TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
እየተባባሰ የመጣው የኮቪድ-19 ስርጭት ፦

ኮቪድ-19 የኒው ዮርኩን የተባበሩት መንግሥታቱን ድርጅት የሥራ እንቅስቃሴ እያስተጓጎለ ነው። የድርጅቱ ጠቅላላ ጉባዔ ፕሬዚዳንት ቮልካን ቦዚከር በካል የሚካሄዱ ስብሰባዎችን ሰርዘዋል።

ይህ የሆነው በመንግሥታቱ ድርጅት የኒዠር ሚሽን ሰራተኞች የሆኑ አምስት ሰዎች ላይ ኮሮና ቫይረስ መገኘቱን ተከትሎ ነው።

ዩናይትድ ስቴትስ ዙሪያ ባለፉት ሰባት ቀናት ብቻ አምስት መቶ ሁለት ሽህ ስምንት መቶ ሃያ ስምንት አዲስ የኮሮና ተያዦች ተመዝግቧል።

የኢሊኖይ ክፍለ ግዛት አስተዳዳሪ በተለይ የሀገሪቱ ሦስተኛዋ ትልቅ ከተማ በሆነችው በቺካጎ አዲስ ዙር የቁጥጥርና ገደብ ርምጃዎች አውጥተዋል።

በዚህም መሰረት ከፊታችን ዓርብ ጀምሮ ምግብ ቤቶችና ቡና ቤቶች ደጅ ብቻ እንጂ የቤት ውስጥ አገልግሎት እንዳይሰጡ ተከልክሏል።

የኮሎራዶዋ ዴንቨር ከተማ ዕሁድ ዕለት 327 አዲስ የቫይረሱ ተያዥች መመዝገባቸውን ተከትሎ ቀደም ሲል 50 ከመቶውን ደንበኞቻቸው እንዲያስተናግዱ ተፈቅዶላቸው የነበሩ የምግብ እና መጠጥ ቤቶች ወደ 25 ከመቶ እንዲቀንሱ የከተማዋ ከንቲባ ማዘዛቸውን #ቪኦኤ አስነብቧል።

@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
#BidenHarris

በአሜሪካ ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ ዶናልድ ትረምፕን ያሸነፉት ጆ ባይደን ከወዲሁ የአስተዳደር ርክክብ ዝግጅት ፈጥነው ጀምረዋል።

በመጪው ጥር 20 (እ.አ.አ) ቃለ መሃላ ፈጽመው ሲረከቡ ቁልፍ የሆኑ የትረምፕ ፖሊሲዎችን ይቀለብሳሉ ተብሏል።

ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትረምፕ ፥ ጆ ባይደን 'በጠባብ አጠቃላይ ድምጽ' ባሸነፉባቸው ክፍለ ግዛቶች ላይ የተፈጸሙ የድምጽ ቆጠራ መዛባቶች ሲፈተሹ ውጤቶቹ ተቀልብሰው አሸናፊ እኔ እሆናለሁ በማለት ክሶች መስርተዋል።

ተመራጩ ፕሬዚዳንት ጆ ባይደን እና ምክትላቸው ካማላ ሃሪስ ትናንት የሽግግር ዌብሳያታቸውን ከፍተዋል።

ፕሬዚዳንት ትረምፕ በምርጫው መሸነፋቸውን ለመቀበልም ሆነ ለጆ ባይደን ስልክ ደውለው ለማነጋገር ፈቃደኛ አልሆኑም ሲል #ቪኦኤ በድረገፁ አስነብቧል።

@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
አሜሪካ ስለህዳሴው ግድብ ፦

ኢትዮጵያ ፣ ግብጽ እና ሱዳን የታላቁ የኅዳሴ ግድብን (GERD) በተመለከተ ያላቸውን አለመግባባት በትብብር እና ገንቢ በሆነ ጥረት እንዲፈቱ አሜሪካ ድጋፍ መስጠቷን እንደምትቀጥል ማስታወቋን #ቪኦኤ በድረገፁ አስነብቧል።

ሦስቱ ሃገሮች ውጤታማ ወደሆነ ውይይት እንዲመለሱ እናበረታታለን ሲል የዋይት ሃውስ የብሄራዊ ጸጥታ ምክር ቤት ቃል አቀባይ ቢሮ አስታውቋል።

