TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#BREAKING የፌዴራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ 34 "የሕወሓት የፋይናንስ ተቋማትን" ማሳገዱን ገለፀ። - ሱር ኮንስትራክሽን ፣ - ጉና የንግድ ስራዎች ፣ - ትራንስ ኢትዮጵያ፣ - መስፍን ኢንዱስትሪያል ኢንጅነሪንግ ፣ - ሠላም የህዝብ ማመላለሻ ማህበር ፣ - ሜጋ ማተሚያ፣ - ኢፈርት ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር - ኢፈርት ኤሌክትሪካል ቢዝነስ እገዳ ከተጣለባቸው ተቋማት መካከል እንደሚገኙበት…
#UPDATE

የፌዴራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ የባንክ ሂሳባቸውን ያገደባቸው ድርጅቶች ዝርዝር ከላይ በምስሉ የምትመለከቷቸው ናቸው።

የድርጅቶቹ የባንክ ሂሳብ ለምን ታገደ ?

በተጠረጠሩባቸው ሶስት ወንጀሎች ምርመራ ጋር በተያያዘ ነው።

ድርጅቶች ከተጠረጠሩባቸው ወንጀሎች መካከል በኢትዮጵያ የተለያዩ ክፍሎች የሚፈጸሙ የዘር ተኮር ጥቃቶችን ፣ የሽብር ተግባራት እና የሕገ መንግስታዊ ስርዓትን በኃይል ለመናድ ከሚሰሩ አካላት ጋር በመመሳጠር እና ግንኙነት በመፍጠር በገንዘብ መደገፍ የሚል ይገኝበታል።

የታገዱት ድርጅቶች "በሙስና እና በወንጀል ድርጊት" የተገኘ ገንዘብን ሕጋዊ አስመስሎ ማቅረብ ወንጀሎች ምርመራ እየተደረገባቸው መሆኑን የጠቅላይ አቃቤ ህግ አሳውቋል።

Via ኢትዮጵያ ኢንሳይደር (የፌዴራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ)
@TIKVAHETHIOPIA @TIKVAHETHIOPIABOT
ችሎት !

ፍርድ ቤት ጋዜጠኛ በቃሉ አላምረው በዋስ ከእስር እንዲፈታ መወሰኑን 'አውሎ ሚዲያ' በይፋዊ የፌስቡክ ገፁ አሳውቋል።

@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
'ጊዜያዊ አስተዳደር በትግራይ ክልል'

ከ "ሕወሓት ነፃ" በሆኑ አካባቢዎች የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር መዋቅሩን እንደሚያደራጅ ዶ/ር ሙሉ ነጋ ገለፁ።

ዶ/ር ሙሉ ዛሬ በሰጡት መግለጫ ፥ "ዋና ሥራ አስፈጻሚው የፕሬዚዳንቱን ሥራ ስለሚሠራ ክልሉ ሙሉ ለሙሉ ነፃ ሲወጣ መንግሥታዊ ሥራውን ተክቶ ይሰራል" ብለዋል።

በዚህ መሠረትም የክልሉን ካቢኔ እንደሚያደራጅ እና የዞን አስተዳዳሪዎችን እንደሚሾም ገልጸዋል።

የወረዳ እና የቀበሌ ምክር ቤቶች ደግሞ ባሉበት እንዲቀጥሉ የሚደረግ መሆኑን አመልክተዋል።

ሥራ አስፈጻሚውን አካል እንደሚመራ ፣ እንደሚያስተባብር እንዲሁም የክልሉን ዕቅድ እና በጀት እንደሚያጸድቅ ኢዜአ ዘግቧል።

@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
#AddisAbabaPolice

የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን በአራዳ ክፍለ ከተማ በልመና ስራ በሚተዳደሩ አንዲት ግለሰብ ቤት ውስጥ ከ45 ሺህ ብር በላይ መገኘቱን ገለፀ፡፡

