TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ጭልጋ

በማዕከላዊ ጎንደር ዞን የተቋቋመው ኮማንድ ፖስት ከጭልጋ ከተማ እና አካባቢው ተፈጥሮ የነበረው የሰላም ችግር እየተሻሻለ መምጣቱን አስታውቋል።

ኮማንድ ፖስቱ ከጭልጋ እና አካባቢው አስር ቀበሌ ከሃይማኖት አባቶች ፣ ከሃገር ሽማግሌዎች፣ ወጣቶች፣ ከወረዳና ቀበሌ አመራሮች ጋር ውይይት ማድረጉ ሪፖርት ተደርጓል።

የማዕከላዊ ጎንደር ዞን ኮማንድ ፖስት አመራር ሌ/ጀ ይመር መኮነን ፤ ማዕከላዊ ጎንደር ዞንን የሽብርተኞች አደባባይ በማድረግ የሀገርን ሰላም ለማሳጣት የሚንቀሳቀሱ የፀረ-ሰላም ሃይሎች ላይ እርምጃ እተወሰደ ይገኛል ብለዋል።

አክለውም ፥ በኮማንድ ፖስቱ እንዲሁም በህብረተሰቡ የጠነከረ ቅንጅት በየጊዜው መሻሻሎች እየተመዘገቡ እንደመጡም ገልፀዋል።

የ33ኛ ክ/ጦር አዛዥ ኮ/ል ደስታ ተመስገን በበኩላቸው የተመዘገበውን ማህበራዊ እንቅስቃሴ እና ሰላም በቀጣይነት ለማረጋገጥ ህብረተሰብ እና የፀጥታ አካላት ይበልጥ ተባብረው መስራት አለባቸው ሲሉ አስገንዝበዋል።

የሃይማኖት አባቶች እንዲሁም የሃገር ሽማግሌዎች ሰላምን ለበጠበቅ ከምንጊዜውም በላይ መዘጋጀታቸውን እና በህዝብ ውስጥ ሰላማዊ ሰው በመምሰል ሃሰተኛ መረጃዎችን በማሰራጨት ለግጭት የሚዳርጉ ወንጀለኞችን በመጠቆም ከኮማንድ ፖስቱ ጋር እንደሚሰሩ ቃል መግባታቸው ተነግሯል።

ምንጭ፦ የሀገር መከላከያ ሰራዊት

@tikvahethiopia
#Update

“የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ መንግሥት ሰኔ 21/2021 ዓ.ም. የወሰደው ‘በሰብዓዊ ምክንያት ተኩስ የማቆም አዋጅ’ ትግራይ ውስጥ ላለውን ግጭት መፍትኄ ለማግኘት ትክክለኛ እርምጃ በመሆኑ እንደግፈዋለን” ሲሉ የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር ሙሳ ፋኪ ማሃማት ባወጡት መግለጫ አስታውቀዋል።

ትግራይ ውስጥ ዘላቂ ሰላም እንዲገኝ መንገድ ለመጥረግ እንዲቻልም የኢትዮጵያ ባለሥልጣናት አጠቃላይና ሁሉን አቀፍ የሆነ ቋሚ ተኩስ ማቆም ላይ እንዲደረስ እንዲሠሩ የኅብረቱ ሊቀ መንበር ጠይቀዋል።

ለዚህም ሁሉም ዓይነት የግጭት ሁኔታዎች እንዲቆሙ ፤ በዓለም አቀፍ ህግ መሠረት ሲቪሎችን ከአደጋ ለመጠበቅ እና ክልሉ ውስጥ ለተጎዱት ሁሉ እጅግ አስፈላጊ አገልግሎቶችን የሚያቀርቡ የሰብዓዊ እርዳታ ተዋናዮች ደኅንነቱ የተረጋገጠ ተደራሽነት እንዲኖራቸው ለማስቻል ሁሉም ወገኖች ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ ጥሪ አድርገዋል።