ውዝግቡ ገንቢ መፍትሄ እንዲያገኝ እና በክልሉ ያለው ውጥረት እንዲረግብ ለመርዳት በምንሰጠው ድጋፍ ከግድቡ ጋር የተገናኙ ጉዳዮች ሚዛናዊ በሆነ መንገድ መያዛቸውን በማረጋገጥ መስራታችንን እንቀጥላለን ብሏል መግለጫው።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
PHOTO : በኮቪድ -19 ምክንያት ለአንድ ዓመት ተራዝሞ የነበረው የቶኪዮ 2020 ኦሎምፒክ ዛሬ አነስ ባለ ነገር ግን በደማቅ የመክፈቻ ሥነ ስርዓት ተጀምሯል።

በየ4 ዓመቱ የሚካሄደው ኦሎምፒክ በዓለም አቀፍ የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ምክንያት ለአንድ ዓመት እንዲዘገይ ሆኗል።

በዛሬው በቶኪዮ ኦሊምፒክ ስቴዲየም የመክፈቻ ሥነ ስርዓት ላይ ለኮቪድ-19 ጥንቃቄ ሲባል ወደ 900 የሚሆኑ ተጋባዥ እንግዶች እና ባለሥልጣናት ብቻ በታደሙበት ነው መክፈቻው የተካሄደው።

#ቪኦኤ

Photo Credit : AP

@tikvahethiopoa
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
ሀገር መከላከያ ሰራዊት ትላንት ካማሽ ገብቷል።

የኢትዮጵያ ሀገር መከላከያ ሰራዊት ካማሽ ከተማ ሙሉ ለሙሉ መግባቱን የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ፖሊስ ም/ኮሚሽነር ኢንስፔክተር ምስጋናው እንጂፈታ አሳውቀዋል።

የኢትዮጵያ ሀገር መከላከያ ካማሽ መግባቱን ተከትሎ በአካባቢው ይሰማ የነበረው የተኩስ ልውውጥ መቆሙንና በአካባቢው የነበረውን ታጣቂ ኃይልም ማፈግፈጉን ገልፀዋል።

ኢስፔክተር ምስጋናው እንጅፈታ ለ#ቪኦኤ በሰጡት ቃል ፥ በካማሺ ዞን የሚንቀሳቀሱ እራሳቸው የቤንሻንጉል ህዝቦች ነፃነት ንቅናቄ (ቤህነን) የሚባሉ ታጣቂዎች የዞኑን በርካታ ቦታዎች ተቆጣጥረው መቆየታቸውን አስረድተዋል።

"የቤህነን ታጣቂ ከኦነግ ሸኔ ጋር ቅንጅት አላቸው፣ ከእነሱ ጋር እየተጋገዙ ነው ይህን የሚያደርጉት፣ በዞኑ 5 ወረዳ ነው ያለው ከዞን እና የወረዳ ማዕከሎች ውጪ አንድም ቀበሌ በመንግስት እጅ ላይ የለም" ሲሉ አክለዋል።

ከመንግስት እጅ በወጡ ቦታዎች በፖለቲካው እንቅስቃሴ የለም፣ ሙሉ በሙሉ ግንኙነቶችም ተቋርጠዋል በዚህ ምክንያት በዞኑ ሰብዓዊ ቀውስ ተፈጥሯል ሲሉ ገልፀዋል።

ኢንስፔክተር ምስጋናው ፥ ባለው የፀጥታ ኃይል ውስንነት የተነሳ ችግር አለባቸው ተብሎ በጥናት የተለዩ ቦታዎች በመግባት ህግ ማስከበር እንዳልተቻለ አመልክተው ፤ ከዚህ ጋር በተያያዘ ህብረተሰቡ በተጎሳቆለ ሁኔታ ውስጥ ነው ያለው ብለዋል።

ከመንግስት ቁጥጥር ውጭ በሆኑ ቦታዎች ያልተዘረፈ ከብት የለም፤ ያልተዘረፈ ንብረት የለም፣ የከፋ ሰብዓዊ ቀውስ ነው ያለው ፤ ህብረተሰቡ በረሃብ እየተጎዳ ነው፣ መድሃኒት የለም ተዘርፏል፣ ጤና ኬላዎች ግብአት አይገባላቸውም ግንኙነት የለም ተቋርጧል በዚህም ህብረተሰቡ ከፍተኛ ስቃይ ላይ መሆኑን አመልክተዋል።

