TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update አርቲስትና አክቲቪስት ታማኝ⬆️

አርቲስት፣ አክቲቪስትና የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ታማኝ በየነን በፍቅር ለመቀበል ዝግጁ መሆኑን የቅበላ ኮሚቴዉ አስታወቀ፡፡

ለአቀባበሉ የተዋቀረዉ ኮሚቴ ዛሬ በሰጠዉ መግለጫ እንዳስታወቀዉ አርቲስት፣ አክቲቪስትና የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ታማኝ በየነ አቀባበል ሙሉ ዝግጅት ተጠናቋል ብሏል፡፡

ታማኝ በየነ በኪነ ጥበቡ ዙሪያ ሀገራዊ ጉዳዮችን በማነቃቃት፣ የመድረክ ፈርጥ ሆኖ ሌሎች ተከታዮቹን በመፍጠር ትልቅ አስተዋጽኦ አበርክቷል ተብሏል፡፡

ለረጅም ዓመታት #አንድነትን#ፍቅርን#መቻቻልን እና መተሳሰብን ሲሰብክ የኖረ፣ አንድ ህዝብ አንዲት ኢትዮጵያ የሚል አቋም ያለዉ እና ብሔር ሃይማኖት ሳይለይ ለኢትዮጵያ ህዝብ የታገለ የኢትዮጵያ ልጅ መሆኑን በተሰጠዉ መግለጫ ተገልጿል፡፡

ይህ ኢትዮጵያዊ #ጀግና ነሐሴ 26/2010 ዓ.ም በቦሌ ኢንተርናሽናል አየር ማረፊያ የመንግስት ሀላፊዎች፣ የኪነ ጥበብ ባለሙያዎችና የሥራ ባልደረቦቹ እና አድናቂዎቹ በተገኙበት ደማቅ አቀባበል ይደረግለታል ብለዋል። በመሆኑም ሁሉም ኢትዮጵያዊ በዚህ ዕለት ተገኝተዉ በፍቅር እጃቸዉን ዘርግተዉ እንዲቀበሉት ጥሪ አስተላልፈዋል፡፡

©የአዲስ አበባ ኮሚኒኬሽን
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ደዴሳ⬆️

እለተ እሁድ የሀይማኖት አባቶች በታደሙበት እንዲሁም የአካባቢው አስታራቂ ሽማግሌዎች ወደ ሁለቱም ተጎጂ ቤተሰቦች ቤት በማቅናት በባህሉ መሰረት እርጥብ ሳር በማቅረብ፣ በግ በማረድ እና አጥንት በመስበር ብሎም በሌሎች ክንውኖች ቂም በቀልን አጥፍቶ እርቅ፣ #ሰላምና #አንድነትን የሚያበስረው ስነ-ስርአት ተካሂዷል፡፡ በሎይጅጋንፎ ወረዳ በለው #ደዴሳ ቀበሌ በቤኔሻንጉል ጉሙዝ እና በአማራ ተወላጆች መካከል ግጭት ተፈጥሮ እንደነበር ይታወሳል፡፡

©አብመድ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update አዲስ አበባ⬆️

ከሚቀጥለው ዓመት ጀምሮ ለአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች የሚሰጠው የመታወቂያ ካርድ #ይዘትና ንድፍ ለካቢኔ ቀረበ፡፡ በምክትል ከንቲባ #ታከለ_ኡማ (ኢንጂነር) የሚመራው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ፣ በቀረቡለት ሁለት አማራጮች ላይ ከመከረ በኋላ አንዱን ያፀድቃል ተብሎ ይጠበቃል፡፡

በተሻሻለው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የነዋሪዎች ምዝገባና የመታወቂያ አሰጣጥ መመርያ ቁጥር 3/2010 መሠረት የተዘጋጀው አዲሱ መታወቂያ፣ ከቀድሞው የሚለይባቸው ይዘቶች አሉ፡፡

አዲሱ መታወቂያ ‹‹የአዲስ አበባ ከተማ የነዋሪ መታወቂያ›› የሚል ሲሆን፣ የክፍለ ከተማና የወረዳ መግለጫ አልያዘም፡፡

ከዚህ በተጨማሪ የትውልድ ሥፍራና #የብሔር ስያሜ ያላካተተ ሲሆን፣ ዜግነትን በልዩነት አካቶ ይዟል፡፡

የአዲሱ መታወቂያ የምዝገባ ሒደት በኮምፒዩተር የታገዘ የዲጂታል አሠራር የሚከተል ሲሆን፣ በአሻራ የተደገፈ ነው፡፡

መታወቂያው በአማራጭ #በሁለት ቀለማት በመዘጋጀቱ፣ ካቢኔው የሚመርጠው አንደኛው ንድፍ ተቀባይነት እንደሚያገኝ ተመልክቷል፡፡

የመታወቂያ አሰጣጥ ሒደቱንና ይዘቱን እንደ አዲስ ማዘጋጀት ያስፈለገው፣ የቀድሞው መታወቂያ #ብሔርን የሚያጎላና #አንድነትን የሚያላላ በመሆኑ ነው ተብሏል፡፡

ምክትል ከንቲባ ታከለ እንዳሉት የቀድሞው መታወቂያ ቀላል ቢመስልም ከፍተኛ ቅሬታ ሲነሳበት ቆይቷል፡፡ የመታወቂያውን ይዘት በማስተካከል፣ አንድነትን ማጎልበት ያሻል በሚል ዕርምጃው መወሰዱ ተመልክቷል፡፡

ከዚህ ባለፈም መታወቂያ አሰጣጡ አሻራን የሚጠቀምና ዲጂታል ስለሆነ፣ ሕገወጦችን ለመቆጣጠር አመቺ መሆኑ ተገልጿል፡፡

በአዲሱ መታወቂያ ከዚህ ቀደም ይፈጸሙ የነበሩ ማጭበርበሮችን ማከናወን እንደማይቻል፣ በምርጫ ጊዜ ተደጋጋሚ ምዝገባ ማድረግ እንደማይቻልና ሌሎች ሕገወጦች ድርጊቶችን መፈጸም አይቻልም ተብሏል፡፡

መታወቂያው ለካቢኔው ቀርቦ ይሁንታ ካገኘ በኋላ የሕዝብ አስተያየት እንደሚሰጥበት ተጠቁሟል፡፡ ከዚህ በኋላ በቅርቡ የነዋሪዎች ምዝገባ እንደሚጀመር ለማወቅ ተችሏል፡፡

የአዲሱ መታወቂያ አጠቃላይ ወጪ ኅትመትን ጨምሮ 300 ብር ያህል ቢሆንም፣ ነዋሪዎች ግን የሚከፍሉት የካርዱን ዋጋ ብቻ 80 ብር እንደሆነ ታውቋል፡፡

©ሪፖርተር
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ፌደራል ፖሊስ⬇️

ለኦነግ አባላትና አመራር በአዲስ አበባ የተዘጋጀው የአቀባበል ስነስርዓት #ያለአንዳች ችግር መጠናቀቁን የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጀነራል ዘይኑ ጀማል አስታወቁ።

ኮሚሸነሩ ከfbc ጋር ባደረጉት ቆይታ በአቀባበል ስነስርዓቱ ላይ የአዲስ አበባ ፖሊስ፣ የሀገር መከላከያ፣ የኦሮሚያ ፖሊስ፣ የፌደራል ፖሊስ እና ደህንነት የተጠናከረ ጥበቃ ሲያደርጉ መቆየታቸውንም አንስተዋል።

በአቀባበል ስነስርቱ ላይ ከአራት ሚሊየን (4,000,000) #በላይ ህዝብ የተገኘ ሲሆን፥ የህዝቡን ሰላም በጠበቀ መልኩ #በሰላም መጠናቀቁን ገልጸዋል።

በአቀባበል ስነስርዓቱ ላይ የተገኙ #ወጣቶችም ከፖሊስ ጋር #ትብብር ሲያደርጉ መቆየታቸውን ያነሱት ኮሚሽነር ጀነራል ዘይኑ #ጸጥታውን ለማስከበርም በጋር ሲፈትሹ እንደነበረም ጠቅሰዋል።

በዚህም #ቄሮዎችን ያመሰገኑ ሲሆን፥ ለሌሎችም አርአያ የሚሆን ተግባር መፈጸማቸውን ጠቅሰዋል።

የአዲስ አበባ ወጣትም የአቀባበል ስነስርዓቱ መጠናቀቅን ተከትሎ ወደ ተለያዩ አካባቢዎች የሚመለሱ ወጣቶችን #ምግብና ውሃ በማዘጋጀት ግብዣ ሲያካሂድ እንደነበረ ገልጸዋል።

