TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#BREAKING

ዶ/ር ኢ/ር ስለሺ በቀለ ፦

"ዛሬ ሀምሌ 12ቀን 2013 ዓ/ም የሁለተኛውን አመት የህዳሴ ግድብ ሙሌት ተገባዶ ውሃው በግድቡ አናት ላይ ፈሶአል። ኢትዮጵያውያን እና የኢትዮጵያ ወዳጆችም እንኩዋን ደስ አላችሁ: ይህ ውጤት ማለት 2 ተርባይኖችን ለማንቀሳቀስ የሚያስፈልገውን የውሃ መጠን ማለት ነው።

በዘንድሮው አመት እየዘነበ ያለው ውሃ መጠን እጅግ ከፍተኛ ነው። ይህም ከፈጣሪ የተሰጠን ፀጋ ምን ያህል ትልቅ እንደህነና እንዴት እያገዘን እንደህነ መረዳት እንችላለን። ለዚሁም ምስጋና ይግባው።

እዚህ ደረጃ ለመድረስ በዘንድሮው አመት መጠነ ሰፊ ስራ ሰርተናል:: በቀጣይ ሁለቱ ተርባይኖች እንዲያመነጩ ብርቱ ስራዎች እየተሰሩ ነው እናም ያንን በቅርብ ወራት በማጠናቀቅ ልፋታችንን ውውጤት ላይ እናደርሳለን።"

@tikvahethiopia
#BREAKING

የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ሁለተኛው ዙር ውሃ ሙሌት ተጠናቋል።

Photo Credit : ዶ/ር ኢ/ር ስለሺ በቀለ

@tikvahethiopia
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
#ItsMyDam🇪🇹

የውሃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስትር ዶ/ር ኢ/ር ስለሺ በቀለ ያስተላለፉት የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት እና ስለሁለተኛው የግድቡ ሙሌት ለብሄራዊ ቴሌቪዥን (ኢቲቪ) የሰጡት ሙያዊ ማብራሪያ

Video : 133 MB (WIFI እንድትጠቀሙ እንመክራለን)

@tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#ItsMyDam🇪🇹

ታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በሁለተኛው ዙር የውሃ ሙሊት የመጀመሪያውን ሃይል ለማመንጨት የሚያስችለውን ውሃ ይዟል፡፡

ዛሬ ሃምሌ 12/ 2013 የውሃ ሙሊቱ ተጠናቆ ከግድቡ አናት ውሃው መፍሰስ ጀምሯል።

ሁለተኛው ዙር የውሃ ሙሊት በያዝነው ሀምሌና ነሃሴ ወር ላይ ለማድረግ ታቅዶ የነበረ ቢሆንም የዝናቡ መጠን ከፍተኛ በመሆኑ ከታሰበው ጊዜ ቀድሞ ውሃው ሊሞላ ችሏል።

በአመቱ የተከናወኑ ተግባራት የሁለተኛውን ዙር የውሃ ሙሊት ስኬታማ እንዲሆን እንዳስቻለው የውሃ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስትሩ ዶ/ር ኢ/ር ስለሺ በቀለ በስፍራው ተገኝተው ተናግረዋል።

22 በሮች እና ትራሽ ክሊነሮች ፤ የስዊች ያርድ ፤ እንዲሁም የትራንስፎርመር ገጠማ ስራዎች ተሰርተዋል ብለዋል ሚንስትሩ። አሁን ደግሞ የተርባይነሮች ገጠማ ስራ እየተካሄደ ይገኛል ብለዋል።

ዶ/ር ኢ/ር ስለሺ ፥ "በተለይ ዘንድሮ ግድቡን ለመገንባት የተኬደበት ፍጥንት የሚደነቅ ነው" ያሉ ሲሆን በቀጣይ ግድቡ እስኪጠናቀቅ በዚሁ ትጋት ስራው እንደሚቀጥልም አስታውቀዋል፡፡ ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብም እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል።

ምንጭ፦ የውሃ ፣ መስኖ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር

@tikvahethiopia
ነገ የሚዘጉ መንገዶች !