ያንብቡ : telegra.ph/Benishangul-Gumuz-09-25

@tikvahethiopia
#ትኩረት_የሚሻ_የፀጥታ_ጉዳይ 📣

በደቡብ ወሎ ዞን የአርጎባ ብሄረሰብ ልዩ ወረዳ እና በአፋር ተላላክ ወረዳ በአንድ ግለሰብ ሞት ምክንያት የተቀሰቀሰ ግጭት ወደ ተኩስ ልውውጥ ተቀይሮ ለሰዎች ሞት እና መቁሰል ምክንያት ሆኗል።

አሁን ያለው የፀጥታ እጅግ ልዩ ትኩረት የሚፈልግ ነው ተብሏል።

ችግሩ የተከሰተው ባለፈው ማክሰኞ ዕለት ሲሆን አንድ የአፋር ተወላጅ አርጎባ ብሄረሰብ ልዩ ወረዳ መድና ከተማ ገበያ ውሎ ሲመለስ መሃል መንገድ ላይ ማንነታቸው ባልታወቁ ሰዎች ከተገደለ በኃላ ነው።

ባለፉት ተከታታይ ቀናት መዲናን ጨምሮ በበርካታ አካባቢዎች ላይ የተኩስ እሩምታ የሚሰማ ሲሆን የግለሰብ ቤቶችም መቃጠል መጃመራቸው ተነግሯል። እስካሁን ምን ያህል ሰው እንደተጎዳ ማወቅ አልተቻለም።

ችግሩን ለመፍታት በአፋርም አማራ ክልል በኩልም ብዙ ቢጣርም ውጤት አላመጣም ይልቅም እየባሰ ሄዷል።

በርካቶች ባለው የፀጥታ ችግር ከቄያቸው እየሸሹ መሆናቸውም ተነግሯል።

የአርጎባ ብሄረሰብ ልዩ ወረዳ ኮሚኒኬሽን ፅህፈት ቤት ኃላፊ ሰኢድ ኢብራሂም አሁን ያለው ሁኔታ ከግለሰብም አልፎ መልኩን ቀይሮ እጅግ አሰቃቂ የሆነና መጥፎ ጉዳት ሊያደርስ በሚችልበት ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ ገልፀው የክልሉ መንግስት እና የፌዴራል መንግስት መኃል ገብተው ካላስቆመው ቀጠናው በጣም አስጊ ነው ሲሉ አስገንዝበዋል።

ከአፋር ክልል ተላላክ ወረዳ ኮሚኒኬሽን ፅ/ቤት እና የአርጎባ ብሄረሰብ ልዩ ወረዳ ኮሚኒኬሽን ፅ/ቤት በኩል ለቪኦኤ ሬድዮ የሰጡት ቃሎች በዚህ ተያይዟል ያንብቡ ⬇️

https://telegra.ph/Attention-06-04-2

#አርጎባ_ብሄረሰብ_ልዩ_ወረዳ #ተላላክ_ወረዳ

#ቪኦኤ

@tikvahethiopia
#OLF

በእስር ላይ የሚገኙት የኦሮሞ ነፃነት ግንባር አመራሮች ጉዳይ ላይ ፍርድ ቤት ትዕዛዝ አስተላልፏል።

በቡራዩ እስር ላይ ካሉ 7 የኦነግ አመራሮች 4ቱ ከእስር እንዲለቀቁ የቡራዩ ወረዳ ፍ/ቤት ትዕዛዝ አስተላልፏል።

ጠበቃ አቶ ደምሴ ፍቃዱ ጉዳዩን በተመለከተ ለ #ቪኦኤ_ሬድዮ በሰጡት ቃል አራቱ የኦነግ አመራሮች አካልን ነፃ የማውጣት አቤቱታ አቅርበው እንደነበር፤ አቤቱታ የቀረበለት የቡራዩ ከተማ ፍ/ ቤት ግለሰቦቹ በማን እና ለምን እንደታሰሩ ለመረዳት ለሶስት ተከታታይ ችሎት ጥሪ ሲያቀርብ ነበር።

ነገር ግን ፖሊስ ሆነ እስረኞች አልቀረቡም። አርብ ሀምሌ 8 የኦሮሚያ ክልል ጠቅላይ አቃቤ ህግ ማብራሪያ ሠጥቷል።

ጠበቃ ደምሴ ፍቃዱ ፦

" 1ኛ አመልካች የሆነው ሚካኤል በቀለ ከዚህ ቀደም የወንጀል መዝገብ ተጣርቶበት በወንጀል አንቀፅ 42 መሰረት የተጠረጠረበት ጉዳይ ወንጀል ነው ተብሎ የሚያስከስስ ባለመሆኑ መዝገቡ ተዘግቶ ፖሊስ ከእስር ቤት እንዲለቀው ትዕዛዝ ፅፈንለት ፖሊስ ግን አለቅም ማለቱን አቃቤ ህግ ገልጿል።