ኮሚሽነሩ ይህ #አንድነትን ይበልጥ የሚያጠናክርና ለሀገሪቱም ትልቅ #ተስፋ መሆኑን አንስተዋል።

አንዳንድ ቦታዎች ላይ "ወጣት ነን" የሚሉ ግለሰቦች #ድንጋይ የመወርወር አዝማሚያ ማሳየታቸውን የጠቀሱ ሲሆን፥ ፖሊስም #በቁጥጥር ስር እንዳዋላቸው ተናግረዋል።

በተመሳሳይ በአዲስ አበባ #ዙሪያ በቄሮ ስም #የሚነግዱ ቄሮ ያልሆኑ ከአቀባበል ስነ ስርዓቱ ጋር ምንም ግንኙነት የሌላቸው ግለሰቦች ዝርፊያና #ግድያ መፈጸማቸውን አንስተዋል።

በዚህም ፌደራል ፖሊስ፣ የኦሮሚያ ፖሊስ እና የሀገር መከላከያ ወደ አካባቢው በመሄድ ግለሰቦቹን በቁጥጥር ስር እያዋለ ይገኛል ብለዋል።

በጥቅሉ አቀባበሉ ኢትዮጵያዊ ጨዋነት የታየበት ጥሩ መንፈስ የነፈሰበት ህዝቡ እንግዶቹን ተቀብሎ በሰላም እንዲጠናቀቅ ያደረገበት ነው ብለዋል።

የአቀባበል ስነስርዓቱ በሰላም መጠናቀቅ ህዝቡ ላደረገው ትብብር፣ ለቄሮ እና ለአዲስ አበባ ህዝብ ምስጋና አቅርበዋል።

በአቀባበል ስነስርዓቱ ላይ የነበሩ ቄሮዎች ባሳዩት ትብብር ፖሊስ መኩራቱን ገልጸው በቀጣይም ፖሊስ ጋር በመሆን እጅና ጓንት ሆነው እንደሚሰሩ እምነታቸውን ገልፀዋል።

ምንጭ፦ ፋና ብሮድካስቲንግ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ባህር ዳር⬆️ለጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐብይ አህመድ፣ ለፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ እና ለፕሬዝዳንት ሙሀመድ አብዱላሂ ፋርማጆ በባህር ዳር ከተማ ነዋሪዎች #አንድነትን የሚገልጽ ሽልማት ተበረከተላቸው።

ምንጭ፦ አብመድ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
‹‹ወጣቶች የመልካም ተግባር አርአያ መሆን እንጂ በስሜት በመነሳሳት #አንድነትን በሚሸረሽሩ ተግባራት ላይ መሰማራትየለባቸውም!››

የትግራይ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር #ደብረጽዮን_ገብረሚካኤል

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ👆

/ሚያዚያ 23/

ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ ረቡዕ ምሽት #የTIKVAH_ETH ቤተሰብ አባላት ሲገቡ በተቋሙ ተማሪዎች እና በተማሪዎች ህብረት ልዩ አቀባበል ተደርጎላቸዋል። በፍቅር ተቀብለው አስተናግደዋቸዋል!! እራታቸውን እጉርሰው ማደሪያቸውን አመቻችተው ወንድምና እህቶቻቸውን በክብር አስተናግደዋቸዋል።

√ከደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ ጋር ቀደም ብለን በተነጋገርነው መሰረት #የStopHateSpeech መድረክን ያካተተ ሌላ ትልቅ መድረክ እያዘጋጁ ስለነበር የውይይት መድረኮች ለሌላ ጊዜ እንዲተላለፉ ሆኗል። ዩኒቨርሲቲውም በራሱ ፕሮግራም በትልቅ ዝግጅት ሊጠራ ስላሰበ የታቀዱ ስራዎች ለሌላ ጊዜ ተላልፏል።

እውነት የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ይለያሉ! #ፍቅርን#መተሳሰብን#አንድነትን ያሳዩን የቤተሰባችን አካል ናቸው። #ክብር ይገባችኃል!

@tsegabwolde @tikvahethiopia