TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን⬇️

የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን #ወደነበረበት የሚመልስ ረቂቅ ዕቅድ ተዘጋጀ። ለመጀመርያ ጊዜ በአዲስ አበባ የፀጥታ አስተዳደር ቢሮ ይቋቋማል

በግንቦት 1997 ዓ.ም. ከተካሄደው #ምርጫ በኋላ በተፈጠረው ቀውስ ወደ #ፌዴራል መንግሥት የተዘዋወረውን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን፣ ወደ ከተማው አስተዳደር መመለስ የሚያስችል ረቂቅ ዕቅድ ተዘጋጀ፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አደረጃጀትና መዋቅር ጥናት ፕሮጀክት ጽሕፈት ቤት ባካሄደው ጥናት፣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የራሱ የሆነ አዲስ የፀጥታ አስተዳደር ቢሮ እንዲመሠርት ምክረ ሐሳብ አቅርቧል፡፡

የፕሮጀክት ጽሕፈት ቤቱ ባከናወነው ጥናት ላይ የመጀመርያ ዙር ውይይት ረቡዕ መስከረም 16 ቀን 2011 ዓ.ም. ተካሂዷል፡፡

በውይይቱ ወቅት በቀረበው ጥናታዊ ጽሑፍ፣ ‹‹የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የፀጥታ አስተዳደር ቢሮ›› የተሰኘ አዲስ የካቢኔ አባል የሚሆን ተቋም እንዲመሠረት ሐሳብ ቀርቧል፡፡

ይህ አዲስ ተቋም ላለፉት 14 ዓመታትአስተዳደር በፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን ሥር ሆኖ የቆየውን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን በድጋሚ ወደ ከተማው በመመለስ፣ የከተማውን ደንብ ማስከበር አገልግሎትና በክፍለ ከተማና በወረዳ የሚቋቋሙትን የፀጥታ አስተዳደር ጽሕፈት ቤቶችን አቅፎ ይይዛል፡፡

#የአዲስ አበባ ከተማ የፀጥታና ቢሮ ተጠሪነቱ በቀጥታ ለከተማ #አስተዳደሩ ከንቲባ ይሆናል ተብሏል፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አደረጃጀትና መዋቅር ፕሮጀክት ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሰይፈ ፍቃዱ ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ የተዘጋጀው ጥናት ለካቢኔ ቀርቦ ይሁንታ ካገኘ ለአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት ቀርቦ ሲፀድቅ ተግባራዊ ይሆናል፡፡

በቀረበው ረቂቅ ጥናት ላይ በሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 49 ንዑስ አንቀጽ 2 እና በቻርተሩ 95 አንቀጽ 10 መሠረት፣ አዲስ አበባ ከተማ ራሱን የማስተዳደር #መብት አለው፡፡

‹‹የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ራሱን በራሱ የማስተዳደር ሙሉ ሥልጣን ይኖረዋል፣ ዝርዝሩ በሕግ ይወሰናል፤›› ሲል ሕገ መንግሥቱ በአንቀጽ 49 ንዑስ አንቀጽ 2 ላይ ደንግጓል፡፡

ረቂቅ ጥናቱን ያቀረቡት የፕሮጀክት ጽሕፈት ቤቱ ከፍተኛ አማካሪ አቶ ቤተ ማርያም መኮንን እንዳሉት፣ አዲስ አበባ ከተማ እስካሁን የራሱ የፀጥታ አስተዳደር ቢሮ የለውም፡፡

‹‹ራሱን የቻለ የፀጥታ መዋቅር ባለመኖሩ የከተማውን ነባራዊ ሁኔታ መሠረት ባደረገ መንገድ ባለመደራጀቱ፣ የፀጥታ ተቋማቱ በተለያየ መዋቅር እንዲመሩ ሆኗል፤›› በማለት የገለጹት አቶ ቤተ ማርያም፣ ‹‹አዲስ የፀጥታ አስተዳደር መዋቅር ተግባራዊ ሲሆን ይህ ችግር ይፈታል፤›› ብለዋል፡፡