2ኛ እና 3ኛ አመልካቾች ለሚ ቤኛ እና ዳዊት አብደታን በተመለከተ በተጠረጠሩበት ወንጀል ተከሰው የአቃቤ ህግ ምስክሮች ከተሰሙ በኃላ ፍርድ ቤት ጉዳዩን መርምሮ የሚያስቀጣ አይደለም በማለት በነፃ ካሰናበታቸው በኃላ ፖሊስ በራሱ ስልጣን ነው ያሰረው ሲል አቃቤ ህግ ለፍ/ ቤት አመልክቷል።

4ኛ አመልካች ገዳ ገቢሳ የተጠረጠረበት ወንጀል አቃቤ ህግ ከመረመረ በኃላ አያስከስስም ብሎ መዝገቡን ዘግቶ ከእስር እንዲለቀቅ ለፖሊስ ትዕዛዝ መስጠቱን አብራርቷል።

ከአቃቤ ህግም ምንም መዝገብ የላቸውም ሲል ነው የኦሮሚያ ጠቅላይ አቃቤ ህግ ለፍ/ ቤት ያስረዳው። "

ፍ/ቤት ሀምሌ 11 ከእስር እንዲለቀቁ የወሰነ ቢሆንን ታሳሪዎቹ እስካሁን አልተለቀቁም።

@TIKVAHETHIOPIA
በዓለም አቀፍ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ውድድር ለሩብ ፍጻሜ የደረሰው ኢትዮጵያዊው ወጣት !

አቤል ዳኜ የሠራው በሁካታ መሃል ሆኖ ድምፅን ማጥፋት የሚቻልበት የቴክኖሎጂ ፈጠራ ፅንሰ ሃሳብ የሚያስረዳው ቪዲዮ በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ መነጋገሪያ ሆኗል።

ነዋሪነቱን በአሜሪካ ያደረገው አቤል ዳኜ የ18 ዓመት ወጣት ሲሆን " ብሬክስሩ፣ ጁኒየር ቻሌንጅ " በተሰኘ የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ እና ሂሳብ ውድድር ላይ ከ2400 ሰዎች መካከል ለዕሩብ ፍጻሜ ከደረሱ 30 ሰዎች አንዱ መሆን ችሏል። 

#ቪኦኤ በሰጠው ቃል " ኮምፒውተር ሳይንስ ፍቅሬን ያዳበርኩት ከአባቴ ነው "  የሚለው አቤል የወደፊት ፍላጎቱም ትምህርቱን ጨርሶ #ኢትዮጵያን መርዳት እንደሆነ ተናግሯል።

ባለፈው ክረምትም በደብረ ማርቆስ ሀዲስ ዓለማየሁ የ2ኛ ደረጃ ት/ቤት ለሚማሩ ከመቶ በላይ ለሚሆኑ ተማሪዎች ዌብ ግንባታ ሲያስተምር ቆይቷል። 

አቤል ይህን " ብሬክስሩ " የተሰኘ ሽልማት ካሸነፈ የ250 ሺ ዶላር የነጻ የትምህርት ዕድል፣ 100 ሺ ዶላር ለተማረበት የሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት የሳይንስ ቤተ-ሙከራ ግንባታ እና እሱን ላበረታታ እና ላነቃቃ መምህር የ50 ሺ ዶላር ሽልማት የሚያገኝ ይሆናል።

ነገር ግን ይሄ ይሆን ዘንድ " ብሬክስሩ ቻሌንጅ " የፌስቡክ እና የዩቱብ ገጽ ላይ ሰዎች ላይክ፣ ኮሜንት በማድረግ እንዲያግዙት ጠይቋል።

የህዝብ ድምፅ አሰጣጡ #የመጨረሻ_ቀን ዛሬ መስከረም 10 (September 20) ነው። #አሁኑኑ በፍጥነት የሚከተሉትን 2 ቪድዮዎች  ‘Like’ አድርጋችሁ ድምፃችሁን ስጡት።