ለትግራይ ክልል ግጭት የፖለቲካ መፍትኄ እንዲፈለግም ሊቀ መንበሩ በተጨማሪ መጠየቃቸውንና በሃገሪቱ ውስጥ ሰላምና መረጋጋት እንዲሰፍን ሁሉንም ኢትዮጵያዊ ጥረቶች የአፍሪካ ኅብረት ድጋፉን ለመስጠት ያለውን ያልተቋረጠ ዝግጁነት ማሳወቃቸውን ከፅ/ ቤታቸው የወጣው መግለጫ ይጠቁማል። (VOA)

@tikvahethiopia
#Update

የኢትዮጵያ የፌዴራሉ መንግስት ካወጀው የተናጠል ሰብዓዊነት ላይ የተመሰረተ ተኩስ አቁም ጋር ተያይዞ የሚወጡት መግለጫዎች ቀጥለዋል።

በተለያዩ ወቅት በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር እና ከፍተኛ ዲፕሎማት ሆነው ያገለገሉት ፦
- ዴቪድ ሺና፣
- ቪኪ ሐድልስተን፣
- ፓትሪሺያ ሃስላች፣
- ኦውሪሊያ ብራለዚል
- ቲቦር ናዥ የተኩስ አቁም ውሳኔውን ተከትሎ መግለጫ አውጥተዋል።

በትግራይ ክልል የነበረውን ሁኔታ በቅርበት ሲከታተሉ መቆየታቸውን ገልጸው የፌደራሉ መንግሥት የሰላም አማራጭ ማቅረቡ "ትልቅ እፎይታን ፈጥሮልናል" ብለዋል።

አምባሳደሮቹ ይህ መልካም አጋጣሚ መታለፍ የለበትም ያሉ ሲሆን በግጭቱ ተሳታፊ የሆኑ አካላት በሙሉ በመንግሥት የቀረበውን ጥሪ እንዲቀበሉ አሳስበዋል።

የሰብዓዊ እርዳታ የሚያስፈልጋቸው ስፍራዎች በበጎ አድራጊ ተቋማት ተደራሽ እንዲሆኑ፣ በትግራይ ያሉ የውጭ ኃይሎች ከግጭቱ ክልል ለቀው እንዲወጡ እና የግጭቱ ተሳታፊዎች ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን እንዲሁም በትግራይ ቀጣይ ሁኔታ ላይ ከስምምነት ለመድረስ ውይይትና ድርድር እንዲያደርጉ ጥሪ ማቀረባቸውን ቢቢሲ በድረገፁ አስነብቧል።

@tikvahethiopia
#Update

ዛሬ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴርና ሀገር መከላከያ ሰራዊት በጋራ መግለጫ ሰጥተዋል።

በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በኩል አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ፤ በመከላከያ በኩል ሌ/ጄነራል ባጫ ደበሌ ናቸው መግለጫውን የሰጡት።

ምን አሉ ?

አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ፦

- የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ከመቐለ ለቆ በመውጣቱን ገልፀዋል። "እንደምንወጣ ከሳምንታት በፊት የነገርናቸው የውጭ ተቋማት ነበሩ ብለዋል።

- በሁሉም አቅጣጫ ማለትም በሱዳን ፣ ኤርትራ አፋር እና አማራ ወሰን ዝግ መሆኑን ገልፀዋል።

- የፌዴራል መንግስት ከዚህ በኋላ በትግራይ ክልል ዙሪያ ለሚኖር ችግር ተጠያቂ እንደማይሆን ተናግረዋል፡፡

- ዓለም አቀፍ ተቋማት ፥ “ከዚህ በኋላ ዕርዳታ ደረሰ አልደረሰ ብለው የፌዴራል መንግስትን ሊጠይቁ” እንደማይገባ ገልፀዋል፤ የትግራይ ክልልን በተመለከተ ሙሉ ኃላፊነቱን አሸባሪ ተብሎ የተፈረጀው "ህወሃት" እንደሚወሰድ አሳውቀዋል።