በአ/አ "በርሜል ሙሉ ገንዘብ ተከማችቶ ተገኘ" በሚል በተለያዩ መገናኛ ዘዴዎች እየተላለፈ ያለው መረጃ #የተሳሳተ መሆኑን ኮሚሽኑ አስታዉቋል፡፡

* የአ/አ ፖሊስ ኮሚሽን በጉዳዩ ዙሪያ የሰጠው ዝርዝር መረጃ ከፎቶ ጋር ከላይ ተያይዟል።

@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ችሎት ! ፍርድ ቤት ጋዜጠኛ በቃሉ አላምረው በዋስ ከእስር እንዲፈታ መወሰኑን 'አውሎ ሚዲያ' በይፋዊ የፌስቡክ ገፁ አሳውቋል። @tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
#UPDATE

ጋዜጠኛ በቃሉ አላምረው ዛሬ በ10,000 ብር ዋስ ፍርድ ቤት ከእስር እንዲለቀቅ ቢወሰንለትም ፣ ፖሊስ ይግባኝ በመጠየቁ ሊለቀቅ እንዳልቻለ "አውሎ ሚዲያ" ገለፀ።

"የመዝገብ ክፍል ሰዎች ባለመኖራቸው" ምክንያት ክሊራንስ ጨርሶ ከእስር የሚወጣው ነገ ነው ተብሎ ነበር።

ማምሻውን ፖሊስ ይግባኝ ስለጠየቀበት በእስር ይቆያል።

@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
#ICRC

በግጭቶች፣ በሌሎች የብጥብጥ ሁኔታዎች / በአደጋዎች ወቅት ሰዎች በቁጥጥር ስር ሊውሉ ወይም ሊጠፉ ይችላሉ።

ይህ ሁኔታ በቤተሰቦቻቸው እና ወዳጆቻቸው ላይ ጭንቀትና አለመረጋጋት ይፈጥራል።

ሰዎች በቁጥጥር ስር የዋሉ ወይም የጠፉ ዘመዶቻቸው ምን እንደገጠማቸው የማወቅ #መብት አላቸው።

የዓለም ቀይ መስቀል ኮሚቴ የዘመዶቻቸውን ዕጣ ፈንታ እና የት እንደሚገኙ ለማወቅ የሚጥሩ ቤተሰቦችን ይደግፋል፣ ያግዛል።

የICRC አገልግሎትን ለማግኘት የሚፈልግ ማንኛውም ሰው የICRC ኢትዮጵያ ልዑክ 0943122207 / 011 552 71 10 ላይ በመደወል ማነጋገር ይቻላል።

* የስልክ መስመሮቹ ሊጨናነቁ ስለሚችሉ ደጋግማችሁ ሞክሩ።

@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
#Security_Alert

በደቡብ ክልል 'ጋቶ፣ ፉጩጫ' እንዲሁም ሌሎች አካባቢዎች ዛሬም (ማክሰኞ) የፀጥታ ችግር መኖሩን የቲክቫህ ኢትዮጵያ አባላት አሳውቀዋል።

ዛሬም የተኩስ ድምፅ ይሰማ እንደነበር ገልፀዋል።

በተመሳሳይ 'ጉማይዴ' አካባቢ ያለው የፀጥታ ችግር አሁንም እንዳልተፈታ አባላቶቻች ገልፀዋል።

* በዚህ አካባቢ ያሉ የሀገራችን ዜጎች በሰላም እጦት እጅጉን እየተሰቃዩ ነው ፤ መንግስት እጅግ አስቸኳይ የሆነ መፍትሄ እንዲሰጣቸው ጥሪ አቅርበዋል።

@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
#FDREDefenseForce

የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የመረጃ ማጣሪያ የመከላከያ ሰራዊቱ በምሥራቁ ግንባር ራያን ሙሉ በሙሉ ነጻ ማውጣቱን ገለፀ።