1,442ኛው ኢድ-አል አድሐ (አረፋ) በዓል በሰላም እንዲጠናቀቅ አስፈላጊውን ዝግጀት አጠናቆ ወደ ስራ መግባቱን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል።

በአዲስ አበባ ስታዲዮም በሚኖረው የጠዋት ስግደት ምክንያት ከማለዳው 11 ሰዓት ጀምሮ የስግደቱ ሥነ-ሥርዓት ተጀምሮ እስከሚጠናቀቅ ድረስ የተወሰኑ መንገዶች ለጊዜዉ ለትራፊክ ዝግ ይሆናሉ።

በዚህም መሰረት ፦

• ከመገናኛ እና ከ22 ለሚመጡ ኡራኤል አደባባይ
• ከቦሌ ወደ መስቀል አደባባይ ኦሎምፒያ
• ከሪቼ ወደ መስቀል አደባባይ የቀድሞ 4ኛ ክፍለ ጦር
• ከጦር ኃይሎች ወደ ስታዲዮም ሜክሲኮ አደባባይ
• ከመርካቶ በበርበሬ በረንዳ በተክለ ሐይማኖት ወደ ስታዲዩም ለሚመጡ ጥቁር አንበሳ ሼል ድሬንስ
•ከሞላ ማሩ በጌጃ ሰፈር ወደ ስታዲዩም ለሚመጡ ጎማ ቁጠባ
• ከፒያሳ ወደ ስታዲዮም ለሚመጡ ቴዎድሮስ አደባባይ
• ከ4ኪሎ በፊት በር ወደ መስቀል አደባባይ ጊቢ ገብርኤል
የሚወስዱ እና በተጠቀሱት አካባቢዎች የሚገኙ መጋቢ የውስጥ ለውስጥ መንገዶች ለተሽከርካሪ ዝግ ይሆናሉ።

ፖሊስ አሽከርካሪዎች አማራጭ መንገዶችን በመጠቀም ትብብር እንዲያደርጉ የጠየቀ ሲሆን በተጠቀሱት መንገዶች ላይ ለአጭርም ሆነ ለረጅም ሰዓት ተሸከርካሪን አቁሞ መሔድ የተከለከለ መሆኑን አሳስቧል።

@tikvahethiopia
#ETHIOPIA

'በ24 ሰዓት የኮቪድ- 19 ሞት አልተመዘገበም'

ኢትዮጵያ ባለፉት 24 ሰዓት 3,447 የኮቪድ-19 ላብራቶሪ ምርመራ ያከናወነች ሲሆን 84 ሰዎች ለቫይረሱ ተጋላጭ ሆነው ተግኝተዋል፤ ህይወቱ ያለፈ ሰው የለም፤ 143 ሰዎች ከበሽታው አገግመዋል።

@tikvahethiopia
እንኳን አደረሰን ፤ እንኳን አደረሳችሁ !

ለመላው እስልምና ዕምነት ተከታዮች እንኳን ለ1442ኛው ዓመተ ሒጅራ የዒድ አል-አድሐ (ዐረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ፣ አደረሰን።

በዓሉ የሰላም፣ የአንድነት፣ የመተሰሳሰብ ይሆን ዘንድ ከልብ እንመኛለን።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#BREAKING ዶ/ር ኢ/ር ስለሺ በቀለ ፦ "ዛሬ ሀምሌ 12ቀን 2013 ዓ/ም የሁለተኛውን አመት የህዳሴ ግድብ ሙሌት ተገባዶ ውሃው በግድቡ አናት ላይ ፈሶአል። ኢትዮጵያውያን እና የኢትዮጵያ ወዳጆችም እንኩዋን ደስ አላችሁ: ይህ ውጤት ማለት 2 ተርባይኖችን ለማንቀሳቀስ የሚያስፈልገውን የውሃ መጠን ማለት ነው። በዘንድሮው አመት እየዘነበ ያለው ውሃ መጠን እጅግ ከፍተኛ ነው። ይህም ከፈጣሪ የተሰጠን…
#SUDAN #EGYPT #GERD

ዶ/ር ኢ/ር ስለሺ በቀለ ፦

"... ሁሉ ነገሩ ፊዚክስ ነው፤ ውሃ ይገባል ይጠራቀማል ሲሞላ መያዝ የሚችለውን ያህል በአናቱ ይፈሳል ከዚህ የተለየ ነገር የለውም። ኒውክሌር ፊሲክስ አይደለም፤ ኖርማል ፊዚክስ ነው ፤ ይህንን ማየት ይቻላል።

ሁሉ ጊዜም እኛ ትክክለኛ ሳይንስ እና ያንን መሰረት ያደረገ ፖሊሲ ይዘን ነው የምንክተለው፤ ይህንኑ ነው በድርድሩ ወቅት ለማስረዳት የሞከርነው።