- በትግራይ ክልል የተከሰተው ግጭት ኢትዮጵያን ለከፍተኛ ኪሳራ እንደዳረጋት ገልጸዋል፤ በልማት ሂደቱ ላይም ከፍተኛ ተጽዕኖ እንዳሳደረ ተናግረዋል፡፡

- ሕወሃት የሀገርን ሉዓላዊነት አደጋ ላይ እንደጣለ ተናግረዋል፤ ሱዳን የኢትዮጵያን ሉኣላዊ ድንበር ጥሳ እንድትገባ አጋልጦ እንደነበርም ገልፀዋል።

- 8 ወራት ብቻ የጦር ወጪን ሳይጨምር የፌደራሉ መንግሥት ከ100 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ ማደረጉን ገልጸዋል።

ያንብቡ : telegra.ph/Tigray-Update-06-30

@tikvahethiopia
#Tigray

በትግራይ በሚገኙት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ልጆቻቸውን ልከው የሚያስተምሩ ወላጆች ሙሉ በሙሉ ኔትዎርክ በመቋጠረጡ ልጆቻቸው ያሉበትን ሁኔታ ማወቅ እንዳልቻሉ ገልፀዋል።

የኢትዮጵያ ፌዴራል መንግስት ተማሪዎች ስላሉበት ሁኔታም በአስቸኳይ ማብራሪያ እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል።

በዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ልጃቸውን ልከው የሚያስተምሩ የቲክቫህ አባል፥ ስላልጃቸው ደህንነት ማወቅ ባለመቻላቸው በከፍተኛ ሁኔታ እሳቸውን ጨምሮ መላ ቤተሰቡ ጭንቀት ላይ እንደሚገኝ ገልፀዋል።

ተቋማቱን አምነው ጥሪ ሲቀርብ ልጃቸውን እንደላኩ የገለፁት አባላችን ተቋማቱን የሚይመራው አካል እስካሁን ግንፅ ማብራሪያ አለመስጠቱ እጅግ እንዳሳዘናቸው አስረድትዋል።

መቐለ ዩኒቨርሲቲ ልጃቸውን ልከው የሚያስተምሩ ሌላ እናት በላኩት መልዕክት ልጃቸውን ባለፉት ቀናት ሊያገኙት እንዳልቻሉ ተናግረዋል።

ዩኒቨርሲቲው በፌዴራል እና መከላከያ ጥበቃ ስር ነበር እኛም ደህንነቱ የተጠበቀ ነው በሚል ነው ልጆቻችን አምንነ የላክነው አሁን ግን በምን ሁኔታ ላይ እንዳሉ አናውቅም ብለዋል።

የፌዴራል ጠባቂዎች ቀድመው እንደሚወጡ ከታወቀ ለምን ልጆቻችን እንዲመለሱ አልተደረግም ሲሉም ጠይቀዋል ? ቤተሰብ በእጅጉ ተጨንቋል አስቸኳይ ማብራሪያ እንፈልጋለን ብለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ወላጆች እያቀረቡት ላለው ጥያቄ ምላሽ ለማግኘት ከፍተኛ ጥረት እያደረገ ነው፤እስካሁን ግን ምላሽ አላገኘም።

በሌላ በኩል የራያ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ግቢውን ለቀው እየወጡ ነው፥ በግቢው የቀሩ ተማሪዎች እንዳሉ የራያ ዩኒቨርሲቲ ቲክቫህ አባላት ጠቁመዋል።

በትግራይ በኔትዎርክ መቋረጥ ምክንያት መሬት ላይ ስላለው አሁናዊ ሁኔታ ትክክለኛ መረጃ ማግኘት አልተቻለም።

@tikvahethiopia
ይህ ገፅ የዓሲምባ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ዓዴፓ) ገፅ ነው ?

