ኃላፊን ለመግደል ያለመ እንደሆነ አሳውቋል።

የአሜሪካ ማዕከላዊ ኮማንድ እንዳሳወቀው ከሆነ ጥቃቱ ኢድሊብ አቅራቢያ የተፈፀመ ሲሆን፤ ያነጣጠረው በሽብርተኛው የአል-ቃይዳ ቡድን ላይ ነው።

የአየር ጥቃቱን ተከትሎ ሲቪሎች ላይ ጉዳት መድረሱን የሚያሳይ ነገር እንደሌለ የአሜሪካ ጦር ገልጿል።

የፔንታጎን ባለስልጣናት ጥቃቱን አረጋግጠው ተጨማሪ መረጃ ከመስጠት ተቆጥበዋል።

ትላንት በማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ የአሜሪካ የአየር ጥቃት የአል -ቃይዳ ተባባሪ የሆነውን "ሁራስ አል-ዲን" 2 ከፍተኛ ኃላፊዎችን መግደሉን የሚገልፁ መረጃዎች ሲሰራጩ ነበር።

@tikvahethiopia
#UNSC

ዛሬ የተመድ የፀጥታው ምክር ቤት #በአፍጋኒስታን ጉዳይ በአሜሪካ የቀረበ የውሳኔ ሀሳብ በሙሉ ድምፅ አፀደቀ።

የተመድ የፀጥታው ምክር ቤት ዛሬ ረቡዕ ባካሄደው ስብሰባ ለአፍጋኒስታን ሰብአዊ ርዳታ የሚያመቻች በአሜሪካ የቀረበ የውሳኔ ሃሳብ በመሉ ድምፅ አጽድቋል።

የውሳኔ ሀሳቡ፥ "የገንዘብ ክፍያ፣ ሌሎች የፋይናንስ ሀብቶች ወይም የኢኮኖሚ ሀብቶች እና እንዲህ ዓይነቱን እርዳታ በወቅቱ ለማድረስ ወይም መሰል ተግባራትን ለመደገፍ አስፈላጊ የሆኑ እቃዎችና አገልግሎቶች አቅርቦት ይፈቀዳል " ነው የሚለው።

እንዲህ ያለው እርዳታ " አፍጋኒስታን ውስጥ ያሉ መሰረታዊ የሰው ልጆች ፍላጎቶችን " የሚደግፍ እንጂ ከታሊባን ጋር በተገናኙ አካላት ላይ የተጣለውን ማዕቀብ " መጣስ አይደለም " ሲልም ያክላል።

አፍጋኒስታን በከፋ የኢኮኖሚ ውድቀት አፋፍ ላይ ትገኛለች።

@tikvahethiopia