ሰራዊቱ ጨርጨር፣ ጉጉፍቶ መሖኒን ነጻ አውጥቷል ተብሏል።

በየቦታው የነበሩትን ወሳኝ የኮንክሪት ምሽጐችንም እንዳፈረሰ ተገልጿል።

ሠራዊቱ በአሁኑ ጊዜ ወደ መቐለ በመገሥገሥ ላይ ነው።

በምዕራብ ግንባር "በአዲ ነብሪድ እና በአዲ ዳእሮ" የሚገኙ ከባድ ምሽጎችንም በማፍረስ ሽሬን ተቆጣጥሮ ወደ አክሱም እየገሰገሰ መሆኑ ተገልጿል።

በውጊያው እጅግ ብዙ መሣሪያዎች ተማርከዋል ፤ የትግራይ ልዩ ኃይል አባላትም በቁጥጥር ሥር ውለዋል ሲል የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የመረጃ ማጣሪያ አሳውቋል።

@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
#DrLiaTadesse

የባለፉት 24 ሰዓት የኮቪድ-19 ሪፖርት :

• የተደረገ የላብራቶሪ ምርመራ - 3,778
• በበሽታው የተያዙ - 339
• ህይወታቸው ያለፈ - 7
• ከበሽታው ያገገሙ - 163

አጠቃላይ 103,395 ሰዎች በበሽታው መያዛቸው ሲረጋገጥ ፤ የ1,588 ሰዎች ህይወታቸውን አጥተዋል ፤ 64,293 ሰዎች ደግሞ ከበሽታው አገግመዋል።

320 ሰዎች በፅኑ ታመው የህክምና ክትትል እየተደረገላቸው ይገኛል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#SecretaryPompeo

የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ምኒስትር ማይክ ፖምፔዎ ህወሓት በኤርትራ ላይ የፈጸመውን ጥቃት አወገዙ።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ "ህወሓት በኤርትራ ላይ የፈጸመውን ጥቃት እና ግጭቱን ዓለም አቀፋዊ ለማድረግ ያደረገውን ሙከራ አጥብቀን እናወግዛለን" ብለዋል።

"ህወሓት" እና የኢትዮጵያ ባለሥልጣናት ግጭቱን ለማብረድ ፣ ሰላምን ለማስፈን እና የሰላማዊ ሰዎችን ደሕንነት ለመጠበቅ አፋጣኝ እርምጃ እንዲወስዱ ጥሪ እናቀርባለን" ሲሉ መልዕክት አስተላልፈዋል።

ፖምፕዎ ዛሬ በሰጡት መግለጫ ፥ ኤርትራ የአጸፋ እርምጃ ባለመውሰድ መታቀቧ ግጭቱ እንዳይስፋፋ ማገዙን ጠቅሰው አመስግነዋል።

በተጨማሪ የሰብዓዊ ዕርዳታ ሰራተኞች ለተጋላጮች ዕገዛ እንዲያቀርቡ ደሕንነቱ የተጠበቀ መተላለፊያ ሊፈቀድላቸው ይገባል ብለዋል ፖምፕዎ።

የአሜሪካ ዜጎችን ጨምሮ ሰላማዊ ሰዎች ከጉዳት ሊጠበቁ ፣ ሰብዓዊ ዕርዳታ ሊሰጣቸው እና ከግጭት ቀጠናው የሚወጡበት መተላለፊያ ሊፈቀድላቸው እንደሚገባም አስገንዝበዋል።

ገለልተኛ የሆነ ዘገባ ለመስራት እንዲቻልና የአሜሪካ ዜጎችን ጨምሮ ከሰላማዊ ሰዎች መገናኘት እንዲቻል በትግራይ የተቋረጡ የመገናኛ አገልግሎቶች ወደ ሥራ ሊመለሱ እንደሚገባም መናገራቸውን ዶቼ ቨለ ዘግቧል።

@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
#UPDATE

የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የመረጃ ማጣሪያ 'ህወሓት' የትግራይ መሰረት ልማቶችን እያፈረሰ ነው አለ።