በአዲሱ መዋቅር መሠረት የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን፣ የክፍለ ከተማና የወረዳ የፀጥታ አስተዳደር ጽሕፈት ቤቶች፣ በማዕከል፣ በክፍለ ከተማና በወረዳ ያሉ የደንብ ማስከበር ጽሕፈት ቤቶች በቢሮው ሥር ይተዳደራሉ፡፡

በአዲስ አበባ ከተማ ባለፉት ዓመታት የፍትሕ፣ የፀጥታ፣ የሰላም፣ የመልካም አስተዳደርና የሰብዓዊ መብት ጥያቄዎች መነሳታቸውን ያስታወሱት ደግሞ፣ የከተማው ፍትሕ ቢሮ ኃላፊ አማካሪ አቶ ኤፍሬም ግዛው ናቸው፡፡

ከነዋሪዎች የሚነሱትን እነዚህን ችግሮች ለመፍታት፣ የከተማውን ሰላምና ፀጥታ አስተማማኝ ለማድረግ አዲሱ መዋቅር ወሳኝ ድርሻ እንዳለው አቶ ኤፍሬም ተናግረዋል፡፡

ይህ ጥናት እንዲካሄድ መመርያ የሰጠው የከተማ አስተዳደር ካቢኔ በመሆኑ፣ በሒደት ላይ ያሉ ሥራዎች ሲጠናቀቁ ተግባራዊ ይደረጋል ተብሏል፡፡

ምንጭ፦ ሪፖርተር
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን‼️

የፌዴራል ፖሊስ ልዩ ሃይልና በአየር የታገዘ የፖሊስ ቡድን እሰከማቋቋም የደረሰ የአደረጃጀት ማስተካከያ አደረገ። የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጀነራል #እንዳሸው_ጣሰው ዛሬ በሰጡት መግለጫ፥ የኮሚሸኑ ተቋማዊ ሪፎርም ሂደት እና የደረሰበትን ደረጃ አብራርተዋል።

የሰው ሃይል፣ ቴክኖለጂ፣ ስልጠና፣ ሎጅስቲክስ እና ከባለደርሻ አካላት ጋር የሚኖር ግንኙነት ላይ መሰረት ያደረገው #ሪፎርም በጥሩ አፈፃፀም ላይ እንደሚገኝ ኮሚሽነሩ ተናግረዋል።

በረፎርሙ መሰረት የፌዴራል ፖሊስ ሰራዊት አሰፋፈር እና አደረጃጀት #መከለሱን እንዲሁም በአራት አቅጣጫ በአራት ክላስትሮች እንዲከፋፈል መደረጉን ነው የገለፁት። ክላስተሮቹም፥ ሰሜን፣ ደቡብ፣ ምእራብ እና ማእከላዊ ክላስተር ናቸው።

በሪፎርሙ መሰረት የከተማ ልዩ የፌደራል ፖሊስ ሃይል እና #በአየር የታገዘ ክትትል ለማድረግም የፌራል ፖሊስ የአየር ሃይል ክንፍ ( AIR WING ) #ይደራጃልም ብለዋል ኮምሽነር ጀነራሉ።

የጦር መሳሪያ ትጥቅን በተመለከተም የፌዴራል ፖሊስ፣ የክልል ፖሊስ እና ልዩ ሃይል እንዲሁም ሚሊሻዎች ምን አይነት መሳሪያ ሊታጠቁ ይገባል የሚለውን የሚመልስ አዋጅ በመዘጋጀት ላይ ነው።

የሪፎርሙ አካል የሆነ የምርመራ ስርኣትን በሚመለከትም የምርመራ ማንዋል ተዘጋጅቶ በቅርቡ ወደ ትግባራ እንደሚገባ ተነግሯል።

#ፌዴራል_ፖሊስ ካሁን ቀደም ከምርመራ ጋር የተያያዙ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን ለማስቀረት ካሜራ የተገጠመላቸው፣ በመስታውት የተከለሉ፣ ሶስተኛ ወገን ምርመራውን መከታተል የሚችልባቸው የምርመራ ክፍሎች መዘጋጀታቸውም በመግለጫው ተነስቷል።