ነገር ግን ይህንን አልምተን የመጠቀም የኛ የኢትዮጵያውያን ሙሉ መብት ነው፤ ይህን እንድሄድበታለን፤ አስፈላጊ የሆነውን ክርክር እንቀጥልበታለን ክርክር የሚያስፈልግ ከሆነ። ነገር ግን ምንም አይነት መጥፎ እና በጎ ያልሆነ ተፅእኖ ስለማያሳድር ይልቅ ተባብረን ቶሎ ግድቡ የሚያልቅበትን ፣ ኔጌቲቭ ተፅእኖዎች በየማያስፈልግ ቦታ ሄደን ክርክር ከመግጠም ይልቅ እዚሁ አንድ ላይ አፍሪካ ውስጥ ቁጭ ብለን ሶስት ወንድማማች/እህትማማች ሀገሮች ተነጋግረን የሚገጥሙንን ችግሮች በጋራ እየፈታን ይልቅ ሪጅናችንን አስተሳስረን፣ እንዴት አድርገን በኢኮኖሚ ብልፅግና ማምጣት እንችላለን የሚሉት ነገሮች ላይ ትኩረት ሰጥተን መስራት ነው የሚያስፈልገን፤ ያ ነው የሚያዋጣው።

ዓለም ተመንጥቆ ሄዶ ይኸው ማርስና ሌሎች ፕላኔቶች ላይ ለማረፍ ይጥራሉ ፤ በቅርቡ ሰዎች ተመንጥቀው ሄደው ተመልሰው ያርፋሉ እኛ ግን ግድብ ስለሰራን እንደአዲስ ነገር አምጥተን ህዝባችንን ማስጨነቅ ፣ ተገቢ ባልሆኑና ፖለቲካዊ በሚመስሉ ንግግሮች ተጠምደን #መመቀኛኘት አይኖርብንም።

መተጋገዝ ፣ አብሮ ማደግ ለአፍሪካውያኖች በጣም አስገላጊ ነው፤ እኛ ይሄን ይዘን ነው የምንቀጥለው"

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ነገ የሚዘጉ መንገዶች ! 1,442ኛው ኢድ-አል አድሐ (አረፋ) በዓል በሰላም እንዲጠናቀቅ አስፈላጊውን ዝግጀት አጠናቆ ወደ ስራ መግባቱን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል። በአዲስ አበባ ስታዲዮም በሚኖረው የጠዋት ስግደት ምክንያት ከማለዳው 11 ሰዓት ጀምሮ የስግደቱ ሥነ-ሥርዓት ተጀምሮ እስከሚጠናቀቅ ድረስ የተወሰኑ መንገዶች ለጊዜዉ ለትራፊክ ዝግ ይሆናሉ። በዚህም መሰረት ፦ • ከመገናኛ እና…
የፖሊስ ሪፖርት :

ዛሬ ሐምሌ 13 በርካታ የእስልምና እምነት ተከታዮች በተገኙበት በአዲስ አበባ ስታዲዮምና በዙሪያው በሚገኙ ጎዳናዎች እንዲሁም በከተማው ልዩ ልዩ ስፍራዎች የተካሄደው የ1442ኛው የኢድ አል አድሃ የሶላት ስነ-ስርዓት በሰላም መጠናቀቁን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል፡፡

የአዲስ አበባ ፖሊስ ፣ የፌዴራል ፖሊስ እንዲሁም ሌሎች አጋዥ አካላት፣ መላው የከተማው ነዋሪ እና ሙስሊሙ ማህበረሰብ ከፀጥታ አካላት ጎን በመቆም ተገቢውን ትብብር በማድረጋቸው የሶላት ስነ-ስርዓቱ በሰላም ተጠናቋል፡፡

ለስነ ስርዓቱ በስኬት መጠናቀቅ ድጋፍ ላደረጉ ሁሉ ምስጋና ቀርቧል።

@tikvahethiopia
እንኳን አደረሰን ፤ አደረሳችሁ !

1442ኛው የኢድ አል አደሃ (ዐረፋ) በዓል በሀገራችን ዋና ከተማ አዲስ አበባ ጨምሮ በሀገራችን የተለያዩ ከተሞች በድምቀት በመከበር ላይ ይገኛል።

በተለያዩ ከተሞች ያለውን የበዓል አከባበር ድባብ የሚያሳዩ ፎቶዎችን በ @tikvahethmagazine መመልከት ይቻላል።

በዓሉ የሰላም፣ የአንድነት፣ የፍቅር፣ ለተቸገሩ ወገኖቻችን የምንደርስበት ይሆንልን ዘንድ እንመኛለን።

@tikvahethiopia