ፌስቡክ ላይ ዓሲምባ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ - ዓዴፓ Assimba Democratic party-ADP በሚል ስም የተከፈተ እና ከ20 ሺህ በላይ ተከታዮች ያሉት ገፅ #ሀሰተኛ ነው።

ከትላትን ጀምሮ ይህን ገፅ ዋቢ አድርገው የተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች እንዲሁም አንድ ዓለም አቀፍ ሚዲያ (ዶቼ ቨለ) መረጃዎችን ሲያጋሩ ተመልክተናል።

የፓርቲው ሊቀመንበር ከመታሰራቸው ከወራት በፊት ገፁ ሀሰተኛ ስለመሆኑ አሳውቀው ነበር።

የፓርቲው ሊቀመንበር አቶ ዶሪ አስገዶም "ገፁ ሀሰተኛ መሆኑን ፣ በዚሁ ሀሰተኛ ገፅ ላይ የሚወጡ መረጃዎች እና መግለጫዎች ዓሲምባ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ዓዴፓ)ን የማይወክሉ እንደሆነ" በተደጋጋሚ ገልፀው ነበር።

አቶ ዶሪ አስገዶም ከትግራይ ጦርነት ጋር በተያያዘ በኢሮብ ወረዳ የኤርትራ ወታደሮች ወረራ እየፈጸሙ ነው በማለታቸው ሳቢያ ለእስር ስለመዳረጋቸው ነው ከፓርቲው የተገኘው መረጃ የሚያመለክተው።

አቶ ዶሪ ታስረው የሚገኙት አዲስ አበባ ውስጥ ነው።

@tikvahethiopia
#Update

ዛሬ በአዲስ አበባ ከተማ፣ በአፋርና በአማራ ክልል የ8ኛ ክፍል ፈተና መሰጠት ተጀምሯል።

ሰኔ 21 ቀን 2013 ዓ.ም በሶማሌ ክልል የ8ኛ ክፍል ፈተና መሰጠት እንደጀመረ ይታወቃል።

@tikvahethiopia
#HachaluHundessa

አዲሱ የአርቲስት ሀጫሉ ሁንዴሳ “ማል መሊሳ (Maal Mallisaa) የሙዚቃ አልበም በዓለም አቀፉ የኢንተርኔት የሙዚቃ መሸጫ በiTunes ወርልድ ቻርት ሽያጭ 3ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል።

አልበሙ እስከ ትናንት ባለ መረጃ በተለቀቀ በሁለት ቀናት ውስጥ ነው 3ኛ ደረጃ ላይ መቀመጥ የቻለው።

“ማል መሊሳ” አለበም በ iTunes በሀገራት ባለው ሽያጭ ያለው ደረጃ ሲታይ በአውስትራሊያ፣ በካናዳ እና በተባበሩት አረብ ኢሚሬቶች 1ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል።

በአሜሪካ በ2ኛ ደረጃ ላይ፣ በብሪታንያ 9ኛ ደረጃ ላይ እንዲሁም በበርካታ ሀገራት እስከ 10 ባሉ ደረጃዎች ላይ መቀመጥ ችሏል።

በአይቱንስ ወርልድ የሙዚቃ ሽያጭ ሰንጠረዥ በየሰዓቱ የሚለዋወጥ ሲሆን ፤ የሙዚቃው የሽያጭ ደረጃ ሊጨምር አሊያም ሊቀንስ ይችላል።

አልበሙ በሀገር ውስጥ የኢንተርኔት የሙዚቃ መሸጫ በሆነው በ “ አውታር ” ላይም በ1ኛ ደረጃ እየተሸጠ ይገኛል ሲል አል አይን በድረገፁ ላይ አስነብቧል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Tigray በትግራይ በሚገኙት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ልጆቻቸውን ልከው የሚያስተምሩ ወላጆች ሙሉ በሙሉ ኔትዎርክ በመቋጠረጡ ልጆቻቸው ያሉበትን ሁኔታ ማወቅ እንዳልቻሉ ገልፀዋል። የኢትዮጵያ ፌዴራል መንግስት ተማሪዎች ስላሉበት ሁኔታም በአስቸኳይ ማብራሪያ እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል። በዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ልጃቸውን ልከው የሚያስተምሩ የቲክቫህ አባል፥ ስላልጃቸው ደህንነት ማወቅ ባለመቻላቸው በከፍተኛ ሁኔታ…
#MoSHE