ምንጭ፦ FBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ለ5 ዓመታት ተቋርጦ የነበረውን የመካከለኛው ምስራቅ ሃገራት የአሰሪ እና ሰራተኛ ጉዞ የፎረንሲክ ምርመራ አገልግሎት መስጠት መጀመሩን የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ፡፡ ኮሚሽኑ አገልግሎቱን ከዛሬ ሚያዚያ 14 ቀን 2011 ዓ.ም ጀምሮ መስጠት መጀመሩን አስታውቋል፡፡

Via #ፌዴራል_ፖሊስ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ፌዴራል_ፖሊስ_ወንጀል_ምርመራ

የፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ጠቅላይ መምሪያ የኦፕሬሽን ዋና መምሪያ ኃላፊ ሙሊሳ አብዲሳ የሰጡት ማብራሪያ ፦

" ህግ ማስከበር ሲባል ብሄርን አይለይም፤ ሃይማኖትን አይለይም ፤ የፖለቲካ status አይለይም ፤ የሚዲያ አክቲቪስት ማንም ማንም ይሁን የSocial Status ፣ ሃይማኖቱ ምንም መሰረት አያደግም።

ህግ ለሁሉም እኩል ነው። እንደ ፖሊስ ሞያዊ ነፃነቱን ጠብቀን የምርመራ ስራ ጥቆማ ሲደርሰን በየትኛውም አካል ላይ ህግ የማስከበር ስራ እየተሰራ ነው የሚገኘው።

እንደሚታወቀው በአሁን ሰዓት ብዙ የሚዲያ ተከታይ ያላቸው ሰዎች ብሄርን ከብሄር የሚያጋጩ፣ ሃይማኖትን ከሃይማኖት የሚያጋጩ ፣ ጥርጣሬን የሚፈጥሩ የህዝቦቻችንን ፣ አጠቅላይ የኢትዮጵያን ህዝብ አብሮነት የሚፈታተኑ እነሱ ጥቅም የሚያገኙበትን በሚዲያ ዘመቻ የሚያደርጉትን በሽብር ድርጊት ውስጥ የተሳተፉትን ሰዎች በማስረጃ ላይ ሆነን መረጃ በመሰብሰብ በህግ ቁጥጥር ስር በማዋል ወደ ህግ እያቀረብን ነው።

ስለዚህ የሆነ ሚዲያ ወይ ጋዜጠኛ የሆነ ምንም ቢሆን እንደ defense ሊቀርብ አይችልም። በወንጀል ውስጥ የተሳተፈ መረጃ የተገኘበት ማንኘውም ሰው ላይ እርምጃ ይወሰዳል፤ በህግ ይጠየቃል፤ ግልፅ በሆነ ነፃ በሆነ ፍርድ ቤት አቅርበን ምርመራ ስራ እንሰራለን።

ስለዚህ በአሁን ሰዓት የሚዲያ ስራ ላይ የተሳተፉ ሰዎች እሱን እየተጠቀሙ አጠቃላይ stability እንዳይኖር የሆነ title እየሰጡ እንደ ገቢ ምንጭ የኢትዮጵያ ህዝብ ያልተረዳው ነገር እነኚህ አክቲቪስት የተባሉ ታሰሩ የተባሉ ግለሰቦች እንደ ገቢ ምንጭ የሚጠቀሙት አይነት ነው ያለው።