1. Facebook https://www.facebook.com/watch/?v=595860615362156
2. YouTube https://www.youtube.com/watch?v=PzTAhCHoIMQ&feature=youtu.be

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Ethiopia በአሜሪካን ዋሽንግቶን ዲሲ የሚገኙት ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ከአሜሪካ - አፍሪካ የመሪዎች ጉባኤ ጎን ለጎን ከተለያዩ ተቋማት ኃላፊዎች ጋር ተወያይተዋል። - ጠቅላይ ሚኒስትሩ ፤ ከአሜሪካ የንግድ ተወካይ አምባሳደር ካትሪን ታይን ተገናኝተው ተውያይተዋል። የሁለቱን ሀገራት የንግድ ግንኙነት ማስፋፋት በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ጥሩ ውይይት መደረጉን ገልጸዋል። - ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ IMF…
#USA #AFRICA

ለ3 ቀናት የተካሄደው የአሜሪካ-አፍሪካ የመሪዎች ጉባኤ ትናንት ሐሙስ ተጠናቋል።

የአሜሪካው ፕሬዜዳንት ጆ ባይደን በጉባኤው ምን አሉ ?

- ከሰሃራ ግርጌ ወዳሉ የአፍሪካ አገሮች በቅርቡ ጉብኝት እንደሚያደርጉ አስታውቀዋል። ከሰሃራ ግርጌ ወዳሉ የአፍሪካ አገሮች የሚያደርግት ጉብኝት እንደ ፕሬዝደንት የመጀመሪያው ነው። ቀኑን እና የትኞቹ ሀገራትን እንደሚጎበኙ ግን አላሳውቁም።

- አፍሪካ እድገት እያስመዘገበች መሆኑን ገልፀው አሜሪካ ትኩረቷን እንደምትጨምርም ጠቁመዋል።

- ከፍተኛ አማካሪዎቻቸውን ወደ አፍሪካ እንደሚልኩ ገልፀዋል። ወደ አፍሪካ ከሚላኩት ውስጥ የውጪ ጉዳይ ሚኒስትሩ አንተኒ ብሊንከን፣ የገንዘብ ሚኒስትሯ ጃነት የሊን እና የንግድ ሚኒስትሯ ጂና ሬይሞንዶ ይገኙበታል።

- በሚቀጥለው ዓመት ለሚደረጉ ምርጫዎች 165 ሚሊዮን ዶላር እንደሚመደብ ቃል ገብተዋል።

ፕሬዚደንት ባይደንና ባለቤታቸው ጂል ባይደን የአፍሪካ አገራት መሪዎችንና ቀዳማዊ እመቤቶቻቸውን በዋይት ሃውስ የእራት ግብዣ አድርገውላቸዋል።

በሌላ በኩል ፤ በአሜሪካ-አፍሪካ ጉባኤ ላይ ሊሳተፍ ወደ አሜሪካ አቅንቶ የነበረው የኢትዮጵያ ልዑክ ወደ ሀገር መመለሱን የጠ/ሚኒስትሩ የደህንነት አማካሪ አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ዛሬ አመሻሹን አሳውቀዋል።

#ቪኦኤ #አምባሳደር_ሬድዋን_ሁሴን

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Lion #Wegagen አንበሳ ኢንተርናሽናል ባንክ በሽረ እንደስላሴና አካባቢው የሚገኙት ቅርንጫፎቹ የባንክ አገልግሎት መስጠት መጀመራቸውን በዛሬው ዕለት አሳውቋል። በሌላ በኩል ፤ ወጋገን ባንክ በግጭት ምክንያት አገልግሎት ተቋርጦባቸው በቆዩት በአላማጣና በራያ ጥሙጋ ቅርንጫፎች አገልግሎት መስጠት መጀመሩን ገልጿል። ባንኩ ሰቲት ሁመራ፣ አዲ ረመፅ ፣ ዳንሻ  እና ተከዜ ቅርንጫፎች ቀደም ብለው አገልግሎት…
ወጋገን ባንክ ትላንት በመቐለ በ28 ቅርንጫፎች ስራ ጀምሯል።