የኢፌዴሪ ሳይንስ እና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ዛሬ ማምሻው በትግራይ ክልል በሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች ላሉ ተማሪዎች ቤተሰቦች አጭር መልዕክት አሰራጭቷል።

ሚኒስቴሩ በመልዕክቱ በትግራይ ክልል ውስጥ በሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች ያሉ ተማሪዎችን በተመለከተ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ ተቋማት እና የተቋማት አመራሮች ጋር እየመከረ እንደሚገኝ ገልጿል።

የተማሪዎች ቤተሰቦችም በትዕግሥት እንዲጠባበቁ ጠይቋል።

@tikvahethiopia
#Ethiopia

ባለፉት 24 ሰዓት በኢትዮጵያ የኮቪድ-19 ሞት አልተመዘገበም።

እንደ ኢፌዴሪ ጤና ሚኒስቴር ዕለታዊ ሪፖርት በኢትዮጵያ ውስጥ ባለፉት 24 ሰዓት የኮቪድ-19 ሞት አልተመዘገበም።

ከረጅም ወራቶች በኃላ ነው በ24 ሰዓት ውስጥ ምንም ሞት አለመመዝገቡ ሪፖርት የተደረገው።

በሌላ በኩል ባለፉት 24 ሰዓታት ውስጥ 4,974 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 137 ሰዎች ለቫይረሱ ተጋላጭ ሆነው ተገኝተዋል።

@tikvahethiopia
#Tigray

የትግራይ ክልል ወቅታዊ ጉዳዮች ፦

- በመላው የትግራይ ከተሞች ኔትዎርክ ባለመኖሩ መሬት ላይ ምን እየተካሄደ እንዳለ ለማወቅ አሁንም አዳጋች እንደሆነ ቀጥሏል።

- በተባበሩት መንግስታ ድርጅት (UN) የአሜሪካ አምባሳደር ሊንዳ ቶማስ ግሪንፊልድ ትግራይ ውስጥ ሁሉም የታጠቁ ወካላ ስለተኩስ አቁሙን እንዲያከብሩ ማለታቸው።

- ተመድ-UN መቐለ እና ሽረ የተረጋጋ ሁኔታ አለ ያለ ሲሆን በአንዳንድ የክልሉ አካባቢዎች ግን ግጭት እንዳለ ጠቁሟል። ቴሌኮሚኒኬሽን እና ኤሌክትሪክ በመላው ትግራይ እንደተቋረጠ መሆኑን ገልጿል።

- አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ወደ ኤርትራ እና ሱዳን የሚወስደው ድንበር ዝግ መሆኑን፣ ወደ አፋር እና አማራ በኩል ያለው ወሰንም ዝግ መሆኑን ገልፀዋል፤ የእርዳታ እና ሰብዓዊ ድጋፍ የሚሄደው ከመሃል ሀገር ነው እሱ ይገባል ከዛ ውጭ ግን (ከእርዳታ ውጭ) ሌሎች እንቅስቃሴዎች እንዳይኖር ጥብቅ ፍተሻ ይደረጋል ብለዋል።

- በትግራይ ክልል የታወጀው የተኩስ አቁም አዋጅ #ጊዜያዊ ሊሆን ይችላል በሚል የአሜሪካ ም/ቤት አንጋፋ አባላት እያስጠነቀቁ ይገኛሉ። ዴሞክራቱ ሪግሪ ሜክስ TPLF ኤርትራ ለመግባት መዛቱ ግልፅ እና አደገኛ ግጭቱን የማባባስ ተግባር ይሆናል ብለዋል።

- አቶ ጌታቸው ረዳ፥ "የተኩስ አቁም" ከመደረጉ በፊት የኤርትራ ጦር ይውጣ ብለዋል፤ የኤሌክትሪክ ኃይል እና ቴሌኮሚኒኬሽን እንዲመለስም አሳስበዋል፤ ኤሌክትሪክ እና ሌሎች አገልግሎቶችን አቋርጦ ሰላም ለማውረድ መጠበቅ አይቻልም ሲሉ ገልፀዋል።

- UNICEF በትግራይ ክልል ህፃናት ላይ ስለተጋረጠው አደጋ አሳውቋል።

- ጠ/ሚ ዶ/ር ዐብይ አሕመድ ከጋዜጠኞች ጋር የነበራቸው ቆይታ ፤ ባለፉት 8 ወራት ከወታደራዊ ጉዳዮች ወጪ ለመንገድ ለመብራት፣ ለሌሎች ተያያዥ ሥራዎች ትግራይ ውስጥ ከአንድ መቶ ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ መደረጉን ገልፀዋል።

ሁሉንም በዝርዝር ያንብቡ👇
https://telegra.ph/Tigray-Update-06-30-2

(ለቲክቫህ ቤተሰብ አባላት የተዘጋጀ የተሰባሰበ ሪፖርት)

@tikvahethiopia
#Update

ኢትዮጵያ በትናትናው ዕለት 2 ሺ 386 ዜጎቿን ከሳዑዲ አረቢያ በማስወጣት ወደ አገራቸው እንዲመለሱ አድርጋለች።

ሳዑዲ አረቢያ ውስጥ በችግር ላይ የሚገኙ ዜጎችን ወደሀገር የመመለሱ ዘመቻ ተጠናክሮ መቀጠሉ ተገልጿል።

@tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#Russia

ትላንትና በተ.መ.ድ. የሩሲያ ቋሚ ተወካይ ቫስሊ ኔቤንዚያ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል። በመግለጫቸ ካነሷቸው ጉዳዮች መካከል የኢትዮጵያ ፥ ትግራይ ክልል ጉዳይ አንዱ ነው።

አምባሳደር ቫስሊይ ኔቤንዚያ ፤ ሩስያ በትግራይ ስላለው ሰብዓዊ ሁኔታ እጅግ በጣም እንደሚያሳባት ገልፀዋል።

ለትግራይ ከፍተኛው የሰብዓዊ ዕርዳታ በኢትዮጵያ መንግሥት በኩል ሲቀርብ እንደነበረና አሁንም እየቀረበ መሆኑን መገንዘብ እና እውቅና መስጠት አለብን ብለዋል።

እንደሌሎች ሁሉ እኛም ለዓለም አቀፍ ድርጅቶች ሰብአዊ ተደራሽነት እንዲኖር እናበረታታለን ሲሉ ተናግረዋል።

በቅርቡ የኢትዮጵያ መንግስት ይፋ ያደረገው የአንድ ወገን/የተናጠል የተኩስ አቁም የተስፋ ጭላንጭል ነው ብለውታል።

በትግራይ ያለው ቀውስ ወታደራዊ መፍትሄ እንደሌለው በመግለፅም ቀውሱን መፍቻ የፖለቲካ መፍትሔ መሆኑን አስረድተዋል።

ጥያቄው አሁን የተፈጠረው ሁኔታ ጊዜያዊ ነው ? ወይንስ ለፖለቲካው መፍትሄ መንገድ ያመቻቻል? የሚለው ነው ሲሉ ጠይቀዋል።

ቫስሊ ኔቤንዚያ ፥ "አንዳንድ ባልደረቦቻችን በኢትዮጵያ ሁኔታ ላይ ግልጽ የሆነ መግለጫ እንድንሰጥ እየጠየቁን ነው ፤ ማናልባትም ይኖረናል ነገር ግን ሁሌም የምንለው የፀጥታው ምክር ቤት መወያየት ያለበት ለዓለም አቀፍ ሰላም እና ደህንነት ስጋት በሆነ ጉዳይ ነው" ብለዋል።

እናም መመለስ ያለበት ጥያቄ አለ ይኸውም "በኢትዮጵያ ያለው ሁኔታ ለዓለም አቀፍ ሰላም እና ደህንነት ስጋት ነውን ?" የሚለው ነው። መልሱ ሁኔታውን በምንመለከትበት አንግል ይወሰናል ሲሉ ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ጉዳይ በእጅጉ የአገር ውስጥ ጉዳይ ነው በመርህ ደረጃ የሀገር ውስጥ ጉዳዮችን በፀጥታው ምክር ቤት አጀንዳ ውስጥ ማስቀመጥን እንደምንቃወም አንሸሽግም ሲሉ ገልፀዋል።

@tikvahethiopia
የአዲስ አበባ የድህነት ምጣኔ ጨምሯል።

የአዲስ አበባ ከተማ የድሀነት ምጣኔ እየጨመረ መሆኑ ተገልጿል።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፕላንና ልማት ኮሚሽን ከፍሮንተሪ አማካሪ ድርጅት ጋር ባደረገው ጥናት ከክፍለ ከተማ ክፍለ ከተማ የድህነት ሁኔታ ቢለያይም የድህነት ሁኔታ እየጨመረ መሆኑን ሰኔ 22 ቀን 2013 ዓ.ም ከባለድርሻ አካላት በተደረገው ውይይት በጥናት መረጋገጡ ተገልጿል።

እንደ ፍሮንቴሬ አማካሪ ድርጅት ጥናት መሰረት በአዲስ አበባ ድህነት እየጨመረ መምጣቱ ዋና ዋና ምክንያቶቹ ፦

- በሀገሪቱ የተከሰተው የኮቪድ 19 ወረርሽኝ፣
- የመንግስት የማስፈፀም አቅም ውስንነት መኖሩ፣
- በከተማው ከጊዜ ወደ ጊዜ በተለያዩ ምክንያቶች የሰው ፍልሰት እየጨመረ መምጣቱ፣
- የስራ ዕድል ያለማግኘት፣
- ዝቅተኛ የስራ ባህል መኖሩ፣
- ህዝቡ የሚያነሳቸው የመልካም አስተዳደር ችግሮች ቶሎ ምላሽ ማግኘት አለመቻላቸው ፣
- በተለያዩ ምክንያቶች ለበሽታ የተጋለጡ ዜጎች ራሳቸውን ችሎ ያለማስተዳደር እና ድጋፍ የሚሹ መሆናቸው፣
- በተለያየ ማህበራዊ ችግር እና የከተማው የህዝብ ብዛት በፍጥነት እየጨመረ መምጣቱ ከኑሮ ውድነት ጋር ባለመመጣጠኑ የተነሳ በከተማው ውስጥ የድህነት ሁኔታ እየጨመረ መምጣቱ ጥናት አጥኚዎቹ ገልፀዋል።

የጥናቱ ተሳታፊዎች የተሻለ ውይይት በማድረግ ሁሉም ባለ ድርሻ አካላት ተቀናጅቶ በመስራትና በከተማ ደረጃ የታዩ ችግሮችን መቅረፍ እንዳለበት ተናግረዋል፡፡

መረጃው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፕላንና ልማት ኮሚሽን ነው።

@tikvahethiopia
#ETHIOPIA🇪🇹

ለቶኪዮ ኦሎምፒክ ተሳታፊ አትሌት ማን ተመረጠ ?

የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ከኢትዮጵያ የኦሎምፒክ ኮሚቴ ጋር በመተባበር #በቶኪዮ_2020 ውድድር ላይ የሚሳተፉ አትሌቶችን ከህዳር 2 ቀን 2013 ጀምሮ ለተከታታይ ስምንት ወራት ከመቶ በላይ አትሌቶችን እና አሰልጣኞችን ሆቴል በማስገባት ሳይንሳዊ እና ተከታታይ ስልጠና በማድረግ #በውጤታቸው 34 አትሌቶች መመረጣቸው ገልጿል ።

ለቶኪዮ ኦሎምፒክ 2020/21 የተመረጡ አትሌቶች ሙሉ ዝርዝር በምስሉ ላይ ተገልጿል።

ስፖርታዊ ገዳዮችን በ t.me/joinchat/VvwzStMNcNHmhK0x

@tikvahethsport