በምርመራ እንዳገኘነው አንድ ግለሰብ ከ4 ዩትዩበሮች ጋር ውል አስሯል፣ ከአንዱ ዩትዩበር 25 ሺህ ብር ነው የሚከገለው በአንድ ጊዜ እስከ 100 ሺህ ነው የሚከፈለው፤ ይሄን ለማድረግ ተመልካች እንዲያገኝ ለማድረግ ብሄርን ከብሄር የሚያጋጭ፣ ሃይማኖትን ከሃይማኖት የሚያጋጭ ፣ ወይም የመንግስትን ተቋም ፣ ወይም የመንግስትን ተሿሚዎች በሚያሸማቅቅ መልኩ ግልፅ በሆነ መልኩ characterize በማድረግ title እየሰጡ እንዲህ እያደረጉ ተመልካችን፣ like , share በብዛት እንዲያገኙ ብዙ ነገር በማድረግ ይሄን መሰረት በማድረግ destabilize በማድረግ የተለያዩ የወንጀል ድርጊቶችን፣ የሃሰት የውሸት ፕሮፖጋንዳዎችን በመልቀቅ ህዝቦች አብረው እንዳይኖሩ ሀገሪቱ በሰላም ተረጋግታ እንዳትኖር አጠቃላይ የማወክ ስራ እና ጥርጣሬ በሚፈጥር መልኩ ጥላቻን በውሸት ዘመቻ እያደረጉ ህዝቡ ላይ ይሄን እየጫኑ ለራሳቸውን የገቢ ምንጭ አድርገው ሀገሪቷን አደጋ ላይ ለመጣይ የሚሰሩ አካላት ናቸው በቁጥጥር ስር የዋሉት።

ይሄንን ደግሞ ፖሊስ ህግን መሰረት በማድረግ ፍርድ ቤት በማቅረብ የጊዜ ቀጠሮ በመጠየቅ በራሳቸው ፍላጎት በሚፈልጉት ጠበቃ ተወክለው በቤተሰቦቻቸው እየተጠየቁ ይሄን የምርመራ ስራ ፣ የህግ ማስከበር ስራ በደንብ እየተሰራ ነው።

ስለዚህ በአጠቃላይ ማንኛውም ሰው ከህግ በታች ነው።

ከህግ በታች እስከሆነ ድረስ ጥቆማ የቀረበበትን እንደፖሊስ ሙያን መሰረት አድርጎ የህግ የማስከበሩን ስራ ማንኛውም ሰው ላይ በየትኛውም ላይ ብዙ እሱን የሚከተል ሰው ሊኖር ይችላል ከዚህ በፊት እንደተደረገው ፣ የሃይማኖት ሰው ሊሆን ይችላል፣ ማንኛውም ሰው ሊሆን ይችላል ዋናው መሰረት የህግ ስህተት አለ ? ወይስ የለም ? የሚለው ነው። ስለዚህ እስካሁን ሃሳብን በነፃነት የመግለፅ ስም ብዙ ነገሮች ተችለዋል በአሁን ሰዓት ግን የለየለት የሽብር ስራ ፣ የሽብር ፈጠራ ፣ ሀገርን የማፍረስ ስራ ፣ ህግ የሌለ እስከማስመሰል ፣ የፍትህ ተቋማት እርምጃ መውሰድ አይችሉም የሚያስብል ደረጃ ላይ ደርሶ ሀገርን የማፍረስ ተልዕኮ ላይ እየሰሩ ያሉት አካላት ላይ የህግ የበላይነት ለማስከበር ከምን ጊዜውም በላይ የፌዴራል ፖሊስ ከሌሎች የፍትህ ተቋማት ጋር በመሆን የምርመራ ስራን እየሰራ ይገኛል። "

@tikvahethiopia
ጄነራሉ ምን አሉ ?

የሀገር መከላከያ ሰራዊት ምክትል ጠ/ኢታማዦር ሹም ጄነራል አበባው ታደሰ ለብሄራዊ የቴሌቪዥን ጣቢያ እና ለመከላከያ ሰራዊት ቴሌቪዥን ፕሮግራም ቃለመጠይቅ ሰጥተዋል።

ይኸው ቃለመጠይቃቸው ዛሬ ለህዝብ ተሰራጭቷል።

ጄነራሉ ምን አሉ ? በተለይም ስለ ልዩ ኃይል መልሶ ማደራጀት ጉዳይ ምን ሃሳቦችን አንስተው ተናገሩ ?