ባንኩ መስጠት የጀመረው አገልግሎት ከባንክ ሂሳብ ገንዘብ ማውጣት እና ማስገባት ከክልሉ ውጭ የተላከ ገንዘብ መቀበል ናቸው።

የባንኩ የመቐለ ዲስትሪክት ስራ አስኪያጅ አቶ ሃፍቶም ገ/እግዚአብሔር ለቪኦኤ የሰጡት ቃል ፦

" ከፌዴራል ሲስተም ጋር በማያያዝ ማንኛውም ተቀማጭ የነበረውን ደንበኛ ገንዘብ መውሰድ ይችላል በቀን እስከ 1,500 ብር ይሄንን ስንል ከአዲስ አበባ ከሌላም ቦታ በተለይ ከትግራይ ክልል ውጭ ያለው ማንኛውም ገቢ ያደረገ ወደ ሂሳብ እሱን እያየን መክፈል እንችላለን። ከዚህ በተጨማሪ የውጭ ሀዋላም ጀምረናል።

መቐለ የጀመርነው በ28 ቅርንጫፎቻችን ነው፤ ብሩ በጣም ትንሽ ነው፤ ሰጠን ብለንም አናስብም ዞሮ ዞሮ ግን ያሉንን ደንበኞችና ድርጅቶች እነሱን በማስተባበር የተወሰነ ገቢ ስላደረጉልን ይሄንን ገቢ በዓልም ከፊታችን ስላለ ህዝባችን የነበረውን ችግር በመጠኑ በጣም በትንሹ እንኳን ለበዓል ለዶሮም ይሁን፣ ለስጋ ይጠቅማል ከሚለው እሳቤ ስለሆነ ነው ይበቃል የሚል እምነት ግን የለንም።

ከፌዴራል ብር እየጠየቅን ስለሆነ ሲመጣ ህዝባችንን እንክሳለን።

...አሁን ከሂሳብ ወደ ሂሳብ እሱን እያስተካከልን ነው በዚህ ሁለት ቀን እጀምራለን። በቀጣይ የATM እና ሞባይል ባንኪንግና ኢንተርኔት ባንኪንግ እሱን እየጨረስን ነው ከዚህ በፊት ጉዳት የደረሰባቸውን ኤቲኤሞች የእየተካን ነው፤ በቅርብ ጊዜ ሙሉ በሙሉ የATM አገልግሎት እንጀምራለን።"

ወጋገን ባንክ ከመቐለ በተጨማሪ ከዛሬ ጀምሮ ኦዲተሮቹን፣ እቃዎቹን እስከ ዓዲግራት ባለው አካባቢ፤ በሌላው መስመር እስከ መኸኒና ዓብይ ዓዲ ያሉት ቅርንጫፎቹ እንደሚያደርስ ገልጿል። በሁለትና ሶስት ቀን ውስጥ የቀሩት ቅርንጫፎች ስራ እንደሚጀምሩ አሳውቋል።

#ቪኦኤ

@tikvahethiopia
ከዘር ማጥፋት እልቂት ለማምለጥ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ የተሸሸጉ 2 ሺህ ቱትሲዎች እንዲገደሉ ትዕዛዝ በመስጠት የተጠረጠረው ግለሰብ ተያዘ።

እ.አ.አ በ1994 በሩዋንዳ በነበረው የዘር ማጥፋት እልቂት፣ ከጥቃት ለማምለጥ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ የተሸሸጉ ሁለት ሺሕ #ቱትሲዎች እንዲገደሉ ትዕዛዝ አስተላልፏል በሚል የተጠረጠረው ግለሰብ ደቡብ አፍሪካ ውስጥ መያዙን የሩዋንዳውን የዘር ማጥፋት የሚከታተለው፣ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የጦር ወንጀል ችሎት አስታውቋል።

የቀድሞው የፖሊስ አባል፣ ፉልጌንሴ ካይሼማ፣ ፍ/ቤቱ በይፋ ክሥ ከመሠረተበት ካለፉት 22 ዓመታት ጀምሮ በሽሽት ላይ ነበር።

በተመድ የተቋቋመው ችሎት፣ ሥራውን ለሩዋንዳ በማስረከቡ፣ ካይሼማ፥ ለሩዋንዳ ተላልፎ እንደሚሰጥ የሮይተርስ ዘገባ አመልክቷል።

የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ ካይሼማ ያለበትን ለሚጠቁም፣ የአምስት ሚሊዮን ዶላር ጉርሻ እንደሚሰጥ አስታውቆ ነበር።

ሌላው የዘር ማጥፋቱ ጠንሳሽ የተባለው ፌሊሲን ካቡጋ፣ ከ26 ዓመታት ሽሽት በኋላ ከሦስት ዓመት በፊት በፈረንሳይ ውስጥ መያዙ ይታወቃል።

እ.አ.አ በ1994 በሩዋንዳ፣ በአክራሪ ሁቱዎች በተፈጸመ የዘር ማጥፋት፣ 800ሺሕ የሚሆኑ ቱትሲዎች መገደላቸው ይታወሳል።

#ቪኦኤ #ሩዋንዳ #Genocide

@tikvahethiopia
#ኤርትራ #ሩስያ

የሩሲያ ፕሬዚደንት ቭላዲሚር ፑቲን #የኤርትራ ፕሬዚደንት ኢሳይያስ አፈወርቂን በክሬምሊን ቤተ መንግሥት ተቀብለው አነጋገሩ።

የኤርትራ የማስታወቂያ ሚንስትር የማነ ገብረ መስቀል በትዊተር ገጻቸው ባወጡት ቃል ፤ ፕሬዚደንት ኢሳይያስ እና ፕሬዚደንት ፑቲን ዛሬ ረቡዕ ከቀትር በኋላ ባደረጉት ቆይታ የአገሮቻቸውን የሁለትዮሽ ግንኙነት፤ ዐለም አቀፍ ጉዳዮች እንዲሁም በጋራ ትኩረት በሚሰጧቸው ሁኔታዎች ዙሪያ በስፋት መወያየታቸውን አስታውቀዋል፡፡

አያያዘውም ፤ “የኤርትራ ፕሬዚደንት ኢሳይያስ በሩሲያ ፌዴሬሽን ያደረጉት #የመጀመሪያ ጉብኝት ለሁለቱ ሀገሮች ግንኙነት ትልቅ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ፕሬዚደንት ፑቲን አስምረውበታል” ብለዋል፡፡

“የሁለቱ ሀገሮች ግንኙነት ርምጃ ሙሉ በሙሉ አመርቂ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ” ፑቲን መናገራቸው አክለው “በመጪው ሐምሌ ወር ሞስኮ በምታስተናግደው ሁለተኛው የሩሲያ እና የአፍሪካ የመሪዎች ጉባዔ ላይ እንዲገኙ ጋብዘዋቸዋል” ብለዋል፡፡

የኤርትራ ፕሬዚደንት በበኩላቸው ጉብኝታቸው የሁለቱን ሀገሮች ከፍተኛ የአጋርነት እና የምክክር ግንኙነት የሚያንጸባርቅ መሆኑን መናገራቸውን የማስታወቂያ ሚኒስትሩ የማነ ገብረ መስቀል አመልክተዋል፡፡

#ቪኦኤ
ፎቶ፦ የማነ ገ/መስቀል

@tikvahethiopia
" በየትኛውም ዓለም ፤ በየትኛውም ሀገር ዋነኛው ቀጣሪ የግሉ ዘርፍ ነው " - አቶ ንጉሱ ጥላሁን

በአፍሪካ ሀገራት የስራ እድል ፈጠራዎች ላይ ባሉ ፈተናዎች እና ምቹ ሁኔታዎች ላይ የሚመክር የስራ ፈጠራ ማድረክ በአ/አ አፍሪካ ህብረት ግቢ ውስጥ ተጀምሯል።

ትላንት በነበረው መድረክ ላይ የተሳተፉት የስራ እና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ንጉሱ ጥላሁን ፤ በኢትዮጵያ ውስጥ በየአመቱ 2 ሚሊዮን አዳዲስ ስራ ፈላጊዎች እየተፈጠሩ ነው ብለዋል።

ለስራ ፈላጊ ዜጎች በተለያየ የስራ ዘርፍ ስራ ለመፍጠር ጥረት እየተደረገ እንደሚገኝ በውጭ ሀገርም ትልቅ እድል እንዳለ አሳውቀዋል።

አቶ ንጉሱ ፤ " በየአመቱ በእቅድ ተይዞ ነው የሚሰራው።

ለምሳሌ በ2015 በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ለ100 ሺህ ዜጎች በውጭው አለም ለመፍጠር ነው የታቀደው፤ ከዙህ ውስጥ 85 በመቶ በቤት ውስጥ ስራ 15 በመቶ skilled የሰለጠነና በከፊል የሰለጠነ ነው። እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ የዓመቱን ማጠቃለያ እንገመግማለን የአመቱን እቅድ እንደምናሳካ መረጃዎች ያሳያሉ።