"ህወሓት" በሁሉም አቅጣጫዎች ወደ #መቐለ የሚወስዱት መንገዶች ላይ የሚገኙ አራት (4) ድልድዮችን አፍርሷል ሲል ገልጿል።

በሽሬና በአክሱም መካከል የሚገኘውን አስፓልት "በግሬደር" ቆፍሮ ወደ ጉድጓድነት ቀይሮታል ሲልም አሳውቋል።

የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የመረጃ ማጣሪያ ፥ "ህወሓት እስከዛሬ ከፈጸማቸው ወንጀሎች በተጨማሪም ባወደማቸው መሠረተ ልማቶች በቅርቡ ይጠይቅባቸዋል" ብሏል።

@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
'የንፁሃን ዜጎቻችን ስደት'

በትግራይ ክልል ያለውን ወጊያ በመሸሽ ወደ ሱዳን እየገቡ ያሉ ሰዎች ቁጥር በእጅጉ እየጨመረ ነው።

አሁን ላይ ያለው ሁኔታም እጅግ አሳሳቢ ነው።

UNCHR ሰላማዊ ከሆነው ኑሯቸው ላይ ተፈናቅለው ሱዳን ለገቡት የሀገራችን ዜጎች ከሱዳን መንግስት ጋር በመሆን የህይወት አድን እርዳታ ለመስጠት እየሰራ ይገኛል።

እስከዛሬ ድረስ ባለው መረጃ ወጊያውን ሸሽተው ወደ ሱዳን የገቡ ዜጎቻችን ከ30,000 ይበልጣሉ።

በትግራይ የኢንተርኔት መቋረጥ ፣ የባንኮች መዘጋት ፣ የትራንስፖርት አገልግሎት አለመኖር ፣ የመሰረታዊ አቅርቦት እጥረት መፈጠሩ በእጅጉ ዜጎቻችን ለችግር አጋልጧቸዋል።

በትግራይ ክልል ልጆቻቸውን የሚያስተምሩ፣ ዘመድ አዝማዶቻቸው ትግራይ ውስጥ የሚኖሩ እርስ በእርስ ከተገናኙ 15 ቀን ሊሆናቸው ነው።

@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
#PMOEthiopia

የኢትዮጵያ ፌዴራል መንግስት በትግራይ ክልል እያካደ የሚገኘውን "ሕግ የማስከበር እንቅስቃሴ" በብሔር ወይም በሌላ ወገንተኝነት ላይ የተቃኘ ነው የሚለውን የተሳሳተ እሳቤ አጥብቆ እንደሚያወግዝ ዛሬ ህዳር 9/2013 ዓ/ም ባወጣው መግለጫ አሳውቋል።

እየተካሄደ ባለው "የህግ ማስከበር ዘመቻ" የትግራይ ህዝብ የመጀመሪያው ተጠቃሚ ይሆናል ሲል በመግለጫው ላይ ገልጿል።

* የጠቅላይ ሚኒስትር ፅ/ቤት ያወጣው መግለጫ ከላይ ተያይዟል።

@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
#ታሽገዋል

ዋልያ ቆዳ ፋብሪካ እንዲሁም አዲስ አበባ ቆዳ ፋብሪካ አክሲዮን ማህበር የአካባቢ እና የህብረተሰቡን ጤና የሚጎዳ ብክለት በማድረሳቸዉ ምክንያት ታሸጉ።

በአቃቂ ቃሊቲ እና በኮልፌ ቀራኒዮ ክ/ከተማ የሚገኙት ሁለቱ ፋብሪካዎች የሚለቁት ከፍተኛ የሆነ ያልታከመ አደገኛ ፈሳሽ ቆሻሻ በአካባቢዉ ላይ ብክለት እያደረሰ እንደሚገኝ ህብረተሰቡ አቤቱታዎችን ሲያቀርብ ነበር።

የአዲስ አበባ ከተማ አካባቢ ጥበቃና አረንጓዴ ልማት ኮሚሽን የአካባቢ ብክለት ኢንስፔክሽን ባለሙያዎችም በመስክ ባደረጉት ምልከታ ይህንን ማረጋገጥ ችለዋል።

ይህ መረጃ ከአዲስ አበባ ከተማ አካባቢ ጥበቃ እና አረንጓዴ ልማት ኮሚሽን የተገኘ ነው።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia