TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
የሸካ ዞን መቀመጫ ቴፒ እንዲሆን ተወሰነ።

ጥቅምት 27/2014 ዓ.ም የሸካ ዞን ም/ቤት ባካሄደው አስቸኳይ ጉባኤ የዞኑ ዋና መቀመጫ #ቴፒ_ከተማ እንዲሆን በሙሉ ድምፅ ወሰኔ አሳልፏል።

ምክር ቤቱ ቅዳሜ ባካሄደው 9ኛ የሥራ ዘመን 4ኛ ዙር 1ኛ አስቸኳይ ጉባኤ የአሠራር ቅልጥፍናና የአገልግሎት አሰጣጥን ለማሻሻል የዞኑን ዋና ከተማ ከነበረበት ማሻ ከተማ ወደ ቴፒ ከተማ ለማዛወር የቀረበውን የውሣኔ አጀንዳ በመወያየት የዞኑ ዋና ከተማ ቴፒ እንዲሆን በሙሉ ድምፅ ወስኗል።

ውሳኔው በተሻሻለው የደ/ብ/ብ/ህ/ክልል መንግስት ህገ መንግስት አንቀፅ 81 ንኡስ አንቀፅ 2 ላይ የዞን ምክር ቤቶች በዞኑ ውስጥ የበላይ የፖለቲካ ስልጣን ባለቤቶች ናቸው ተብሎ በተገለፀው መሠረት በጉዳዩ ላይ በመወያየት ካለው ህዝባዊ ጠቀሜታ እና ፋይዳ አንጻር የዞኑ ማዕከል አሁን ካለበት ማሻ ከተማ ወደ ቴፒ ከተማ እንዲዛወር በሙሉ ድምፅ ውሳኔ መተላለፉ ተገልጿል።

መረጃው የደረሰን ከሸካ ዞን ኮሚኒኬሽን ነው።

@tikvahethiopia