ከዛ ባሻገር በውጭ ሀገር ገበያ በርካታ ፍላጎት አለ፤ 2 ሚሊዮን ያህል የስራ ገበያ ፍላጎት አለ።

በአንዳንድ ሀገራት ተወዳዳሪ ሆነን እስከተገኘን ድረስ ዋናው ብቃት ያለው ሰው ፣ ታታሪ ፣ ታማኝ ፣ ምርታማ የሆነ ፣ ስነምግባር ያለው ፤ ብቃት ያለው ተወዳዳሪ የሆነ ሰው ማዘጋጀት ከቻልን ሰፊ እድል አለ " ብለዋል።

በሌላ በኩል ፤ በአዲሱ በጀት ዓመት የመንግሥት አዲስ ሰራተኞች የስራ ቅጥር እንደሌለ በገንዘብ ሚኒስቴር ይፋ የተደረገውን ውሳኔ በተመለከተ አቶ ንጉሱ ተጠይቀው ማብራሪያ ሰጥተዋል።

አቶ ንጉሱ ፤ ስራ መፍጠር ያለበት መንግሥት ብቻ ነው የሚለው የቆየ አስተሳሰብ መቀየር አለበት ብለዋል።

" እኔ ምረዳው እውነታውም ጭምር መንግሥት ዋነኛ ስራ ቀጣሪ አይደለም። በየትኛውም ዓለም ፤ በየትኛውም ሀገር ዋነኛው ቀጣሪ የግሉ ዘርፍ ነው። መንግሥት የግሉ ዘርፍ ሁኔታዎችን እንዲመቻቹለት ማድረግ ነው የሚጠበቅበት ፤ ይሄንን የስራ እድል ለመፍጠር የማያስችሉ ፖሊሲዎች ፣ መመሪያዎችን አሰራሮችን ማውጣት ፣ የገንዘብ አቅርቦት እንዲሟላ ማድረግ ፣ የቴክኖሎጂ ትስስር ሽግግር እንዲኖር ማድረግ ፣ መሰረተ ልማት ማሟላት ፣ የገበያ ትስስር እንዲኖር ማድረግ የመንግስት ድርሻ ነው " ሲሉ አቶ ንጉሱ ጥላሁን ተናግረዋል።

" እነዚህ ሁሉ የተሟሉ ሲሆኑ ፤ አገልግሎት ሲሟላ የግሉ ዘርፍ ይስፋፋል ያድጋል ፣ ኢንቨስትመንት ይሰፋል በዚህ ምክንያት የስራ እድል ይፈጠራል መንግሥት ሁሉንም ጀምሮ የሚጨርስ አይደለም። ዘንድሮ 3.1 ሚሊዮን የስራ እድሎች ተፈጥረዋል እስካሁን ከዚህ ውስጥ በመንግሥት መ/ቤቶች እና ተቋማት የተቀጠረው በጣም ዝቅተኛ ነው ከ3.1 ሚሊዮኑ መቶ ሺህ የማይሞላ ወደ 92 ሺህ ያህል ነው ከወረዳ እስከ ፌዴራል ድረስ ያለው ፤ በመንግሥት የስራ ዘርፍ ያሉት እድሎች ውስን ናቸው ጥቂቶች የሚገቡባቸው ናቸው ፤ ይልቁንም መንግሥት ማድረግ ያለበት ምቹ ሁኔታዎችን ፈጥሮ በርካታ ዜጎች የስራ እድል እንዲፈጠርላቸው የሚያስችሉ ኢንተርፕራይዞች እንዲሰፉና እንዲያድጉ ማድረግ ነው " ብለዋል።

አቶ ንጉሱ ፤ " በባለፈው ዓመት ከለየነው 6 ሚሊዮን የስራ ፈላጊ ፤ ወደ 650 ሺህ አካባቢው ምሩቅ ነው ፤ ይሄንን ምሩቅ ከቴክኒክና ሙያ እና ከዩኒቨርሲቲ የተመረቀ መንግሥት ሁሉም ቦታ ላይ አስገባዋለሁ ቢል ቦታው የለውም ፤ ይሄን ሁሉ ምሩቅ እና ስራ ፈላጊ መንግሥት ማድረግ ያለበት አሰልጥኖ አብቅቶ የገንዘብ አቅርቦት አመቻችቶ የስራ ቦታ አመቻችቶ የስራ ባለቤት እንዲሆኑ ማድረግ ይጠበቅበታል። " ሲሉ ተደምጠዋል። #ቪኦኤ

@tikvahethiopia