ጄነራል አበባው ታደሰ ፦

- መላ የኢትዮጵያ ህዝብ እንዲያውቅልን የምንፈልገው በሀገሪቱ የፀጥታ ኃይል እንዲገነባ ህገመንግስቱ የሚፈቅደው #መከላከያ_ሰራዊትና #ፌዴራል_ፖሊስን ነው።

- በየክልሉ ያለው ልዩ ኃይል በሳይዙ ልክ አለው ፤ በሌላ አነጋገር ሀገር በሚመስል ደረጃ 14 እና 15 ሬንጀር አለው ይሄ ፈፅሞ አይቻልም።

- አሁን ያለው የክልል ልዩ ኃይልን መልሶ የማደራጀት ስራ ዛሬ የተጀመረ / በሞራል የተገባበት ሳይሆን ከዚህ ቀደም ለረጅም ጊዜ ጥናት ተደርጎበት ነው።

- የክልል ልዩ ኃይሎች ፦ የክልልን ፀጥታን ይጠብቁ ነበር ፣ ከእኛ (ከመከላከያ) ጋር ሆነው ይሞቱ ነበር ህይወታቸውን አሳልፈዋል ፣ ቆስለዋል ደምተዋል። ይሄ ኃይል ይሄን የመሰለ ትልቅ ኳሊቲ ነበረው።

- ከህገመንግስት አንፃር ስናየው እነዚህ ኃይሎች ህጋዊ አይደሉም ህገመንግስቱ እውቅና አይሰጣቸውም። ለክልል ኃይል የሚሰጠው መደበኛ ፖሊስን ብቻ ነው። ህገመንግስቱ የታጠቀ ኃይል የሚያውቀው አንደኛ መከላከያ፣ ሁለተኛ ፌዴራል ፖሊስ፣ ሶስተኛ መደበኛ ፖሊስ ነው ከዚህ ውጭ ህገመንግስቱ አይልም።

- የኃይል አገነባቡ (የልዩ ኃይል መዋቅር) ብሔር ተኮር ነው ፤ ለኦሮሞ ህዝብ እሞታለሁ ብሎ ቃል ይገባል አማራውስ ? ጉዳዩ አይደለም ማለት ነው በግልፅ አማርኛ ፤ አማራው ደግሞ ይመጣና ለአማራ ህዝብ እሞታለሁ ይላል ኦሮሞውስ ? ጉዳዩ አይደለም ። ብሄር ተኮር ስለሆነ ሀገር አቀፍ የሆነውን አብሮነት የመኖር ፤ የህዝቦችን አንድነት ይሸረሽረዋል።

- የክልል ልዩ ኃይል መልሶ ማደራጀት ፕሮግራም ወደ መከላከያ ሰራዊት ማስገባት፣ ወደ ፌዴራል ፖሊስ ማስገባት፣ ወደ መደበኛ ፖሊስ ማስገባት ነው። በማን በራሱ ምርጫ፣ በምን ? ክብሩን ሞራሉን ፣ ጥቅሙን በማይነካ ሁኔታ።

- አፈፃፀሙ በተመለከተ ሁሉንም እኩል እደራጀዋለን ፣ በጥንቃቄም ይሰራል።

- አንደኛውን ክልል ኃይል እንዲኖረው ሌላውን ክልል ኃይል እንዳይኖረው አናድረግም። ይሄ ኢትዮጵያ ውስጥ አይታሰብም።

- የታጠቁ ኃይሎች ትጥቅ መፍታት አለባቸው ለምሳሌ የትግራይ የትግራይ ክልል እንደማንኛውም ክልል መደበኛ ፖሊስ ብቻ ነው የሚኖረው ፣ የታጠቀ ልዩ ኃይል የሚባል በፍፁም አይኖረውም።

- በአንዳንድ የአማራ ክልል አካባቢና ዩኒቶች ካልሆነ በስተቀር አማራ ልዩ ኃይል የሚባለው በአብዛኛው ተቀብሎታል ፤ ይሄ በኮሚኒኬሽን ያለ ችግር ነው ይሄን የኮሚኒኬሽን ችግር እየፈታን ነው ያለነው። አፈፃፀሙ ላይ የታየው ጉድለት ይሄ ነው እንዲህ አይነት ነገር ሊኖር እንደሚችል እንጠብቃለን አስበንም ነው የገባነው። ከዛ  ውጭ ባወጣነው ፕሮግራም መሰረት ይሄን ኃይል ወደምንለው ፕሮግራም እናስገባዋለን ሁሉንም እኩል አድርገን።

ያንብቡ 👇
https://telegra.ph/Tikvah-Ethiopia-04-07