TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update ልክ ጎንደር እንደተደረገው በደብረብርሃን ከተማም ክልከላዎች ተጣሉ። ደብረ ብርሃን ከተማ ውስጥ #ህጋዊ_መታወቂያ ሳይዙ መንቀሳቀስ በጥብቅ የተከለከለ ሲሆን ህጋዊ መታወቂያ ሳይዝ የተንቀሳቀሰ ግለሰብም ሆነ ቡድን በህግ ቁጥጥር ስር ይውላል ተብሏል። የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር የፀጥታ ኮማንድ ፖስት " የከተማዉን ሰላምና የህግ የበላይነት ለማረጋገጥ " እንዲቻል በሚል ክልከላዎችን መጣሉን…
#ደሴ

የአማራ ክልል ከተሞች ተመሳሳይ / #አንድአይነት ይዘት ያላቸው ክልከላዎችን እየጣሉ ይገኛሉ።

ማምሻውን የደሴ ከተማ ኮማንድ ፖስት በጎንደር እና ደብረብርሃን የተጣሉትን አይነት ተመሳሳይ ክልከላዎች መጣሉን ገልጿል።

ኮማንድ ፖስቱ የጣላቸው ክልከላዎች ከላይ ተያይዘዋል።

በሌላ በኩል ፤ የፀጥታ ኮማንድ ፖስቱ ለከተማው ነዋሪዎች ባሰራጨው መልዕክት " በከተማው እየተሰራ ያለው ልማት ለደቂቃም ሊስተጓጎል አይገባም። " ብሏል።

" ህዝባችን ሰላም ፣ ልማት እንደሚፈልግ ጠንቅቀን እንረዳለን። " ያለው ኮማንድ ፖስቱ " የደሴ ህዝብ ከእንግዳህ በሴራ እየተጎዳ መቀጠል የለበትም " ሲል ገልጿል።

" ወጣቶቻችን በሆደ ሰፊነት በትዕግስት በስክነት ነገሮች እንዲፈቱ እንደሚፈልጉና ልማቱን ምንም እንቅፋት እንዲፈጠርበት እንደማይፈልጉ ጠንቅቀን እናውቃለን " ሲል የገለፀው ኮማንድ ፖስቱ " መንግስት ህግ ለማስከበር የተደራጀ ኃይል እና ዝግጅት ቢኖረውም ከተማችን ነገሮች በሰከነ መንገድ በውይይት እንደፈቱ ከመፈለግ ታግሰናል። " ብሏል።

የፀጥታ ኮማንድ ፖስቱ " ዋናው ችግር ከሌላ ቦታ በመጡ ኃይሎች አስተባባሪነት እንጂ በከተማው ህዝብ እንዳልሆነ ህዝባችን ልብ ሊል ይገባል " ብሏል።

የደሴ ከተማ የፀጥታ ኮማንድ ፖስት " ከሌላ ቦታ መጡ " ያላቸው ኃይሎች እነማን እነድሆኑና ከየት እንደመጡ ባወጣው መግለጫ ያለው ነገር የለም / ማብራሪያም አልሰጠም።

@tikvahethiopia